Abu Hamza Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Abu Hamza shared a
Translation is not possible.

☑️ ዒልም የማይጠገብ ስብእና..!!

~ ኢብኑ ተይሚያ

አምሮታቸው ፣ጉጉታቸው ፣ኢልም መቅስም ፣ ኢልም ማስራጨት ነበር። ለኢልም ሲሉ የለበሱት ልብስ ከላያቸው ላይ ከሚያድፍ ትተውታል። ለዒልም ሲሉ ከፍተኛ ስልጣንን አሽቀንጥረው ጥለዋል። ኢብኑ ተይሚያ ባሉበት የሆድና የሴት ጉዳይ አይነሳም። አጥጋቢ ድምዳሜ ላይ ያልደረሱበትን ጉዳይ ከጫፍ ሳይደርሱ ልባቸው አያርፍም። አንዳንዴ አንዲትን የቁረአን አንቀጽ እያጠናሁ ምናልባትም ወደ መቶ አካባቢ ተፍሲሮችን የማገላብጥበት ጊዜ አለኝ" ይላሉ።

{ አልዑቁድ : 42}

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Hamza shared a
7 month Translate
Translation is not possible.

በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው እና በትላንትናው ዕለት የተካሄደው

ካዝማት ቺማቭ እና ቀመሩ ኡስማን

ዩኤፍሲ 294 ግጥሚያ ቺቺኒያዊው ካዝማት በአሸናፊነት ካጠናቀቀ በኃላ ባደረገው ንግግር

" ምንም እንኳ ታላቅ ውድድር ያሸነፍኩ ቢሆንም ደስታዬ የተሟላ አይደለም ሙስሊም ወንድሞቼ በእስራኤል በግፍ እየተጨፈጨፉ እኔ ቁምጣ ለብሼ እዚህ መቧቀስ አያምርብኝም

ክብሬም፣ ዝናዬም ይቅርብኝ

ወላሂ መሳሪያ አስታጥቀኝ ከፍልስጤም ወንድሞቼ ጎን ተሰልፌ በክብር መሞት ነው ፍላጎቴ " በማለት ለቺቺኒያው ፕሬዝዳንት ራምዛን ጥሪ አቅርቧል

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Hamza shared a
7 month Translate
Translation is not possible.

"አል-አቅሷዐ በመስቀላዊያን እጅ ውስጥ ሆኖ ሳለ እኔ እንዴት ፈገግ ልል እችላለሁ? ምግብ እና ውሃ ከእኔ ጋር እንዴት ጣዕም ሊኖራቸው ይችላል?!" ይህ ቁድስን ከወራሪዎቹ የመስቀል ጦረኞች ነፃ ሳያወጣ በፊት አንድ ጊዜም ፈገግ ብሎ የማያውቀው የጀግኖቹ ጀግና የኩርዳዊው #ሰላሁዲን_አልአዩቢ ንግግር ነበር!

