UMMA TOKEN INVESTOR

Ye hnatu Lej shared a
Translation is not possible.

በአንድ ወቅት በአውሮፓ አየር መንገድ የመጀመሪያ ደረጃ ክፍል

(Buisness Class) ውስጥ የተቀመጠ አንድ ሙስሊም ወጣት

ተሳፋሪ ነበር፡፡

በጉዞ ላይ ሳለ ከአውሮፕላኑ አስተናጋጆች አንዷ ለዚህ ሙስሊም

ወጣት የነፃ መጠጥ ይዛለት መጣች፡፡

መጠጡ የአልኮል መጠጥ ስለነበረ ሙስሊሙ ወጣት

አልተቀበለም፡፡

አስተናጋጇም ከመጠጫው ችግር ይሆን በሚል በሚስብና

በሚያምር ዲዛይን በተሰራ የመጠጥ ማቅረቢያ በድጋሚ ይዛለት

መጣች፡፡

ሙስሊሙ ወጣት የአልኮል መጠጥ እንደማይጠጣ በመናገር

አሁንም አልተቀበለም፡፡

አስተናጋጇ ጉዳዩ አሳሰባትና ለአውሮፕላኑ ማናጀር አሳወቀች፡፡

ማናጀሩ ይበልጥ ባሸበረቀ እቃ መጠጡን ይዞ መጣና ቀርቦ

ያናግረው ጀመር

“ወንድም በአገልግሎታችን ላይ ችግር አለ ወይ ሲል ጠየቀውና

ይህ ነፃና የጉዞ መክፈቻ መጠጥ ነው፤ እባክህ ጠጣ እንጂ” ሲል

ጠየቀው

ወጣቱ ሙስሊም “እኔ ሙስሊም ነኝ አልኮል መጠጥ አልጠጣም”

በማለት መለሰ፡፡

ማናጀሩ መጠጡን እንዲወስድ አሁንም መወትወቱን ቀጠለ. . .

ወጣቱ ሙስሊም “ማናጀር መጠጡን መጀመሪያ ለአውሮፕላን

አብራሪው ስጡት” አለ፡፡

ማናጀሩ “እንዴት አብራሪ እያበረረ አልኮል ይጠጣል? እሱኮ

ተልዕኮ ላይ ነው፡፡ አውሮፕላኑ እንዲከሰከስ ትፈልጋለህ ወይ ሲል

ጠየቀው ?” ወጣቱ ሙስሊም ረጋ ባለ አነጋገር “እኔ ሙስሊም ነኝ

ሁሌም ተልዕኮ ላይ ነኝ፡፡

ኢማኔን የመጠበቅ የሁልጊዜም ተልዕኮዬ ነው፡፡ ከጠጣሁ

የዚህንም የመጪውንም ሀገሬን ነው ማበላሸው” የሚል

የማያዳግም ምላሽ ሰጠው፡፡

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Ye hnatu Lej shared a
Translation is not possible.

«በአዛን ውስጥ ያሉ አስደናቂ ተአምራት»

አዛን የተዋቀረበት የቃላት ብዛት

« አላሁ አክበር ከሚለው መጀመሪያ እስከ ላ ኢላሀ ኢለሏህ» እስከሚለው መጨረሻ የቃላት ብዛት 50 ናቸው።

ቁርአን 6:160 እንደሚነግረን

በአንድ በጎ ተግባር አላህ የሰው ልጅ አስር ሀሰና ይሰጠዋል።

በአምስት አውቃት ሰላት ስንሰግድ የአምሳ ሶላት ያህል እንደ የምናገኘው የሀሰናት መጠን ጋር ቃላቶቹ ጋር እኩል ናቸው።

ሌላም ልቀጥል የአረበኛ ፊደላት ብዛታቸው 28 ናቸው ።

ከነዚህ ውስጥ አስገራሚው ነገር አዛን የሚባልባቸው ፊደላት ብዛት 17 ናቸው ።

ከታች ፊደላትን ቁጠሩ እስኪ

ا ل ه ك ب ر ش د ن م ح س و ي ع ص ف

እነዚህ 17 ፊደላት በቀን ውስጥ ከምንፈፅመው ረከአ ጋር እኩል ናቸው።

ሱብሀነላህ ጥራት ይገባህ ጌታየ!

