UMMA TOKEN INVESTOR

Yehya Safoz shared a
Translation is not possible.

በሐማስ ወታደራዊ ክንፍ የዒዘዲን ቀሳም ብርጌዶች ቃል አቀባይ አቡ ኡባይዳ እንደተናገሩት

24 የእስራኤል ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን እንዳወደሙ በአፅንኦት ገልፀው "ተዋጊዎቻችን ከጠላት ኃይሎች ጀርባ መክበባቸውን ቀጥለዋል። ዜሮ ሰርተው እያጠቁ ነው።

ባለፉት ሁለት ቀናት በህንፃዎች ውስጥ በመሸጉ የጠላት ኃይሎችን በአል-ያሲን ዛጎሎች አውድመናል።

ሙጃሂዶቻችን በሰሜን ምእራብ በጋዛ በስተደቡብ በበይት ሀኑን ግንባር እየተዋጉ ነው።

የአልቀሳም ብርጌድ ቃል አቀባይ በኃይል የማይመጣጠን ጦርነት ውስጥ መሆናቸውን ጠቅሰው ለዓለም ትምህርት የሚሰጥና በታሪክ የማይሞት መሆኑን ሲገልፁ "ህዝባችን በጫካ ህግ በሚተዳደር አለም ቅጣት ስልታዊ በሆነ መንገድ እንዲጠፋ እየተደረገ ነው"

በተንቀሳቃሽ ምስሎች አስደግፈን የለቀቅነው ሙጃሂዶቻችን በጦር ሜዳው በጠላት ጦር ላይ ያደረጉትን ጀግንነት ትንሹን ክፍል ነው" ብለዋል።

ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን አዲሱን የፌስቡክ አካውንቴን ፎሎው አድርጋችሁ ተከታተሉኝ። ለሌሎች ወንድምና እህቶችም ሼር አድርጉልኝ።

https://www.facebook.com/profi....le.php?id=6155301438

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Yehya Safoz shared a
Translation is not possible.

#ሸይኽ ኢብን ባዝ ተጠየቁ ፡ ሙቅ ውሃን በምናፈስበት ጊዜ

ቢስሚላህ እንላለንን፣ ይህም ጂን ቦታው ላይ ይኖራል ብሎ

በመፍራት ነው

መልስ፡

"አዎን! ቢስሚላህ ይበል ምን አልባት ቦታው ላይ ጂን ካለ

እንዲነቃ ለማድረግ ነው" ከዛም ሽይኹ እንዲህ አሉ" በርግጥም

በአንድ ወቅት አንድን ሰው ጂን ይዞት በሚቀራበት ቦታ ተገኝቼ

ነበር

#ሩቃ የሚያደርገው ሰው በሰውየው ላይ ለተደበቀው ጂኒ "ለምን

ያዝከው "አለው

#ጂንውም "የሞቀ ውሃ በአንዱ ልጄ ላይ ደፋና ገደለው "አለ

#የሚቀራዉ ሰውዬ ደግሞ "እሱ ልጅህ በቦታው መኖሩን

ስላላወቀ ነው" አለው

#ጂኒው ደግሞ "ለምን ቢስሚላህ አይልም ነበር እንዲያሳውቀው

(እንዲያነቃው)"

#ሽይኽ ዘይድ አል መድኸሊ ረሂምሁሏህ እንዲህ አሉ ፡

"ለማንኛውም የሞቀ ውሃ በፍሳሽ ትቦዎችም ይሁን በመሬት ላይ

አይደፋም ምክኛቱም መሬት በነዋሪዎች የተሞላች ነች

ምናልባትም በጂኖች አለም ወይም በትንንሽ ፍጡሮች ላይ ያርፋል

በዚህም ለበቀል ይነሳሱና ይይዙታል።ስለዚህ አንድ ሰው የሞቀን

ውሃ መድፋት ከፈለገ በቀዝቃዛ ውሃ ቅዝቃዘው የማያስቸግር

እስኪሆን ያብርደውከዛም ከፈለገ የፍሳሽ ትቦዎች ውስጥ ከፈለገ

መሬት ላይ ያፍሠው" ንግግራቸው እዚህ ጋር አለቀ ረሂመሁሏህ.

