UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
ለመጅሊስ መሪነት ማንን እንምረጥ?
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በአሕመዲን ጀበል
💢💢💢💢💢💢
ሕዝበ ሙስሊሙ የመሪ ተቋሙ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ምርጫ ላይ ይሆነኛል የሚለውን አካል በነጻነት መምረጥ ለድርድር የማይቀርብ መብቱ መሆኑ እሙን ነው። በዚህ ረገድ የሚመርጣቸው አካላት ምን እንዲያደርጉለት ይፈልጋል? የሚመርጣቸውስ ለምን ዓላማ ነው?
ሊመርጣቸው ያሰባቸው አካላትስ ያንን የሚያልመውን ዓላማውን እውን ማሳካት ይችላሉ ወይ? የሚለውን በአግባቢ ማየትና መለየት እጅግ ወሳኝ ይሆናል። ምክንያቱን መጅሊስንም ሆነ መሪዎቹ የሚፈለጉት የሕዝቡ ወኪል አገልጋይ ሆነውለት ከተቋሙ ሕዝበ ሙስሊሙ የሚፈልጋቸውን አገልግሎቶቹ በተገቢው መልኩ እንዲሰጡ ነውና። በመሆኑም መራጮች ይሆኑኛል የሚሉትን አካላት ሲመርጡ አልያም ለመመረጥ ያሰቡ ተመራጮችም ራሳቸውን ለቦታው ሲያጩ ስለተቋሙ ምንነት፥ የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት፥ስለሚጠበቅባቸው ሚና እንዲሁም የራሳቸውን አቅምና ብቃት ከግምት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
በዚህ ጽሑፍ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤትን ምንነትና ሚናን ስለመጅሊስ በቂ ግንዛቤ ለሌላቸው ለማስገንዘብ ፥ግንዛቤው ላላቸው ደግሞ ለማስታወስ እሞክራለሁ።ይህም የመጅሊስን ራዕይ፥ ተልዕኮ፥ ግቦች፥ ዓላማዎችና ተግባራትን በማብራራት ይሆናል። መልካም ንባብ።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች(መጅሊስ) ራዕይ
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥
በሀገሪቱ ውስጥ በእስልምና መርሆች ላይ የተመሰረተ እና ለፍትህ፣ ለልማት እና ለአንድነት ቁርጠኛ የሆነ ሰላማዊ፣ ሁሉን ዓቀፍ እና በሃይማኖቱ የበለጸገ ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ማህበረሰብ ተፈጥሮ ማየት ።
የመጅሊስ ተልዕኮ
🏀🏀🏀🏀🏀
በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኘውን ሙስሊም ማህበረሰብ ኢስላማዊ አስተምህሮዎችን በማስፋፋት ፣የሃይማኖት መብቶችን በማስጠበቅ፣የማህበረሰብን ተጠቃሚነት በማጎልበት ለሀገሪቱ ሃይማኖታዊ፣ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት የመሪነት ሚናውን መወጣት።
የመጅሊስ ግቦች
🔮🔮🔮🔮🔮
1. የሃይማኖት ነፃነት እና እኩልነት በማስጠበቅ ከትንኮሳና ከአድሎ የራቀ ሰላማዊና የተረጋጋ ሕይወት ለሕዝበ ሙስሊሙ እውን እንዲሆን ማድረግ።
2. በመላው ኢትዮጵያ ኢስላማዊ ትምህርቶችን እና እሴቶችን ማሳደግ።
3. በሙስሊሞች መካከል አንድነት እና ትብብርን ማጠናከር።
4. የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ።
5. የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት በብቃት ለመፍታት እንዲያስችል ተቋማዊ አቅምን ቀጣይነት ባለው መልኩ መገንባት።
የመጅሊስ ዓላማዎች
🌺🌺🌺🌺🌺🌺
1. ለሙስሊሞች መብቶች መከበር መቆም
🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅
የህብረተሰቡን ሃይማኖታዊ እና ህዝባዊ ጥያቄዎችን ለመፍታት ከመንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ተባብሮ መስራት።
2. ትምህርት እና ግንዛቤ
📀📀📀📀📀📀📀📀