ይቀጥላል ፣

አንድ አመት አስራ ሁለት ወር ነው ቁርአንን ይህን ያረጋግጥልናል አል_ተውባህ 36 ኛው አንቀፅ ላይ ይናገራል።

እዚህ ላይ ምን ያስገርማል ካላችሁ የአዛን ንግግሮች 12 አረፍተ ነገር ናቸው ።

الله اكبر الله اكبر1

الله اكبر الله اكبر2

اشهد ان لا اله الا الله3

اشهد ان لا اله الا الله 4

اشهد ان محمد رسول الله 5

اشهد ان محمد رسول الله 6

حى على الصلاة7

حى على الصلاة8

حى على الفلاح9

حى على الفلاح10

الله اكبرالله اكبر11

لا اله الا الله12

12 አረፈተ ነገር ብቻ መሆናቸው ሳይሆን የአዛን ድምፅ በነዚህ ወሮች ለደቂቃዎች ለሰከንድ ጥሪው በአለም አይቁያረጥም።

በቅርቡ ሳይንስ ይህን አረጋግጡዋል ።

በመሆኑም ምድራችን ዙሪያዋ 360° ሲሆን እያንዳንዱ ዲግሪ ማሐል የ4 ደቂቃ ልዩነት ቢኖርም አዛን ለአንድ ደቂቃ እንኳን ሳይቋረጥ መሰማቱ እጅግ አስገራሚ ነው።

የአንድ እለት 24 ሰዓት ማለት ምድር በምድር ወገብ 360 ድግሪ አንዴ የምትዞረበት ጊዜ ማለት ነዉ፡፡

በቅድሚያ ድግሪ ማለት የምድር ወራጅ መስመር እና ገዳሚ መስመር የሚገናኙበት ነጥብ ማለት ነዉ፡፡ በመሆኑም እያንዳንዱ የምድር ወራጅ መስመር እና ገዳሚ መስመር የሚገናኙበት 4 የተለዩ ነጥቦች አላቸዉ፡

በያአንዳንድ ዲግሪ ርቀት መካከል የ4 ደቂቃ ልዩነት አዛን ይደረጋል ይህም 360° × 4 ደቂቃ= 1440 ደቂቃ = 24 ሳአት ይሆናል ። ሱብሃነላህ

የመጨረሻው የአዛን ቃላት ላኢላሀ ኢለላህ የሚለው አረፍተ ነገርም የፊደሎቹ ብዛት 12 ነው።

ሙሐመድ ረሱሉላለህ የሚለውም የፊደል ብዛት እንዲሁ 12 ነው።

ሱብሀአነላህ

ላ ኢላሃ ኢለ ሏህ" لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ "ከአሏህ በቀር ሌላ አምላክ የለም" ማለት ነው፣

እነዚህ ቃላቶች الله ከሚለው ሶስት ፊደሎች ብቻ የተዋቀሩ ናቸው ።

لا إله إلا الله

«ማንኛውም እዚህ ዩንቨርስ ያለ አካል የራሱን ስም የተፃፈበትን ፊደላት በመጠቀም ስለማንነቱ መልሶ በነዚያው ፊደላት ለሌላው መግለፅ የሚችል ከአላህ በቀር ወይም ከዚህ ከላኢላኢለላህ ከሚለው ቃላት በቀር ሌላ ቃላት የለም ወደፊትም መፍጠር አይቻልም ።

እንቀጥል ሌላ ተአምር

አዛን አላህ አክበር ብሎ «አላህ»ብሎ በአላህ ስም ይጀምራል ላኢላሀኢለላህ ብሎ በ «አላህ» ስም አዛኑ ያልቃል ። አዛን ላይ የሚደጋገመሙ ብዙ ቃላቶች አላህ የሚለው ነው።