የቅርቡን የዚህችን እጅግ ጥንታዊት ከተማ ታሪክ እናንሳ እንኳ ቢባል ለ በርካታ መቶ አመታት በባይዛንታይን ሮሞች አረመኔያዊ አገዛዝ ስትማቅቅ የቆየችው ቁድስ በነ #ኻሊድ_ኢብን_ወሊድ እና #አቡኡበይዳ_ኢብን_አልጀራህ የሚመራው ጦር ባይዛንታይኖችን አንበርክኮ ቁድስ ዳግም በሙስሊሞች እጅ ለመግባት ችላ ነበር። የቁድስን ቁልፍ ቦታው ድረስ ሂደው የተቀበሉት #ኡመር_ኢብኑል_ኸጧብ የቁድስን ነዋሪዎች ነፃነት አውጀው ነበር የተመለሱት። ቁድስ ከዚያ በሗላ በፍትህና በኢስላማዊው ስልጣን ተንቆጠቆጠች። በኡመር ጊዜ ሙስሊሞች ከተቆጣጠሯት በሗላ ቁድስ እስከ መጨረሻው በሙስሊሞች እጅ አልቆየችም። የሙስሊሞችን መከፋፈልና እርስበርስ መባላት ተጠቅመው ባይዛንታይኖች ዳግም ቁድስን ተቆጣጠሩ። ቁድስ ዳግም የጨለማ ዘመን ውስጥ ገባች። ከተማዋን በደል ግፍና ጭካኔ ሞላት! በከተማዋ የሚስኪኖች ዋይታና የገዥዎች ከልክ ያለፈ አረመኔነት እንጅ አይሰማም አይታይም ነበር! ቁድስ በባይዛንታይኖች እንደዚህ በበደል ተውጣ ቆዝማ አዝና ብዙ አመታትን አሳለፈች! አሏህ #ሰልጁቅ የተሰኙ ቱርኮችን ከወደ ምስራቅ ኤዥያ አስነሳ። የሰልጁቅ የልጅ ልጅ የሆኑት እነ #ቱግሪል#ቻግሪ#አልፕ_አርስላን#መሊክ_ሻህ የመሳሰሉ ተወዳዳሪ አልባ ጀግና የጦር መሪዎች የአለም ልእለሀያል የነበረውን የባይዛንታይን ሮም ስርወመንግስት ስብርብር አድርገው የቱርኮች የኢስላም ገባሪ አደረጉት። ከሰልጁቆች ጎሳ #ከኪኒክ የሚመዘዘው የሰልጁቆቹ ጦር መሪ #አቲሲዝ_ቤይ ባይዛንታይኖችን አንኮታኩቶ ዳግም ቁድስ ነፃ አወጣት። አላህ ዲኑን በማን እንደሚረዳው ይአጅባል። ገና ከሰለሙ ጥቂት አመታትን ያስቆጠሩት ሰልጁቅ ቱርኮች የኢስላም ቅዱስ ከተሞችን በሙሉ አስመልሰው ከቻይና እስከ ሮም ያሉ የኢስላም ጠላቶችን በጉልበቶቻቸው አንበረከኳቸው። በሃያሎቹ ወራሪዎች የሰልጁቆች የአባሲድና የኸዋርዚም ሙስሊም መንግስታቶች ሲደመሰሱ አሁንም ዳግም አውሮፓዊያን ተባብረው "የመስቀል ጦርነት" በሙስሊሞች ላይ አወጁ። ሁሉንም የአውሮፓ መንግስታት ባካተተውና በጳጳስ ክሊመንት በተባረከው በዚህ ጦርነት ሙስሊሞች እንደ ቅጠል ረገፉ! ኢየሩሳሌምን ( ቁድስ ) የሰው ደም ሀይቅ ሆኖ ተንጣለለባት። ህፃናት አዛውንት ሳይሉ ፣ ሴት ደካማ ሳይሉ መስቀላዊያኑ ሁሉንም በሰይፋቸው አረዷቸው። ቁድስም ዳግም በጭራቆች እጅ ገባች። ቁድስን ዳግም ማስመለስ የአንድ በአሁኗ የኢራቋ ቲክሪት ከተማ የተወለደ ኩርዳዊ ሙጃሂድ ተራ ሆነ። ያ ሙጃሂድ የሙጃሂድ ልጅ ሰላሁዲን አልአዩቢ ይባላል። ሰላሁዲን በሰልጁቅ የጦር መሪ በነበረው በኢማዱዲን ዘንኪ ልጅ በኑረዲን ዘንኪ አመራር ስር ሆኖ በወታደራዊ ክህሎት ተኮትኩቶ በኡለሞች ተርቢ ታንፆ አደገ። አባቱ ሰላሁዲንን ከልጆች ጋር ሲጫወት ባገኘው ጊዜ ብድግ አደረገና ፍርጥ አደረገው። እና ተቆጣው ሰደበው "እኔ አድገህ ቁድስን ታስመልሳለህ እያልኩ አንተ እዚህ አቧራ ታቦናለህ?" አለው። ሰላሁዲን አላለቀሰም። ለምን እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃልና።

ሰላሁዲን ቁድስን ነፃ ሳያወጣ በፊት ስቆ አያውቅም ተደስቶ አያውቅም። ያ የአሏህ ወልይ በቱርኮች ጥምረት መላው የአውሮፓ መስቀላዊ ጦርን ደምስሶ ኢየሩሳሌም ( ቁድስን ) ዳግም ነፃ አወጣ።

ከዚያ በሗላ በግብፅ የነገሱት ቱርኮቹ ማምሉኮች ተረክበው ኢየሩሳሌምን ጠብቀው አ hiቆዩ።

ከነርሱ በሗላ የአለማችን የምንጊዜውም ሀያሉ ኢምፓየር የሚሰኘው የኦቶማን ኺላፋ ( ደውለቱል ኡስማኒያ ) ቦታውን ተክቶ በየትኛውም የአለም ጫፍ ያለን የኢስላም ሉአላዊነት ሳያስደፍር ለ 500 አመታት ቀጥ አድርጎ ገዛ። ያኔ እንኳንስ ቁድስንና ትሪፖሊን እንኳ ማጥቃት የኦቶማኖችን ጀሃነም ያስከትላል። አውሮፓን በእንብርክኳ ያስኬዳት ፣ ሩሲያን ወገቧን የሰበራት ያ የኦቶማን ኺላፋ እስከ ውድቀቱ መጨረሻ ድረስ ቁድስን መካንና መድናን ለጠላት አሳልፎ አልሰጠም ነበር!

#አሁን_ቁድስ ከአንደኛው የአለም ጦርነት በሗላ #በክርስቲያን_አይሁዳዊያን ጥምረት ስር ነች። እነሆ ቁድስ ማንባት ከጀመረች ድፍን አንድ ክፍለዘመን ሊሞላት ነው።

እና ከዚያ ሁሉ ጨለማ የወጣች ቁድስ አላህ አሁን ሌላ ሰላሁዲን ፣ ሌላ አቲሲዝ ቤይ ፣ ሌላ አልፕ አርስላንን አይልክላትም ብላችሁ ታስባላችሁ??? በፍፁም አታስቡ !

ወድቆ መነሳት ፤ ጨለሞ መብራት የቁድስ ተፈጥሮዎች ናቸው !

ቁድስን አንድ ጊዜ አረቦች ፣ 3 ጊዜ ቱርኮች አንድ ጊዜ ኩርዶች ነፃ አውጥተዋታል ! አሁንስ እነማን የነፃነት ሰንደቁን ይዘው ቁድስን ነፃ ያወጡ ይሆን? ሁሉንም ጊዜ ያሳየናል! ግና አትጠራጠሩ ቁድስ ነፃ ትወጣለች።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group