UMMA TOKEN INVESTOR

Reyhana Abdela قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

ፍልስጥኤም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥251 "በአላህም ፈቃድ ድል መቷቸው፥ ዳውድም ጃሉትን ገደለ"፡፡ فَهَزَمُوهُم بِإِذْنِ اللَّهِ وَقَتَلَ دَاوُودُ جَالُوتَ

"ፊልሥጢን" فِلَسْطِين ማለት "ፍልስጥኤም" ማለት ሲሆን በአንድ ወቅት የፍሊሥጢን ንጉሥ "ጃሉት" جَالُوت ማለትም "ጎልያድ" እና ሠራዊቱ ከጧሉት ማለትም ከሳኦል ሠራዊት ተዋግተዋል፦

2፥249 ጧሉትም በሠራዊቱ ታጅቦ በወጣ ጊዜ፡- «አላህ በወንዝ ፈታኛችሁ ነው፥ ከርሱም የጠጣ ሰው ከእኔ አይደለም፡፡ ያልቀመሰውም ሰው በእጁ መዝገንን የዘገነ ሰው ብቻ ሲቀር እርሱ ከእኔ ነው» አለ፡፡ ከእነርሱም ጥቂቶች ሲቀሩ ከርሱ ጠጡ፡፡ እርሱ እና እነዚያም ከእርሱ ጋር ያመኑት ወንዙን ባለፉት ጊዜ፡- «ጃሎትን እና ሠራዊቱን በመዋጋት ለኛ ዛሬ ችሎታ የለንም» አሉት፡፡ እነዚያ እነርሱ አላህን ተገናኝዎች መኾናቸው የሚያረጋግጡት፡- «ከጥቂት ጭፍራ በአላህ ፈቃድ ብዙን ጭፍራ ያሸነፈች ብዙ ናት፤ አላህም ከታጋሾች ጋር ነው» አሉ፡፡ فَلَمَّا فَصَلَ طَالُوتُ بِالْجُنُودِ قَالَ إِنَّ اللَّهَ مُبْتَلِيكُم بِنَهَرٍ فَمَن شَرِبَ مِنْهُ فَلَيْسَ مِنِّي وَمَن لَّمْ يَطْعَمْهُ فَإِنَّهُ مِنِّي إِلَّا مَنِ اغْتَرَفَ غُرْفَةً بِيَدِهِ ۚ فَشَرِبُوا مِنْهُ إِلَّا قَلِيلًا مِّنْهُمْ ۚ فَلَمَّا جَاوَزَهُ هُوَ وَالَّذِينَ آمَنُوا مَعَهُ قَالُوا لَا طَاقَةَ لَنَا الْيَوْمَ بِجَالُوتَ وَجُنُودِهِ ۚ قَالَ الَّذِينَ يَظُنُّونَ أَنَّهُم مُّلَاقُو اللَّهِ كَم مِّن فِئَةٍ قَلِيلَةٍ غَلَبَتْ فِئَةً كَثِيرَةً بِإِذْنِ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ مَعَ الصَّابِرِينَ

ከዚያም በጦርነቱ ተፋልመው ተስፋ በቆረጡ ጊዜ ዳውድ ጃሉትን ገሎታል፦

2፥250 ለጃሉት እና ለሠራዊቱ በተሰለፉም ጊዜ፡- «ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ትዕግስትን አንቧቧ፤ ጫማዎቻችንንም አደላድል፤ በከሓዲያን ሕዝቦችም ላይ እርዳን» አሉ፡፡ وَلَمَّا بَرَزُوا لِجَالُوتَ وَجُنُودِهِ قَالُوا رَبَّنَا أَفْرِغْ عَلَيْنَا صَبْرًا وَثَبِّتْ أَقْدَامَنَا وَانصُرْنَا عَلَى الْقَوْمِ الْكَافِرِينَ

2፥251 "በአላህም ፈቃድ ድል መቷቸው፥ ዳውድም ጃሉትን ገደለ"፡፡ فَهَزَمُوهُم بِإِذْنِ اللَّهِ وَقَتَلَ دَاوُودُ جَالُوتَ

