UMMA TOKEN INVESTOR

3 months Translate
Translation is not possible.

የኡመቱ ችግር በጥቃቅንና በሱናዎች ግሩፕ ይዞ ሲለያይ ያሳዝናል

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ወጣትነቴን አገኘሁ በናንተ ሰበብ፡፡ (ከሪም)

ክፍል 3

 ከዚህ በፊት ተመርምራ ሲህር እንዳለ በትዳሯ ላይ እንዳወቀች ነገረችኝ፡፡ ማነው እንደዚህ ያለሽ አልኳት ፡፡ አዳማ ሂዳ ነበር ምርመራ የተደረገላት አንድ ሰውዬ ሙስባሃ እየቆጠረ አውራ ጣቷን አይቶ ነው የነገራት፡፡ ለሱም የሰጣትን መድሃኒት ነገረችኝ፡፡ 

በህይወቴ ሰው መትቼ ቀርቶ ተቆጥቼ አላውቅም፡፡ እንዴት እንደተበሳጨሁ አላውቅም በጥፊ አጮልኳት እንዴት ጠንቋይ ጋር ትሄጃለሽ አልኳት፡፡ ሙስሊም ናቸው አለችኝ፡፡ አይደሉም አልኩ ተከራከርኳት ብዙ ነገሮችን ስጠቁማት ተጣልተን ስለነበር በግዜው ዝም ብትልም በሁለተኛው ቀን ይቅርታ አለች ተውበትም አደረገች፡፡ 

በዚህ መሃል ለኔ ሳትነግረኝ እናንተ ዘንድ ህክምና ጀምራ ነበር፡፡ በሷ ላይ በጣም የሚገርም ለውጥ አይባት ነበር፡፡ ፊት የሆነ ነገር ስላት ብስጭት የሚያደርጋት አሁን ትመክረኝ ጀመር፡፡ እኔ ላይ እያሾፈች ነው ብዬ መልሼ ላናድዳት ያልፈጠረብኝን አውቄ ሳናዳት እሷ በጣም ትረጋጋብኝ ነበር፡፡ በተለይ በጣም ስልኳ ላይ ግዜ ታሳልፈፋለች፡፡ 

በሌላ ነገር እንዳልጠረጥራት ደግሞ ማታ ላይ ኪታብ ትቀራለች ሰላቷን ትሰግዳለች፡፡ ግንኙነት ላይ እንደበፊቱ አታስጨንቀኝም በፍቅር ነው የምናደርገው፡፡ በፊት  እኔ መውለድ እፈልጋለሁ ነበር ጭቅጭቃችን አሁን ግን ናፍቀሀኛል ትለኝ ጀመረ፡፡

 የሆነ ሰው መክራት ነው ብዬ በጣም ገርሞኝ ትቼዋለሁ፡፡ አሁን የሆነ ቀን ህልም አየች በጣም ያስጨነቃትን ህልም ፡፡ እና ስለዛ ህልም ነግራኛለች፡፡ ኅልሙ እኔንም በጣም አስገርሞኝ ስለነበር በውስጤ ይዤዋለሁ፡፡

 ከዛንም በነጋታው ይሁን ብቻ አላስታውስም እኔ ሸሚዜን እየተኮስኩ እያለ ስለ ህልሟ አስታወሰችኝና ሰደቃ ብትሰጥ ግን የተሸለ ነው፡፡ አለች፡፡ እኔ ሰደቃ እሰጣለሁ ምንም ያጎደልኩት ነገር የለም አልኳት፡፡ አቃለሁ ግን የምትሰጠውለሚያቃቅሙህ ሳይሆን በትክክለ ለሚፈልጉ ሰዎች ነው፡፡ ይቀጥላል፡፡

ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇

https://t.me/Qallbdoc

ህክምና ለማግኘት👇

https://t.me/freeeeeeeeeeeere

👆

ህክምና ለማግኘት👇

https://t.me/UstazulQallb

👆

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ወጣትነቴን አገኘሁ በናንተ ሰበብ፡፡ (ከሪም)

