UMMA TOKEN INVESTOR

About me

አልሀምዱሊላህ

Translation is not possible.

..አፄዎቹን የምትጠላው ካሀዲያን ስለነበሩ፣ ላኢላሃኢለላህ ያለችን ነፍስ ሲያጠፉና ኢስላምን ሲዋጉ ስለነበር ከሆነ አጂር አለህ! የዐቂዳ ምሰሶ የሆነውን ወላእ እና በራእም አረጋግጠሃል ‼ የምትጠላቸው ለብሄራቸው ከሆነ ግን አንተ በርግጥም በጃሂሊያ አረንቋ ውስጥ የሰመጥክ ቁረይሺይ ነህ‼

መልእክተኛው ﷺ እንዲህ ብለዋል ፦ « ለአላህ ሲል የወደደ ለአላህ ሲል የጠላ ለአላህ ሲል የሰጠና ለአላህ ሲል የከለከለ በርግጥም እርሱ ኢማንን አሟልቷል » (አቡዳውድ)

Ismile nuru

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

.✍

አንደሉስ ሲከፈት የሙስሊም ሰራዊቶች

አስራ ሁለት ሺህ ነበሩ ተባለ;

አንደሉስ ስትወድቅ ግን በውስጧ በሚሊየን የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ነበሩ።

ቁም ነገሩ፦ የኢማን ጥንካሬ እንጂ

የቁጥር ብዛት አ ይ ደ ለ ም!!

منقول

አሏህ ሆይ ጠላትን የሚያሸብር ኢማን 🤲

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

.ኢማም አልጁነይድ ( ረ ዐ) ...

"መከራ ( በላእ) .... የአላህ ቅጣት ወይስ ወንጀል ማበሻ ወይስ ወደሱ ከፍታ ነው ? ተብለው ተጠየቁ ...

እሳቸውም ....

" በውሳኔው ከተበሳጨህ ቅጣት ነው ፣ ከታገስክ ወንጀል ማበሻ ነው ፣ ከወደድክ ከፍታ ነው ‼ " አሉ ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

.የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«በጁምዓ ሌሊትና በጁምዓ ቀን በእኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ ፣ በእኔ ላይ አንድ ሰለዋት ያወረደ አላህ በእርሱ ላይ አስር ሰለዋት ያወርድለታል።»

አልባኒ ሀዲሱን "ሐሰን" ብለውታል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
6 month Translate
Translation is not possible.

ጋጠ ወጥነት ይህ

ሰበካ ሳይሆን የሰዎችን መብትና ነፃነት መጋፋት ነው‼

==============================

✍ ባለፈ ጦር ኃይሎች አካባቢ የተወሰኑ ወጣቶች የማንንም መብት ሳይጋፉ የመንገድ ላይ ዳዕዋ ጀምረው ነበር። ግን ወዲያው ለእስር ተዳረጉና በዛውም ማሸማቀቂያና ማስፈራሪያ ተደረገባቸው።

በየታክሲው ሰልፍና በመስጂዶች ዙሪያና በሙስሊሞች ሰፈር ሳይቀር እየዞሩ ከባድ የድምፅ ማጉያና ሞንታሪቦ ተጠቅመው ሰዎችን ማደንቆራቸው አንሷቸው፤

ይሄው እንደ ሐድያ ሆሳና ባሉ አካባቢዎች በህብረት የተደራጁ ሰባኪ ተብዬ ወንበደዎች እኚህን በእድሚያቸው የገፉ ሙስሊም አባታችንን ከበው በግድ እስልምናን ለቀህ የእኛን እምነት ካልተከተልክ እያሏቸው ነው።

ነውር ነው! እጅግ ሲበዛ ዓይን ያወጣ ስግጥና!

እነዚያ ሰላማዊ ሙስሊምን ከመንገድ ላይ አፍሰው የሚያስሩ የጸጥታ አካል ተብዬዎች እንዲህ አይነቶቹን ወንበዴዎች ተጠያቂ ያደርጉ ይሆን?

በተለይም ደቡብ አካባቢ እንደዛ የሚያደርጉ አይመስለኝም። እንዳውም አብረው ሲያጅቡና አዳራሽ ገብተው ሲደንሱ ነው የምናውቀው። ይሄ ነገር ገደብ ካልተበጀለትና ከወዲሁ በቃ ካልተባለ ቀስ በቀስ ከዚህ በከፋ ደረጃ ላይ ሊደርስ ይችላል።

የኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ተብዬው የአንድ እምነት ተቋም፤ ሙስሊሞች ዳዕዋ ሲጀምሩ እንደሚንጨረጨረው ሁሉ እንዲህ አይነት ጋጠ ወጦችን ያወግዝ ይሆን?

የምናየው ይሆናል! ይህንን እምነትን በአደባባይ አስገድዶ የማስለቀቅ ተግባር ሁሉም ሰው ሊኮንነው ይገባል።

የሚመለከተው አካል በነዚህና መሰል አካላት ላይ ተገቢውን እርምጃ ሊወስድ ይገባል። የዚያ አካባቢ እስልምና ጉዳዮችም ተነጋግራችሁ ጉዳዩን ወደ ፍርድ አቅርቡትና ፍትሕ ካለ መቀጣጫና ለሌሎችም ማረሚያ እንዲሆኑ ይደረግ።

||

t.me/MuradTadesse

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group