ቁርኣን ላይ ስለ ፍልስጥኤማውያን የሚናገረው እነዚህ አናቅጽ ላይ ነው። ሚሽነሪዎች፦ "ፍልስጥኤማውያን ፍልስጥኤም የምትባል አገር የላቸውም" እያሉ ባላነበቡት ነገር ይዘባርቃሉ። ፈጣሪ እስራኤልን ከግብጽ ምድር እንዳወጣ ሁሉ በጥንት ጊዜ ፍልስጥኤማውያንንም ከከፍቶር አውጥቶ የራሳቸው ግዛት ሰቷቸዋል፦

አሞጽ 9፥7 እስራኤልን ከግብጽ ምድር፥ ፍልስጥኤማውያንንም ከከፍቶር፥ ሶርያውያንንም ከቂር አላወጣሁምን?

ኢዮኤል 3፥4 ጢሮስና ሲዶና የፍልስጥኤምም ግዛት ሁሉ ሆይ! ከእናንተ ጋር ለእኔ ምን አለኝ? በውኑ ብድራትን ትመልሱልኛላችሁን?

"የፍልስጥኤምም ግዛት" የሚለው ይሰመርበት ፍልስጥኤም ግዛት ከነበረች ለምን መብቷ አይከበረም? እስራኤላውያን ቦታቸው መጥተው ሰፈሩባቸው እንጂ ጥንትም ቢሆን የእስራኤል ቅም አያት አብርሃም ከከላዳውያን ኡር በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀምጧል፦

ዘፍጥረት 21፥34 "አብርሃምም በፍልስጥኤም ምድር ብዙ ቀን እንግዳ ሆኖ ተቀመጠ"።

ፍልስጥኤም መጤ ሳትሆን የራሷ ምድር ስለሆነ "በፍልስጥኤም ምድር" የሚል ኃይለ-ቃል ተጽፏል። ባይብል ላይ ብዙ ቦታ "የፍልስጥኤም ምድር" እያለ ይናገራል፦

ኤርምያስ 25፥20 የተደባለቀውንም ሕዝብ ሁሉ፥ የዖፅ ምድር ነገሥታትንም ሁሉ፥ "የፍልስጥኤም ምድር" ነገሥታትንም ሁሉ አስቀሎናንም ጋዛንም አቃሮንንም የአዞጦንንም ቅሬታ"።

ዘጸአት 13፥17 እንዲህም ሆነ ፈርዖን ሕዝቡን በለቀቀ ጊዜ፥ ምንም ቅርብ ቢሆን እግዚአብሔር "በፍልስጥኤማውያን ምድር" መንገድ አልመራቸውም።

ፍልስጥኤማውያን የራሳቸው አገር አላቸው፥ እስራኤላውያን የሰፈሩበት ከነዓን ሁሉ ሳይቀር የፍልስጥኤማውያን ምድር ነው፦

2ኛ ነገሥት 8፥2 ሴቲቱም ተነሥታ እንደ እግዚአብሔር ሰው ቃል አደረገች፤ ከቤተ ሰብዋም ጋር ሄዳ "በፍልስጥኤም አገር" ሰባት ዓመት ተቀመጠች"*።

ሶፎንያስ 2፥5 "የፍልስጥኤማውያን ምድር ከነዓን ሆይ"፥ የእግዚአብሔር ቃል በአንተ ላይ ነው።

ዛሬ አገር እና ግዛት እንደሌላቸው እና መጤ እንደሆኑ ታይቶ እየተፈናቀሉ ነው፥ አሏህ ነስሩን ያቅርብላቸው! አሚን። ይህንን የምንለው ስለ ሐቅ እና ስለ ፍትሕ ነው፥ "ኢሥላም ሰም እና ወርቅ የያዘ ቅኔ ነው፥ ሰሙ ሐቅ ሲሆን ወርቁ ፍትሕ ነው" ስንል ዕውር ድንብ ጸለምተኛ ሙግት ይዘን ሳይሆን ጠቅሰንና አጣቅሰን በመሞገትና በመሟገት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ወሠላሙ ዐለይኩም

أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
Reyhana Abdela قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

አሁናዊ አጫጭር መረጃዎች:

