UMMA TOKEN INVESTOR

About me

Ya! Allah Give me Sobr!

Translation is not possible.

በረመዳን በብዛት የሚፈፀሙ ስህተቶች

~~~~

① ሶላት ሳይሰግዱ መፆም፣

② ሌሊቱን በጫት ካሳለፉ በኋላ ሱሑርን አስቀድሞ በመመገብ ፈጅር ሳይሰግዱ መተኛት፣

③ ቀኑን በእንቅልፍ፣ ሌሊቱን በተከታታይ ፊልም/ ሙሰልሰላት ማሳለፍ፣

④ ረመዳንን ጠብቆ መንዙማና ነሺዳ እየለቀቁ ሰዎችን ከቁርኣን ማዘናጋት፣

⑤ ተራዊሕን በንቃት እየሰገዱ ፈጅር ሶላትን በእንቅልፍ ማሳለፍ፣

⑥ ተራዊሕ ላይ በየ አራቱ ረከዐ መሐል የቢድዐና የሺርክ እንጉርጉሮዎችን ማስገባት፣

⑦ የተራዊሕ ኢማሞች ከሶላቱ ይልቅ ለቁኑት ዱዓእ የበለጠ ትኩረትና ጊዜ መስጠት፣

⑧ መግሪብ ሶላት ሲጠናቀቅ አሳፋሪ በሆነ መልኩ ለፊጥራ መጣደፍ (ሰጋጆችን የሚያቋርጥ፣ የሰው ጫማ የሚያቀያይር፣…ብዙ ነው)

⑨ ሌሊት ላይ "ተሰሐሩ " እያሉ በእስፒከር መጮህ፣

(10) የሱሑር ጊዜ ሳያልቅ ለጥንቃቄ በሚል ቀድሞ አዛን ማድረግ፣

(11) ሱሑር ላይ "ነወይቱ ሰውመ ገዲን" እያሉ በቃል መነየት፣

(12) እያንቀላፉ ተራዊሕ መስገድ፣

(13) ልጆች "እንፁም" ሲሉ ማበረታታት ሲገባ መከልከል፣ "ውሃ አያፈጥርም፣ ተደብቀህ ብላና ትፆማለህ" እያሉ መዋሸትና ውሸት ማለማመድ፣

(14) ሴቶች በተጋነነ የምግብ ዝግጅት ሰፊ ጊዜያቸውን ማቃጠል፣

(15) ሴቶች ሽቶ ተቀብቶ ለተራዊሕ መውጣት፣

(16) በተራዊሕ ወቅት የሴቶችና የወንዶች አላስፈላጊ መዝረክረክ፣

(17) ሃሜት፣

(18) ፊጥራ ላይ ከመጠን በላይ መመገብ፣

(19) ቀኑን በካርታ፣ በዳማ፣ ወዘተ ማሳለፍ፣

(20) ሙዚቃ ማዳመጥ፣

(21) የሰው ስራ የሚሰሩ ተቀጣሪዎች ጧት በሰዓት አለመግባት (አማና መጠበቅ፣ ቃልን ማክበር ግድ ይላል። ግዴታ ያልሆኑ ዒባዳዎች ተፅእኖ የሚያሳድሩብን ከሆነ መተው ወይም መቀነስ ነው)፣

(22) በተለይ በስራ ቦታዎች ላይ በመንዙማና በነሺዳ ማሳለፍ (መሆን ያለበት ከተመቼ ቁርአን መቅራት፣ ካልሆነ ዚክር ማድረግ ወይም ደዕዋ ማዳመጥ፣ ካልሆነ ዝምታ ይሻላል።)

(23) ለይለተል ቀድርን ለማየት ሰማይ ሰማይ እያንጋጠጡ መጠበቅ (የሚታይ ነገር የለም)፣

(24) አንዳንድ አካባቢዎች ዒሻን በጣም በማዘግየት ሰው ጀማዐ ላይ እንዳይካፈል እንቅፋት መሆን፣

(25) አንዳንድ አካባቢዎች መስጂድ ውስጥ ጫት ይዞ ገብቶ መቃም፣

(26) አንዳንድ አካባቢዎች "ተርቲብ" ብለው ንፍሮ፣ ቆሎና መሰል ምግቦችን ወደ መስጂድ እንዲያቀርቡ ሰዎችን ማዘዝ፣ ወዘተ

=ዒብኑ ሙነወር

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እንደሆነ ይረዳበታል። ይህም የሚሆነው ግለሰቡ የፈለገውን እና የተፈቀድልትን መብላት እና መጠጣት እንዲሁም ከተፈቀደለት አካል ጋር የግብረ ስጋ ግንኙነትን ማድረግ በፈለገ ሰአት እንዲያገኝ አላህ ያገራለት መሆኑን ስለሚያስተውልበት ነው። ስለሆነም ጌታውን ያመሰግናል፣ ይህንን ማግኘት ያልቻለውን ድሃ ወንድሙን ያስታውሳል በዚህም የተነሳ ለሱ ምፅዋትን (ሰደቃን) ይሰጣል እንዲሁም መልካም ተግባራትን በመፈፀም የቸርነትን ባህሪ ይላበሳል።

ከፆም መደንገግ ጥበቦች መካከል፦ የሰው ልጅ እንዴት አድርጎ ነፍሱን (ስሜቱን) መቆጣጠር እና ሙሉ ለሙሉ በርሱ የበላይነት ስር በማዋል ለርሶ በቅርቢቱ ዓለምም (ዱንያ)ም ይሁን በወዲያኛው ዓለም (አኼራ) መልካም እንዲሁም ስኬታማ ወደ ሆነው አቅጣጫ መምራት እንደሚችል የሚለማመድበት መድረክ መሆኑ ነው። በዚህም ነፍሱን ከፍላጎቶቿ መከልከል የማይችል እንስሳዊነት የተጠናወተው ሰብአዊ ፍጡር ከመሆን ይልቅ ለርሷ ጠቃሚ የሆነውን ወደ ማሟላቱ ያዘነብላል።

ከፆም መደንገግ ጥበቦች መካከል፦ ፆመኛ ምግብን በመቀነሱ የተነሳ ጨጓራ እና መሰል የምግብ መፈጨት ሂደት የሚከናወንባቸው የሰውነት ክፍሎች ለተወሰነ ግዜ እረፍት ያገኛሉ በተጨማሪም አንዳንድ ለሰውነት አላስፈላጊ የሆኑ በሰውነት ውስጥ የሚገኙ እንደ ስብ እና መሰል ትርፍ ጎጂ ነገሮች መወገድ ከጤና ጋር ተያያዥነት ካላቸው የፆም ጥቅሞች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።

