UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ራስህን ከማንም ጋር አታወዳድር !!

ከሰዎች ጋር ራስህን አነፃፅረህ መቼም ሰላም አይኖርህም፤ ህይወት ውድድር አይደለም! ማሸነፍ ወይም መሸነፍ አይደለም!!

የዱኒያ ህይወት ማለት ከዚህ አለም ከመሰናበትህ በፊት ዘላለማዊ ለሆነው

የአኬራ ቤትህ  ስንቅ የምትይዝበት ነው።

ውድድር አቁም!!

#copy

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ይደመጥ!!

رسالة مجاهد للعالم

6 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የሙእታህ ዘመቻ🌴| ይነበብ‼️

🍁🍁🍁🍁🍁🍁

በስምንተኛው አመተ ሂጅራ፡ በጁማደል አወል ወር ረሱል ﷺ ወደ ቡስራ አሚር የላኩትን መልዕክተኛቸው ሀሪስ ኢብኑ ዑመይርን የገደሉ ሰዎችን ለመበቀል ጦርን አዘጋጁ።

ረሱል ﷺ ዘይድ ኢብኑ ሀሪሳህ የጦሩ አሚር እንዲሆን፡ እሱ ከተገደለ ደግሞ ጀዕፈር ኢብኑ አቢ ጧሊብ፡ እሱ ከተገደለ ደግሞ ዐብደሏህ ኢብኑ ረዋሀ አሚር እንዲሆን አዘው፡ በአሏህ ስም ዝመቱ፡ የአሏህንና የናንተን ጠላቶችን ተፋለሙ ብለው ሸኙዋቸው።

ሙእሚኖች ሀሪስ ኢብኑ ዑመይር የተገደለበት ሙእታህ የተባለው ቦታ ሲደርሱ፡ ሩሞች እጅግ ብዙ ጦር አዘግጅተው ጠበቋቸው።

የሙስሊሙ ጦር 3,000 የነበረ ሲሆን የኩፋሮች ቁጥር 200,000 በአንዳንድ ዘገባ ደግሞ 150,000 ነበር።

በዚህ ወቅት ሶሀቦችም ወደ ረሱል ﷺ ተጨማሪ ጦር እንዲልኩ ሰው እንላክ? ወይስ በዚሁ ሁኔታ ቀጥታ ወደ ፍልሚያው እንግባ? በሚለው ጉዳይ ሲወያዩ ዐብደሏህ ኢብኑ ረዋሀ እንዲህ አለ፡

ህዝቦቼ ሆይ! ይህ የምትጠሉት ነገር'ኮ የወጣችሁለት ጉዳይ እኮ ነው። ሸሂድነት ፈልጋችሁ እኮ ነው የወጣችሁት። እኛ እኮ ያ ከፍ ያለው አሏህ ባተለቀን ዲን እንጂ ጠላቶቻችን' ኮ በጦር በዝግጅት፡ በጉልበት ወይም በሰራዊት ብዛት አንጋደልም፡ ደግሞም ጉዳዩ ከሁለት መልካም ነገሮች አንዱ ቢሆን እንጂ ሌላ አይደለም። ወይ አሸንፎ የበላይ መሆን፡ ወይም በአሏህ መንገድ ሸሂድ መሆን አላቸው🌴

ሶሀባዎችም ወሏሂ ኢብኑ ረዋሀ ትክክል ብሏል ብለው ወደ ፍልሚያው ገቡ።

ከባድ የሆነ ፍልሚያን ተፋልመው፡ ባንዲራ የያዘው አሚራቸው ዘይድ ኢብኑ ሀሪሳህ ሸሂድ ሆነ።

ከዛም ጀዕፈር ኢብኑ አቢ ጧሊብ ባንዲራውን ይዞ ሸሂድ እስኪሆን ድረስ ብርቱ ፍልሚያን ተፋለመ።

እሱ ሲገደል ደግሞ ዐብደሏህ ኢብኑ ረዋሀ ባንዲራውን ይዞ ሸሂድ እስኪሆን ድረስ ከባድ ፍልሚያን ተፋለመ።

ዐብደሏህ ኢብኑ ረዋሀ ሲገደል ግን ከፊል ሶሀባዎች ወደ ኋላ ለመመለስ አሰቡ።

ከዛስ?

ኢንሻላህ ቀጣዩና ስለ ሙእታህ ዘመቻ የመጨረሻው ክፍል፡ ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ ሰይፉሏህ የተሰየመበትን ክስተት በአሏህ ፈቃድ በቀጣይ አቀርባለሁ።

ታሪካችን እንወቅ፡ ለልጆቻችን እናስተምር፡ እንደ ቀደምቶቻችን መሆን ባንችል እንኳ ለመመሳሰል እንሞክር።

✍ወንድማችሁ ዩኑስ ሀሰን አብራር ሙሀመድ።

٢٠ ربيع الأخر ١٤٤٥.

https://t.me/abufurat

https://ummalife.com/YunusHassen

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ጠያቂ፡- የተከበሩ ሸይኽ! የቁርኣን አንቀፆችን ግድግዳ ላይ ማንጠልጠል ምንድን ነው ብይኑ?

ኢብኑ ዑሠይሚን፡ ለምንድን ነው የቁርኣን አንቀፆችን ግድግዳ ላይ የምናንጠለጥለው?

ጠያቂ፡ ለጌጥ!

ኢብኑ ዑሠይሚን፡ ለውበት ከሆነ እንግዲያው (ይህን የሚያደርገው) የአላህ አንቀፆችን መቀለጃ አድርጎ ይዟቸዋል ማለት ነው!! እንዴት ተብሎ በልብ ውስጥ ላለ ህመም ፈውስ ሆኖ እንዲሁም መገሰጫ ሆኖ የወረደው የተከበረውና ታላቁ ቁርኣን ለግድግዳ ማስጌጫ ይውላል?!!

ጠያቂ፡- ለበረካ ፍለጋ ከሆነስ?

ኢብኑ ዑሠይሚን፡ ቀደምቶች በንዲህ አይነት ተግባር በረካን ይፈልጉ ነበርን? ማስረጃስ መጥቷል? መልሱ፡- “በጭራሽ አልመጣም” የሚል ነው፡፡ እኛ ዘግይተን የመጣን ትውልዶች ቀደምቶቻችንን የበቃቸው ሊበቃን ይገባል፡፡ ሶስተኛ ምክኒያት ካለ አምጣ

ጠያቂ፡- (የሚያነቡትን ሰዎች) ለማስታወስ

ኢብኑ ዑሠይሚን፡- አንቀፆቹ የሚለጠፉበት ግድግዳ አካባቢ የሚቀመጡ ሰዎች አይተው ያስታውሳሉ? ቀድሞ ነገር ያነባሉ? መልሱ “በጭራሽ!” የሚል ነው፡፡ ምናልባት ጥቂት ካልሆኑ በቀር፡፡ ያውም ከኖሩ ነው፡፡ አራተኛ ምክኒያት ካለ አምጣ

ጠያቂ፡- ከጂን ለመጠበቅ

ኢብኑ ዑሠይሚን፡- መልካም ቀደምቶቻችን በእንዲህ አይነት ተግባር ከጂን ይጠበቁ እንደነበር ማስረጃ መጥቷልን?

ጠያቂው፡- የለም!

ኢብኑ ዑሠይሚን፡- በፍፁም! ስለዚህ እንዴት ሆኖ ነው ይሄ ዘዴ ከቀደምቶቻችን ተሰውሮ ለኛ የተገለጠልን?!!

ስለዚህ ይህን በተመለከተ የምንለው ነገር ቢያንስ ቢያንስ “ቢድዐ ነው!” የሚል ነው፡፡ ይህ እንግዲህ በሆነ መልኩ የቁርኣንን ክብር የሚያዋርድ ከመሆኑ ጋር ነው፡፡ ምክኒያቱም ለምሳሌ የሆነ ገፅ ላይ ወይም ግድግዳ ላይ ((ከፊላችሁ ከፊላችሁን አይማ)) (አልሑጁራት፡ 12) የሚል ይፃፋል፡፡ ስብሰባው ግን በሃሜት የተሞላ ይሆናል፡፡ ይሄ ሹፈት ነው!!

ስለዚህ ግድግዳም ላይ ይሁን ወረቀት ላይ ወይም ሌላ ነገር ላይ የቁርኣን አንቀፆችን ፅፎ ግድግዳ ላይ አንጠልጥሎ ያገኛችሁትን ሁሉ ከዚህ ተግባር እንዲታቀቡ ምከሯቸው፡፡ የአላህ ንግግር ለዚህ ተግባር መገልገል አይቻልም” በለው ወንድምህን፡፡…

(ሊቃኣቱልባቢልመፍቱሕ፡ 25/197)

ሼር ማድረግ እንዳይረሱ፡፡ ጥፋቱ ከብዙ ቤቶች ውስጥ ያለ ነውና ሰዎችን ከጥፋቱ ለመመለስ ያቅሞትን ይጣሩ፡፡

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Mensura Mohammednur Changed her profile picture
8 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group