በብዛት የተደጋገሙ ቃላቶችችም እነዚህ የአላህ ስም የተገለፀባቸው ቃላቶች ናቸው ።

አዛን ውስጥ ብዛት ያለው ቃል አላህ የሚለው አስር አንድ ግዜ ተጠቅሱዋል።

11 ቁጥር በባህሪው እኩል መካፈል የሚችለው ለአንድ ብቻ እና ብቻ ነው ።

ሱብሀነላህ

በአዛን ውስጥ አሊፍ የሚለው ፊደል 47 ጊዜ ተጠቅሱዋል ።

ላም የሚለው ፊደል 45 ግዜ ይነሳል ።

ሀ የሚለው ፊደል 20 ግዜ ተጠቅሱዋል የነዚህ ፊደላት ድምር = 112 ፊደላት ናቸው።

አስገራሚው ነገር ይህ ቁጥር የአላህ ስም ከሱረቱል ፋቲሀ እስከ ሱረቱል ኢኽላስ ባለው ምዕራፍ መካከል ተገልፁዋል ግን በመጨረሻዎቹ ፈለቅ እና ናስ በሚባሉ ሁሉት ሱራዎች ላይ የአላህ ስም የለም ።

ሱብሀነ አላህ

አዛን በአመት ከ1800 ግዜ በላይ እንሰማለን ይህ ሁሉ ተአምር እንደያዘ አስተውለን ይሆን?

ምንም አማራጭ የለንም አልሀምዱሊላህ አላ ኒእመተል አዛን አልሀምዱሊላህ አላኒዕመተል ኢስላም ከማለት ውጭ አላህ ታላቅ ነው።

ኢስላምን ተረድተው ከሚያስረዱት አድርገን ያረብ ልቤን አታድረቅብኝ ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Ye hnatu Lej shared a
Translation is not possible.

ጦርነቱን ሐማስ ነው የጀመረው ብለው ለሚወቅሱ ሰዎች የተሰጠ መልስ በትርጉም!

الشيخ عثمان الخميس

14 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Ye hnatu Lej shared a
Translation is not possible.

እስራኤል 680 የጦር ጄቶች አሏት ።

ሁሉም በሚባል መልኩ አሜሪካ ስርታ ያስረከበቻት ነው ።

ከነዚህ ውስጥ 360 የሚሆኑት ሀያሎቹ የአሜሪካ F-16 የጦር ጄቶች ናቸው !

36 የሚሆኑት ደግሞ ከራዳር እይታ ውጭ መብረር የሚችሉትና የየትኛውንም ሀገር ድንበር ጥሰው ሲገቡ የማይታዩት F-35 የጦር ጀቶች ናቸው ። ሁሉም አሜሪካ ሰራሽ ናቸው !

በዚያ ላይ 2,200 ታንኮች አሏት አብዛኛው ከአሜሪካ የተገኙ ናቸው ።

አሜሪካ እስራኤልን ከሀማስ ትከላከልበት ዘንዳ Iron dome የተሰኘውን የአየር መከላከያም አስታጥቃለች ።

እስራኤል ከ 500,000 በላይ እግረኛ ጦርም አላት ።

ወታደራዊ በጀቷ 24 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን ከዚህ ውስጥ 4 ቢሊዮን ዶላሩ በአሜሪካ ይሸፈናል ።

ፍልስጤማዊያን የሚታገሉት ከዚህች የአሜሪካና የእንግሊዝ ልጅ ጋር ነው ።

እስራኤልን ማጥቃትም ሆነ መደብደብ ለኢራንም ሆነ ለሌሎች የእስራኤል ጠላቶች በጣም የሚያስፈራ ሆኖ አይደለም ። ዋናው ፈተና አሜሪካ ከጀርባ መሰለፏ ነው ።

ጠላት ሀያል ነው ተብሎ ሙቶ አይጠበቅምና ፍልስጤማዊያን በፅናት እየታገሉ ነው ። ይሄው ለ 22 ቀን ገትረው ይዘዋታል ። ባለቤቷን የተማመነች በግ እንዲሉ እስራኤልም ጌታዋን አሜሪካን ተማምና በእብሪቷ ቀጥላለች !

ፍልስጤሞችም አላህን ቢሞቱ ውደታውን ቢኖሩ ድሉን አምነው እየተዋደቁ ነው !

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ስለመጠጥ

Surah Al-Baqarah (البقرة), verses: 219

یَسۡـَٔلُوۡنَکَ عَنِ الۡخَمۡرِ وَ الۡمَیۡسِرِؕ قُلۡ فِیۡہِمَاۤ اِثۡمٌ کَبِیۡرٌ وَّ مَنَافِعُ لِلنَّاسِ ۫ وَ اِثۡمُہُمَاۤ اَکۡبَرُ مِنۡ نَّفۡعِہِمَا ؕ وَ یَسۡـَٔلُوۡنَکَ مَا ذَا یُنۡفِقُوۡنَ ۬ؕ قُلِ الۡعَفۡوَؕ کَذٰلِکَ یُبَیِّنُ اللّٰہُ لَکُمُ الۡاٰیٰتِ لَعَلَّکُمۡ تَتَفَکَّرُوۡنَ ﴿۲۱۹﴾ۙ

Translation: አእምሮን ከሚቃወም መጠጥና ከቁማር ይጠይቁሃል፡፡ «በሁለቱም ውስጥ ታላቅ ኃጢኣትና ለሰዎች ጥቅሞች አሉባቸው፡፡ ግን ኃጢኣታቸው ከጥቅማቸው በጣም ትልቅ ነው» በላቸው፡፡ ምንን እንደሚመጸውቱም (መጠኑን) ይጠይቁሃል፡፡ «ትርፍን (መጽውቱ)» በላቸው፡፡ እንደዚሁ ታስተነትኑ ዘንድ አላህ ለናንተ አንቀጾችን ይገልጽላችኋል፡፡

Surah Al-Ma’idah (المآئدة), verses: 90 91

یٰۤاَیُّہَا الَّذِیۡنَ اٰمَنُوۡۤا اِنَّمَا الۡخَمۡرُ وَ الۡمَیۡسِرُ وَ الۡاَنۡصَابُ وَ الۡاَزۡلَامُ رِجۡسٌ مِّنۡ عَمَلِ الشَّیۡطٰنِ فَاجۡتَنِبُوۡہُ لَعَلَّکُمۡ تُفۡلِحُوۡنَ ﴿۹۰﴾اِنَّمَا یُرِیۡدُ الشَّیۡطٰنُ اَنۡ یُّوۡقِعَ بَیۡنَکُمُ الۡعَدَاوَۃَ وَ الۡبَغۡضَآءَ فِی الۡخَمۡرِ وَ الۡمَیۡسِرِ وَ یَصُدَّکُمۡ عَنۡ ذِکۡرِ اللّٰہِ وَ عَنِ الصَّلٰوۃِ ۚ فَہَلۡ اَنۡتُمۡ مُّنۡتَہُوۡنَ ﴿۹۱﴾

Translation: እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሚያሰክር መጠጥ ቁማርም ጣዖታትም አዝላምም ከሰይጣን ሥራ የኾኑ እርኩስ ብቻ ናቸው፡፡ (እርኩስን) ራቁትም ልትድኑ ይከጀላልና።

ሰይጣን የሚፈልገው በሚያሰክር መጠጥና በቁማር በመካከላችሁ ጠብንና ጥላቻን ሊጥል አላህን ከማውሳትና ከስግደትም ሊያግዳችሁ ብቻ ነው፡፡ ታዲያ እናንተ (ከእነዚህ) ተከልካዮች ናችሁን (ተከልከሉ)፡፡

Send as a message
Share on my page
Share in the group