፟፟=========================

#ጉዳዩ አደገኛ ነው ሙስሊሞች ሆይ ነቃ በሉ ለወንድሞቻችሁ

ለእህቶቻችሁ ለእናቶቻችሁ አድርሱላቸው ስንትና ስንት እህቶች

በዚህ ሰበብ ችግር ውስት ይገባሉ ፓስታ የቀቀሉበትን ውሃ

አውጥተው በመድፋት ስንቱ ተለክፎዋል ስለዚህ አድርሱላቸው!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Yehya Safoz shared a
Translation is not possible.

ፊትን በአማኢም መሸፈን የጀግንነት ምልክት ነው። ለዘመናት የተሻገረ የሙስሊም ሙጃሂዶች ልብስ

አብዛኞቹ ሰሐቦች ወደ ጦር ሜዳ ሲገቡ ይጨነበላሉ። ዙበይር በቢጫ አቡ ሐምዛና ሚህጀንም በቀይ ጥምጥም ፊታቸውን ይሸፍኑ ነበር። ማነው አቡ ሚህጀን?!

እርሱ የአላህንና የነቢን ጠላት በማሸበር ወደር ያልተገኘለት ጀግና። ወደ ጦር ሜዳ ሲገባ ጭንቅላቱ ላይ የሚጠመጥማት ቀይ አማይማን የተመለከተ ከሐዲ በፍርሐት ይርዳል። አንድ መሰረታዊ ችግር ግን ነበረበት። ሁሌም ይጠጣል። ጭንብስ ብሎ ይሰክራል። የአላህን ህግ በተደጋጋሚ እየጣሰ አስቸግሯልና በአደባባይ ብዙ ጊዜ ተገርፏል። ከዚህ ተግባሩ ባለመላቀቁ በእግረ ሙቅ ተጠፍሮ በግዞት ወደ እስር ቤት ተወርውሯል።

ዕለቱ የቃዲሲያ ዘመቻ ወቅት ነበር። አቡ ሚህጀን የታሰረው ጦርነቱ ከሚካሄድበት ቦታ ብዙም አይርቅም። የፈረሶችን ማሽካካት የሰይፍ ግጭቶችና የተክቢራ ድምፆችን ሲሰማ መታሰሩን አምርሮ ጠላ። ከተጋጋለው ጦር ገብቶ የአላህን ጠላቶች አንገት በሠይፍ መሸልቀቅን በእጅጉ ናፈቀ። ከአይኖቹ እንባን እያረገፈ ውስጡ ክፉኛ ተረበሽ። የጂሃድ ናፍቆት እንደነበልባል እያንገበገበ አላስችል ቢለው የታሰረበትን ክፍል በር ደብድቦ ለጦር መሪው ሚስት መልዕክትን ላከ። እንዲህም አላት "ካቴናዬ ተፈቶ የጦር መሳሪያና ፈረስ አዘጋጅተሽ የናፈኩትን ጂሃድ እንድካፈል አድርጊኝ። እባክሽ እፋለም ዘንድ እርጂኝ። በህይወት ከተረፍኩ ራሴ መጥቼ የእስር ቤቱን በር በላዬ ላይ እከረችማለሁ" አላት።

ንግግሩን ስትሰማ አዘነች የመጣው ይምጣ ብላ በራሷ ወሰነች። ፈረስና ሠይፍ ሰጥታ ለቀቀችው። አቡ ሚህጀን ፊቱን በጨርቅ ሸፍኖ ከጦር ሜዳው መሐል ሰፈረ። የአላህ ጠላቶች የበላይነትን ለመቆጣጠር ቀርበዋል። የሙስሊሙ ጦር ተዳክሟል። በዚህ ቅፅበት አቡ ሚህጀን ከመሐላቸው ተከሰተ። አንዱን በአንዱ ላይ አነባበረ። ድል ወደ ሙስሊሞች ማዘንበል ጀመረ። አቡ ሚህጀን የአላህንና የሙስሊሙን ጠላቶች አረገፋቸው። ከፊቱ የቀረበን የጠላት ጦር አንገቱን ቀንጥሶ መሬት ላይ እየጣለ፣ ያገኘውን እየገነዳደሰ ወደመሐል ገሰገሰ።

የጦር መሪው ሰዕድ የዚህን ተዋጊ ገድል እየተመለከተ ነው። እንዲህ በፅናት የአላህን ጠላቶች አመድ የሚያደርገው ማን ነው ሲል ይጠይቃል። የሚያውቀው ሰው ጠፋ። አቡ ሚህጀን ነው እንዳልል እሱን አስሬዋለሁ ይላል።