▶️በቱርክ ፕሬዚደንት ውስጥ የደህንነት እና የውጭ ፖሊሲ ኮሚቴ አባል አል-ኑር ሻፊቅ እንደገለፁት የቱርክ ፕሬዝዳንት እስራኤልን በአለም አቀፍ ህግ ለመክሰስ ህጎችን እየገመገመ ነው ያሉ ሲሆን፣አሜሪካም ካለቅድመ ሁኔታ ለእስራኤል በሰጠችው የጦር ድጋፍ ጥፋተኛ ነች ብለዋል።

▶️ሃማስ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ ሰብአዊ ሚና ያላቸውን ሆስፒታሎች ለመጠበቅ ሁሉም ሀገራት እና አለም አቀፍ ተቋማት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስዱ እንጠይቃለን በማለት ጥሪ አስተላልፏል።

▶️የእስራኤል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እንደዘገበው የእስራኤል የመንገደኞች አይሮፕላን እንዳያርፍ በመቃወም የዳግስታን ዜጎች ወደ ማካችካላ አውሮፕላን ማረፊያ ሲገቡ የሚያሳዩ ምስሎችን አሳትሟል።

▶️የሩስያ ሚዲያ እንደዘገበው የእስራኤል የመንገደኞች አውሮፕላን በማካችካላ ካረፈ እና ተቃዋሚዎች ከወረሩት በኋላ የዳግስታን ባለስልጣናት የዋና ከተማይቱን ማካችካላ አየር ማረፊያ ለመዝጋት መገደዳቸውን ዘግቧል።

(NB:ዳግስታን“የተራሮች ምድር”የሚል ትርጓሜ ያለው በሩሲያ ሰሜን ካውካሰስ የሚገኝና የሩስያ አካል ከሆኑት 22 ሪፐብሊኮች አንዱ ሪፐብሊክ ግዛቶች አንዱ ሲሆን፣በምዕራብ ከቺቺኒያ እና ከጆርጂያ ጋር ፣በደቡብ ከአዘርባጃን እና በምስራቅ ከካስፒያን ባህር ጋር ይዋሰናል።

የዳግስታን ህዝብ ብዛት 3,209,800 ሲሆን ከ83% በላይ ህዝቦቹ የሱኒ ሙስሊሞች ናቸው።)

▶️የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ የሀማስን የጋዛ ሀላፊ የህያ ሲንዋርን እስከምንገድል ወይንም እስከምንማርክ ድረስ ወደጋዛ ዘልቀን እንገባለን፣በጋዛ ያለውን የሰራዊታችንን እንቅስቃሴም አናሳውቅም ብሏል!

Umma1698005714

أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
Reyhana Abdela قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

ጦርነቱን ሐማስ ነው የጀመረው ብለው ለሚወቅሱ ሰዎች የተሰጠ መልስ በትርጉም!

الشيخ عثمان الخميس

14 وجهات النظر
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
Reyhana Abdela قام بمشاركة
7 شهر ترجم
لا يمكن الترجمة

😭😭

8 وجهات النظر
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
Reyhana Abdela قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

« የተራበቡ ሰዎች በሰሃን ወደ ቀረበው ምግብ ሊበሉ አንደሚሰባሰቡት(እንደሚጠራሩት)  ጠላቶች በናንተም ላይ ይጠራሩባቹሃል!»

ከሶሃቦች መካከልም የአላህ መልእክተኛ ሆይ እንዲህ የሚተባበሩብን ያን ግዜ እኛ በቁጥር አናሳ ስለሆንን ነውን?

ረሱሉም « እንደውም ያኔ ብዙ ናችሁ ነገር ግን ጎርፍ ሰብስቦ እንደሚያመጣው የተበታተናችሁ ግሳንግስ ናችሁ!  አላህም ጠላቶቻችሁ እናንተን የመፍራትን ግርማ ያነሳላቸዋል በናንተ ልብ ውስጥ "ወህን" ን  ይጥልባቹሃል! አሉ

ሶሃቢዪምየአላህ መልእክተኛ ሆይ ወህን ምንድነው?  ብሎ ጠየቃቸው

ረሱሉም ወህን ማለት « ዱንያን መውደድና ሞትንም መጥላት ብለው መለሱ »

(صحيح أبي داود 4297)

አንዋር ኺያር

image
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة