UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

መላ ዐረቢያን የሚያስተዳድረው የኢስላማዊ ስረወ መንግስቱ መሪ ዑመር ረዐ የመስጂደል ሀራምን ግቢ ለማስፋፋት የዐባስ ቤት እንዲፈርስ እና ለዐባስም በምትኩ ቆንጆ ቤት ሌላ ቦታ እንዲገነባለት ትዕዛዝ አስተላለፈ።

አባስም፦‹‹ቤቴ እንዲፈርስ እልፈቅድም›› አሉ።

(መብት)

ዑመርም፦‹‹ዐባስ! የአላህን ቤት ቤት ለማስፋፋት እኮ ነው›› አለው።

(ማባበል)

ዐባስም፦‹‹አልፈቅድም አልኩኝ እኮ ዑመር!›› ብሎ መለሰ።

(መሪ ፊት መብትን ማስከበር)

ዑመርም፦‹‹እንግዲያውስ ወደ ሸንጎ ሂደን እንዳኝ፤ ሚዳኘንን ዳኛም አንተው ምረጥ›› አለው።

(ፍትህ እና መተናነስ)

ዐባስም፦‹‹ዳኛ ሹረይሕ ይዳኘን›› አለ።

(ጥሩ ስም ሲኖር)

ዑመርም፦‹‹ተስማምቻለሁ››አለ።

(መተናነስ)

ዐባስም፦‹‹የምእመናን መሪ ሆይ! በል ዳኛ ሹረይሕን ጥራው'ና ይዳኘን›› አለ።

ዑመርም፦‹‹ዳኛ ወደሚዳኛቸው ሰዎች አይሄድም፤ እነሱ ናቸው ወደ እሱ መሄድ ያለባቸው። ተነስ እኛ እንሂድ›› አለው።

(መርህ)

ሁለቱም ተያይዘው ወደ ሸንጎው ዳኛ አመሩ። ሸንጎው ፊት ሲቆሙም ዳኛው፦‹‹የምእመናን መሪ...›› ብሎ ዑመርን ሲጠራ ዑመርም፦‹‹ዑመር ብለህ ጥራኝ፤ ሸንጎ ላይ እስካለሁ ድረስ›› አለው።

(የሸንጎ እና የዳኛ ክብር)

ሸንጎው ተጀመረ። ሁለቱም ስሞታቸውን ለዳኛው ካሳሰቡ በኋላ ዳኛው እንዲህ ስል ውሳኔ አስተላለፈ፦‹‹ከሀራም የፀዳ ቦታ ማለት መስጅድ ነው።መስጂድን ለማስፋፋት ያለ በጎ ፈቃዱ የዐባስን ቤትም ማፍረስ ደግሞ ሀራም ነው››

(ፍትህ ፣ ሀላፊነት፣ ድፍረት)

ዑመርም ክሱ ውድቅ ሲሆንበት፦‹‹ምንኛ ፍትሀዊ ዳኛ ነህ! ሸንጎህ ያማረ›› አለው።

(ዕውነታን መቀበል)

ዑመር እዝያው ሽንጎ ላይ ሁኖ ይህንን ዳኛ የዳኞች ሁሉ የበላይ አድርጎትም ሾመው።

(ዕምነት)

ይህን የተመለከተው ዐባስም፦‹‹እንግዲያ ነገሩ እንዲህ ተሆነማ ፤ እኔም ቤቴን በገዛ ፈቃዴ ለአላህ ብዬ ለቅቄያለሁ›› አለ

(ከድል በኋላ ያለ ለጋስነት)

ምንጭ፦

البدايه والنهايه

Send as a message
Share on my page
Share in the group
idrisuma shared a
Translation is not possible.

Another one from Berlin…

#freepalestinian 🇵🇸

#ድል_ለፍልስጤማውያን✊ 🇵🇸

7 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Aktualisiere deinen Browser | Facebook

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
Telegram: Contact @h4_h4i
t.me

Telegram: Contact @h4_h4i

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group