ኢንሻ አላህ ክፍል ሶስት ይቀጥላል…

በበሸታ እና በመንገድ ላይ ስላሉ ሰዎች የጾም ህግጋት በተመለከተ ይሆናል። 

አላህ በተሞላ ጤንነት እና እሱ በሚወደው መልኩ ረመዷንን ከሚጾሙት ያድርገን። በተለያየ የጤና እክል ላይ ላሉትም አላህ ጤንነትን ይስጣቸው!!

✍️መንቁል!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ክፍል አንድ

የፆም ብይንን (ሑክምን) በተመለከተ

የረመዷንን ወር መፆም ግዴታነት በቁርአን፣ በሐዲስ እና በሙስሊሙ ማህበርሰብ ስምምነት (ኢጅማዕ) የተረጋገጠ ነው። አላህ እንዲህ ይላል፡-

[[ يَاأَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُتِبَ عَلَيْكُمُ الصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى الَّذِينَ مِنْ قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ (183) أَيَّامًا مَعْدُودَاتٍ فَمَنْ كَانَ مِنْكُمْ مَرِيضًا أَوْ عَلَى سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِنْ أَيَّامٍ أُخَرَ وَعَلَى الَّذِينَ يُطِيقُونَهُ فِدْيَةٌ طَعَامُ مِسْكِينٍ فَمَنْ تَطَوَّعَ خَيْرًا فَهُوَ خَيْرٌ لَهُ وَأَنْ تَصُومُوا خَيْرٌ لَكُمْ إِنْ كُنْتُمْ تَعْلَمُونَ (184) شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنْزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِلنَّاسِ وَبَيِّنَاتٍ مِنَ الْهُدَى وَالْفُرْقَانِ فَمَنْ شَهِدَ مِنْكُمُ الشَّهْرَ فَلْيَصُمْهُ وَمَنْ كَانَ مَرِيضًا أَوْ عَلَى سَفَرٍ فَعِدَّةٌ مِنْ أَيَّامٍ أُخَرَ يُرِيدُ اللَّهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَى مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ ]] [البقرة: ١٨٣ - ١٨٥]

ትርጉሙም፦ «እናንተ ያመናችሁ ሆይ ፆም በነዚያ ከናንተ በፊት በነበሩት (ሕዝቦች) ላይ እንደ ተጻፈ በናንተም ላይ ተጻፈ (ተደነገገ) ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡ የተቆጠሩን ቀኖች (ጹሙ)፤ ከናንተም ውሰጥ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነ ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን መፆም አለበት፤ በነዚያም ፆምን በማይችሉት ላይ ቤዛ ድኻን ማብላት አለባቸው፤ (ቤዛን በመጨመር) መልካምንም ስራ የፈቀደ ሰው እርሱ (ፈቅዶ መጨመሩ) ለርሱ በላጭ ነው፤ መጾማችሁም ለናንተ የበለጠ ነው፤ የምታውቁ ብትኾኑ (ትመርጡታላችሁ)፡፡ (እንድትፆሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርአን የተወረደበት የረመዷን ወር ነው፤ ከናንተም ወሩን ያገኘ ሰው ይጹመው፤ በሽተኛ ወይም በጉዞ ላይ የኾነም ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን (በልኩ) መፆም አለበት አላህ በናንተ ገሩን (ነገር) ይሻል፤ በናንተም ችግሩን አይሻም፤ ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡» (አል-በቀራ፡ 183-185)

ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦ «ኢስላም በአምስት መሰረቶች ላይ ተገንብቷል:: እነርሱም፦ ከአላህ ሌላ አምልኮ የሚገባው አምላክ እንደሌለና ሙሐመድም የአላህ መልእክተኛ እንደሆኑ መመስከር፣ ሰላትን በተሟላ ሁኔታ መስገድ፣ ዘካን መስጠት፣ ወደተከበረው የአላህ ቤት ለሐጅ መጓዝ እና የረመዷንን ወር መፆም ናቸው::» (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)

በሌላው የኢማሙ ሙስሊም ዘገባ «የረመዷንን ወር መፆም እና ወደ ተከበረው የአላህ ቤት ለሐጅ መጓዝ ናቸው::» በሚል (ቅደም ተከተል) ሰፍሯል።

የረመዷንን ወር መፆም ግዴታነት ሙስሊሙ ማህበረሰብ በአጠቃላይ ተስማምቶበታል:: ስለሆነም የረመዷንን ወር መፆም ግዴታነትን ያስተባበለ ከኢስላም በኋላ ወደ ክህደት የገባ (ሙርተድ) ተደርጎ ይቆጠራል:: ተውበት እንዲያደርግ ይመከራል ከዚህ አቋሙ ተመልሶ ግዴታነቱን ካረጋገጠ ይተዋል ካልሆነ ግን (በኢስላማዊ ህግ ስርአት በሚተዳደሩ ሀገሮች ውስጥ በህግ ፊት) ከሃዲ እንዳለ በሞት ይቀጣል::

የረመዷንን ወር መፆም ግዴታ የሆነው ከሂጅራ በሁለተኛው አመት ነበር:: በዚህም መሰረት መልእክተኛው(ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ዘጠኝ ረመዷኖችን ፆመዋል:: ፆም በእያንዳንዱ ለአካለ መጠን በደረሰ እና ጤናማ አዕምሮ ባለው ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው:: ፆም ሙስሊም ባልሆነ (በካፊር) ላይ ግዴታ አይሆንም:: ኢስላምን እስካልተቀበለ ቢፆምም ተቀባይነት የለውም። ለአካለ መጠን እስካልደረሰም በሕፃን ልጅ ላይ ፆም ግዴታ አይሆንም። ወንድ ልጅ አስራ አምስት አመት በመሙላቱ ወይም በሀፈረተ-ገላው አካባቢ ያሉ ፀጉሮች በማደጋቸው አልያም በመኝታ ላይ እያለም ይሁን ከዚያ ውጪ የዘር ፈሳሽ ከፈሰሰው ለአካለ መጠን መድረሱ ሲታወቅ ሴት ልጅ ደግሞ ከነዚህ ምልክቶች አንዱን ወይም የወር አበባን በማየቷ ለአካለ መጠን መድረሷ ይታወቃል:: አንድ ታዳጊ ከነዚህ ምልክቶች መካከል አንዱ ከታየው ለአካለ መጠን ደርሷል ማለት ነው:: ሆኖም ታዳጊው ያለምንም መጎዳት መፆምን ከቻለ ለአካለ መጠን ባይደርስም ፆምን እንዲለምድ እና ለወደፊቱ የመፆም አቅምን እንዲያጎለብት በማሰብ እንዲፆም ይታዘዛል:: በአእምሮ መቃወስ አልያም በሌላ ምክንያት እራሱን በመሳቱ እና በመሳሰሉት ምክንያቶች በትክክል ማሰብ የተሳነው ሰውም ፆም ግዴታ አይሆንበትም:: በዚህ መሰረት ነገሮችን መለየት የተሳነው የጃጀ ሽማግሌ የመፆምም ይሁን (ምስኪን) የማብላት ግዴታ የለበትም::

ኢንሻ አላህ ክፍል ሁለት ይቀጥላል…

ለሌሎች በማድረስ ለኢሰላማዊ እውቀት መስፋፋት የበኩላችንን አስተዋፅኦ በማበርከት የምንዳው ተቋዳሽ እንሁን።

አላህ ያግራልን!!

መንቁል!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Ibnu Sherefa shared a
Translation is not possible.

Sheikh Dr. Salih Fewzan Al-Fewzan

ሸይኽ ዶ/ር ሷሊሕ ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና የአይሁዶች በፈለስጢን አካባቢ መሰባሰብ የቂያም ቀን አንዱ ምልክት ነው ይላሉ።

አላህ እነዚህን ካፊሮች ከነ አጋሮቻቸው ከምድረ ገፅ ያጥፋቸው።

192 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Ibnu Sherefa shared a
Translation is not possible.

እናተ በአላህ የመናቹ ሙስሊሞች ሆይ አላህ ከታገሱት ጋር ነኝ ብሎዋል ስለዚህ እኛ የምንሞትለት ዲን እጂ ዱንያ የለንም...የፍልስጤማውያን ሙስሊሞች ሰቆቃ በቃችሁ በላቸው አሚን አሚን!!!

أيها المسلمون المتقون، قال الله إني مع الصابرين، فليس لنا دين نموت من أجله إلا الدنيا، أرجو أن تتقبلوا معاناة المسلمين الفلسطينيين، آمين، آمين!!!

Send as a message
Share on my page
Share in the group