ጦርነቱ በሙስሊሞች ድል አድራጊነት ሲጠናቀቅ ወደ እስር ቤቱ ተመለሰ። እነዛን በጦርነት የደከሙ እግሮቹንና እጆቹን በካቴና ጠፍሮ አሰራቸው። ሰዕድ ወደ ቤት ሲመለስ ሚስቱ ውሎውን ጠየቀችው።

ሰዕድም የሽንፈት ማቅ ልንከናነብ በተቃረብንበት ወቅት አላህ አንድ ልዩ ተዋጊ ላከልን። ያ የመነመነ የድል ተስፋ ተቀልብሶ ለማሸነፍ በቃን። አቡ ሚህጀንን አስሬው ባልሄድ ኖሮ ያ ጀግና ተፋላሚ እሱ ነው ብዬ እጠረጥር ነበር። የጦር ስልቱ የእሱን ይመስላል በማለት ተናገረ።

ሚስቱም በአላህ ይሁንብኝ እራሱ አቡ ሚህጀን ነው ብላ የተከሰተውን አስረዳችው። በሁኔታው በእጅጉ የተደሰተው ሰዕድ አቡ ሚህጀንን አስጠርቶ ከዛሬ ጀምሬ አልገርፍህም። አላስርህም በነፃ ለቅቄሀለው አለው።

አቡ ሚህጀንም እንግዲያውስ እኔም ከዛሬ ጀምሬ አልጠጣም አልሰክርም በማለት መለሰ።

ረድየላሁ አንሁም አጅመዒን

#mahi mahisho

ቴሌግራም

👇👇👇

t.me/yesheh_kalidrashid_daewawoch

ኡማ ላይፍ

👇👇👇

https://ummalife.com/mahimahisho

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Yehya Safoz shared a
Translation is not possible.

#አስቸኳይ_ሼር || የእዝራኤልን ምርቶችን መጠቀም ፍልስጢን ላይ ቦንብ እንደመወርወር ነው ‼️#baycot

በሀገራት መካከል በሚደረግ ጦርነት ከቀጥተኛው ውጊያ በላይ የኢኮኖሚ እቀባው ምርት እና አገልግሎታቸውን አለመጠቀም ትልቁ ጦርነት ነው።

ሁላችነም ሰብዓዊነት የሚሰማን የፍልስጢን ወገኖች ሞ**ት ስቃይ እና እንግልት የሚያመን እነዚህን የእዝራኤል ምርቶችን ባለመግዛት እና ባለመጠቀም የበኩላችነን እንወጣ።

ይህ በትንሹ የምናግዘው እና የምናሳየው አጋርነት ነውና ለሁሉም እንድደርስ #ሸር_እናድርገው

Follow & share share

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Yehya Safoz shared a
Translation is not possible.

በባንኮች ውስጥ ገንዘባችሁን የምታስቀምጡ ወገኖች በጣም ጥንቃቄ አድርጉ። በተለይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደንበኞች ከነ ጭራሹ ሳያውቁ ከአካውንታቸው የሚፈፀመው ዘረፋ ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ ነው ያለው። ባንኮች ከአንድ ደንበኛቸው ሂሳብ የተወሰደ ገንዘብ እንዴት ወደየትኛው ሂሳብ እንደገባ እንደማያውቁ ወይም እንዴት የገባበትን እያወቁ ማስመለስ እንደማይችሉ በጣም ግራ የሚያጋባ ነው።

ለማንኛውም በየጊዜው ገንዘባችሁ መኖሩን አስረግጡ። በተለይ ሙስሊሞች በብዛት እየተዘረፉ ነው። ከዚያ አመልክቱ ይባላሉ። እስካሁን ድረስ የተወሰደበት እንጂ ተወስዶበት አመልክቶ የተመለሰለት መኖሩን አላውቅም። ብትችሉ እነሱ ዘንድ ከማስቀመጥ ንብረት ላይ ወይም ስራ ላይ አውሉት።

Ibnu Munewor

=

የቴሌግራም ቻናል፡-

https://t.me/IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

كناشة ابن منور
Send as a message
Share on my page
Share in the group