ክፍል 2

ማንም ሰው እሱ ይሰራል እሱ ሃብታም ነው ሚለውን መቀበል አይሻም አይፈልግም፡፡ አልሃምዱሊላህ ይሄም አንዱ ኒእማ ነው፡፡ ወደናንተ ያመጣኝን አጋጣሚ ላጫውታችሁ፡፡ እኔ ለሶስተኛ ግዜ ማግባት ነበረብኝ ቤተሰብን ጫጫታ ለመቀነስ በተለይ እህቶቼ በጣም ነው የሚጨነቁልኝ፡፡ እነሱ ላይ እንዳልወድቅ ሴት ካላገባህ ይሉኛል፡፡

እኔ የራሴ ሁለት ሰራተኞች አሉ፡፡ ከዛ ውጭ ምንም አልፈልግም ስላቸው አንዳንዴ እንደውም ምናልባት ወንድ እወድ ይሆን ብለው ጠርጥረው ነበር፡፡ እኔ ግን ይህን ሃሳብ ሲያነሱ ደንግጬ ሰድቤያቸዋለሁ፡፡ በፍጹም ለተመሳሳይ ፆታ ፍላጎት የለኝም፡፡

ከዛንም በዚህ ምክንያት በቃ አግባ ሶስተኛ ብለው አንዲት አላህ ወደዳትን ሚስት ሰጠኝ፡፡ ከኔ በእድሜ በጣም ታናሼ ናት ገና ሩጣ ያልጠገበች፡፡ በሷ ምክንያት ተጠቅሜ የማላውቀውን መድሃኒት ቫያግራ እንድጠቀም ተገድጃለሁ፡፡ በፍጹም ሃቋን መጠበቅ አለብኝ ብዬ ስላሰብኩ፡፡

በሱ በኩል ምንም ችግር አልፈጠረብኝም፡፡ ግን ጤናዬ እንደፊቱ አይደለም፡፡ ቶሎ ቶሎ ይደክመኛል፡፡ ለጡሃራ ተነስቼ ስመጣ ጭንቀት ነው ምተነፍሰው፡፡ ውሃ ሲጠጣ ሰው ያልበዋል እኔ የምጠጣው ውሃ በአናቴ ላይ የሚፋላ ነው የሚመስለው፡፡

ከኔ ጋር የሚቅሙ ጓደኞቼ ወይም በኔ አጠራር አቃቃሚዎቼ እራሳቸው ሳይቀር ለጤናዬ ተጨነቁ፡፡ በዚህ መሃል ግን ቤታችን ውስጥ ነበረው ችግር በኔ ላይ ብቻ አይደለም፡፡ ባለቤቴን ለንደን ድረስ ወስጄ አስመርምሬ ህክምናዎችንም ተጠቅማለች፡፡ አንቺ መውለድ ትችያለሽ የርሱ ዘር ፍሳሽ ደካማ ነው አሏት፡፡ እኔ የኔን ለማዳበር ብዙ ነገሮችን ተጠቀምን፡፡

የቀረው የኔን እንቁላል ማዳበር ነው፡፡ ግን ከዛ በፊት ዶክተሩ ያለኝ እንዲህ ለመውለድ ሁሌ እንዲህ መዳበር ያስፈልገዋል፡፡ ላይሳካም ይችላል ብሎ አስጠነቀቀኝ፡፡

አላህዬ ብዙ ነገሮችን ሲሰጠኝ በዚህ ሊያሰቃየኝ ነው አልኳት ሚስቴን፡፡ እሷ ግን አታምንበትም አባባሌን፡፡ መውለድ እፈልጋለሁ አንተም መውለድ ትችላለህ ባንተ ላይ የሆነ ነገር ቢኖር እንጂ አል፡፡ ምን ማለት ፈልገሽ ነው አልኳት፡፡ ይቀጥላል፡፡

ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇

https://t.me/Qallbdoc

ህክምና ለማግኘት👇

https://t.me/freeeeeeeeeeeere

👆

ህክምና ለማግኘት👇

https://t.me/UstazulQallb

👆

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ወጣትነቴን አገኘሁ በናንተ ሰበብ፡፡ (ከሪም)

ክፍል 1

ምን ማለትሽ ነው ብዬ ነው ቀጥታ የናንተን ስም ስሰማ የሰደብኳት፡፡ በጣም ነው ስማችሁ የሚያስደነግጠው፡፡ ውስጥ ልብ ያስጮሃል ፍርሃት ይለቃል፡፡

በተለይ ለእንደኔ አይነቱ ችግር ላለበት ሰው ገና ስማችሁ መድሃኒት ይመስለኛል፡፡ እኔ እንዲህ በዋዛ በፈዛዛ ጫትን የመሰለ የህይወቴን ግማሽ አካል በናንተ ምክንያት እተወዋለሁ ብዬ በፍጹም አላስበውም ነበር፡፡ በጣም እቅማለሁ እቅማለሁ አይገልፀውም በቀን አንድ መኪና ጫት ውስጥ ቢከቱኝ የምጨርሰው ይመስለኛል፡፡ አልሃምዱሊላህ በዚህ ምክንያት ሁለት ምን የመሳሰሉ ሚስቶን ፈትቻለሁ፡፡

ሁለቱም ምክንያታቸው አልጋ ላይ አይችልም እንደሚሆን አልጠራጠርም ፡፡ ምክንያቱም አልጋ ላይ ስደርስ ብልቴን ማዘዝ የማልችልበት አጋጣሚ አለኝ ብችልም ቶሎ ልምሻ ሁኜ አፍራለሁ፡፡ እነሱ ግን ሽምግልና ላይ በቃኝ በቀኝ ብለው ከኔ ሸሹ ሰው ለምን ሚስቶችህን አትለማመጥም ይሉኝ ነበር፡፡

ሚስቶቼ ሁለቱም የቀድሞ ሚስቶቼ ማለት ነው ከኔ የራቁበት ምክንያት ብለው ያቀረቡት አይሰራም ጫት ነው ቀኑን ሙሉ የሚቅመቀው የሚል ነው፡፡ እኔ እንደ ሌላው በኒ አደም ለፍተህ ሰርተህ ኑር አልተባልኩም አንድ ስልክ ብቻ ይበቃኛል የ አመት ወጪዬን ለመሸፈን፡፡ ብዙ ቤቶች አሉ የድለላን ጣራ ነው የምሰራው ፡፡

አንድ ሁከት ስልክ ከደወልኩ የትኛውንም ሰው ከድህነት የሚያወጣ አቅም አላህ ሰጥቶኛል አልሃምዱሊላህ፡፡ ስቅም ሁሉም ነገር ግልፅ ብሎ ይታየኛል፡፡ ሁሉንም ነገር ማሰካት ማገጣጠም እችልበታለሁ፡፡ አልሃምዱሉላህ፡፡

ስለዚህ ነው የምቅመው፡፡ ፊት ወታደር ነበርኩኝ፡፡ ከዛ ከወጣሁ ኋላ በቃ ጫትን ቀን ለማሳለፍ ብዬ ጀመርኩት፡፡ እኔ ለጫት ካለኝ ሱስ የተነሳ ሁለት ሶስት ሰዎችን በጫት ስራ ላይ አቋቁሜ ይሀው በነፃ ነው የምቅመው፡፡ ብዙ ግዜ ግን ለሰዎችም ስለምገዛ ገንዘብ መውጣቱ አይቀርም፡፡

ጥዋት ደህና ቁርስ ከበላሁ ኋላ የሚያምረኝ ጫት ነው፡፡ እኔ ጠላት የለብኝም ያኝ ሰው ሁሉ በዚሁ ስለሚገምተኝ የማልረባ ሰው አድርጎ ነው የሚቆጥኝ፡፡ እናም ይህ ነገር ለኔ ጠቅሞኛል፡፡ ሃብትም ከ ቤተሰቤ የማገኝ ነው ሰው የሚመስለው፡፡ ይቀጥላል፡፡

ቻናላችንን ለኡማው ያስተዋውቁ 👇

https://t.me/Qallbdoc

ህክምና ለማግኘት👇

https://t.me/freeeeeeeeeeeere

👆

ህክምና ለማግኘት👇

https://t.me/UstazulQallb

👆

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አስቸካይ የትውልድ አድን ጥሪ🚨

ባሳለፍነው ህዳር 5 ቀን 2016 ዓም ኢትዮጵያን ጨምሮ ከአፍሪካ ከካሪቢያንና ከፓሲፊክ የተውጣጡ ሀገራት ለሚቀጥሉት 20 ዓመታት የሚቆይ የንግድና ኢኮኖሚ ትብብር ስምምነትን ከአውሮፓ ህብረት ጋራ ሳሞዋ በምትባል ሀገር በፈረሙ ወቅት አገራችን ኢትዮጵያም ይህንኑ ስምምነት ተቀማጭነታቸው ብራሰልስ በሆኑ አምባሳደV አማካኝነት በፊርማዋ አጽድቃለች፡፡ ይህ አደገኛ ይዘቶች ያሏቸውን አንቀጾች የያዘው ስምምነት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ከሚቀጥለው ጥር ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡

 

ይህ የትብብር ስምምነት በውሥጡ የያዛቸውን አስራ ሁለት ዋና ዋና አደገኛ ይዘቶችን ጠቅልለው የሚይዙ የተወሰኑ ሀሳቦች ለመጥቀስ ያህል ፡-

 

ሀ) የሀገር ሉዓላዊነትን የሚጥሱ አንቀጾች በግልጽ መቀመጣቸው፣

 

⭕️ለ) ግብረሰዶማዊነት፣ የጾታ መቀየርና፣¸ውርጃና ሁሉን አቀፍ የወሲብ ትምህርትን የመሳሰሉ እኩይ አጀንዳዎች በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በሌሎች አሳሳች ሀረጎች ተሰውረው የገቡበት መሆኑ፣

 

ሐ) ግብረሰዶማዊነት በርካታ ቀውሶች ማለትም በአካል፣ በሥነልቦናና በማህበራዊ ህይወት ላይ የሚያስከትልና ለሀገር ደህንነትም አደጋ መሆኑ፣

 

መ) የወላጆችን መብት የሚጥስና የኢትዮጵያዊ ቤተሰብ እሴቶችን የሚንድ መሆኑ፣

 

ሠ) የሀገራችንን ሀይማኖት፣ባህልና እሴቶች የሚንዱ ጸያፍ ልምምዶችን እንድንቀበል በሰብዓዊ መብት ሽፋንና በእርዳታ ስም የምንገደድበትና ለዘመናዊ ባርነት ወይንም ቅኝ አገዛዝ ታልፈን የምንሰጥበት መሆኑ፣

 

በአጠቃላይ ይህ አዲስ የአጋርነት ስምምነት ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡና ትውልድንና ብሎም ሀገርን እጅግ የሚጎዱ በርካታ አንቀጾች የተካተቱበት መሆኑ ለሀገራችን ህዝብ ዕድገትን ሳይሆን ውድቀትንና ከፍተኛ የሞራል ዝቅጠትን የሚያስከትል መሆኑን በሚገባ ተረድተናል፡፡

 

በተጨማሪም ከተጠበቀው ውጭ ሀገራችን ይህንን ስምምነት በመፈረJ የተጋረጠብንን እጅግ አሳሳቢ አደጋ ለመቀልበስ አስፈላጊ የሆኑ ሰላማዊና ህጋዊ መንገዶችን ሁሉ በመጠቀም መንግስት ትኩረትን እንዲሰጠው ማድረግ ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡

 

በመሆኑም ይህ የመንግስት ውሳኔ እንደገና ተጠንቶ ውሳኔው እንዲቀለበስ ማለትም ስምምነቱ አስፈላጊው ሁሉ ማስተካከያ እስኪደረግበት ድረስ ወይንም እጅግ አደገኛ የሆኑት አንቀጾች ተነቅሰው ወጥተው የማንቀበላቸው መሆናችንን በይፋ ማሳወቅ (Submission of an Interpretive Declaration) እስከምንችል ድረስ የምንወዳት ሐገራችን ኢትዮጵያ ፊርማዋን በመሰረዝ ከስምምነቱ ራሷን እንድታገልል በሐገራችን ከፍተኛው የሥልጣን አካል ለሆነው ለተከበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለሐገሪቱ መሪ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በታላቅ አክብሮት እጅግ አስቸኳይ ጥሪን እናደርጋለን፡፡

 

የዚህንም ስምምነት አደገኛ አንቀጾችንና በኤክስፐርቶች የተሰጠውን ትንታኔ የያዘ ዶኩመንት በአባሪነት ያቀረብን መሆናችንንም በታላቅ አክብሮት እንገልጻለን፡፡

Send as a message
Share on my page
Share in the group