የኢስላማዊ ትምህርት ተደራሽነትን ለማሻሻል ኢስላማዊ ትምህርት ቤቶችን እና ማዕከላትን ማቋቋም፥ያሉትን ማጠናከር እና መደገፍ።
3. አንድነት እና ትብብርን ማጠንከር
🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁
በሙስሊሞች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር በማህበረሰቡ መካከል ውይይቶችን እና ዝግጅቶችን ማድረግ።
4. የበጎ አድራጎት ድርጊቶችንና ተቋማትን ማስተባበር
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶
የተቸገሩና ተጋላጭ የሆኑ ሙስሊሞችን ለመርዳት ተነሳሽነቶችን ማዘጋጀት።
5. ተቋማዊ ልማት
🆙🆙🆙🆙🆙
የአቅም ግንባታና የቴክኖሎጂ ትግበራ በማድረግ የምክር ቤቱን የአሰራር ቅልጥፍና ማሻሻል።
የመጅሊስ ስትራቴጂዎች
🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲
1. በሃይማኖታዊ፥ ማህበራዊ፥ኢኮኖሚያዊና ሀገራዊ ጉዳዮች የሕዝበ ሙስሊሙን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ዉጥኖችን ቀርጾ ንቅናቄን ማድረግ።
2. በሃይማኖታዊና ዓለማዊ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ሙስሊሞች በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ።
3. የመጅሊስ መዋቅርንና ሌሎች ኢስላማዊ ተቋማትን በሁለንተናዊ መልኩ የሕዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች መመለስ እንዲችሉና ፍላጎት ማሟላት በሚችሉበት ቁመና ላይ እንዲገኙ ማጠናከር።
4. ሕዝበ ሙስሊሙ ከድህነት፥ ችግርና ችጋር፥ ኋላ ቀርነትና መሃይምነት የተላቀቀ የተሻለ ሕይወት መኖር እንዲያስችለው የሙስሊሞችን ኢኮኖሚያዊ አቅምና ደረጃን ማጎልበት።
5. በሀገሪቱ ሙስሊሞች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ያሉ አደናቃፊና ችግር ፈጣሪ የሆኑ ፖሊሲዎች፥ሕጎችና አሰራሮች እንዲለወጡ መስራት።
የመጅሊስ ተግባራት
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
1. በኢትዮጵያ ዉስጥ የሃይማኖት ጉዳዮችን በየእርከኑ በተገቢው መልኩ መምራት።
2. የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ፍላጎትና መብት ማስጠበቅን ዓላማ ባደረገ መልኩ በሀገር ዉስጥም ሆነ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሙስሊሞችን መወከል።
3. በዘወትር የሚደረጉ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በተገበው መልኩ ማስተዳደር።
4. የሙስሊሞችን መብቶችና ጥቅሞችን ማስጠበቅ።
5. የሕዝበ ሙስሊሙ ማህበራዊ ችግሮች እንዲቀረፉ የበጎ አድራጎት እና ማህበራዊ አገልግሎቶችን ማስተባበርና በተገቢው መልኩ መተግበር።
6. በኢትዮጵያ ያሉ ኢስላማዊ ቅርሶችና ታሪኮች እንዲጠበቁና እንዲታወቁ ማድረግ።
7. በሁለንተናዊ መልኩ ለሙስሊሙ ማህበረሰብና ተቋማት የአቅም ግንባታ ተግባራት መከወን።
8. የሕዝበ ሙስሊሙን አንድነት፥ ትብብርና ትስስር ማጎልበት የሚችሉ ተግባራትን መከወን።
9. በመላ ሀገሪቱ የሙስሊሞችን ማህበረሰባዊ ልማትን በተቀናጀ መልኩ መተግበር።
10. የሕዝበ ሙስሊሙን መብቶችንና ጥቅሞችን አሳልፎ በማይሰጥ መልኩ በሀገራዊና ሕዝባዊ ጉዳዮች ከመንግስት ጋር ተባብሮ መስራት።
በመጨረሻም!
🌹🌹🌹🌹🌹
ከላይ የተጠቀሱት የሕዝበ ሙስሊሙ መሪ ድርጅት የሆነው መጅሊስ በአስተዳደር ረገድ የሚጠበቅበትን ሚናን ለማብራራት የተሞከረበት ነው።እያንዳንዱ አንባቢ መጅሊስም ሆነ መጅሊሱን የሚመሩ አካላት ምን ዓይነት አገልግሎቶች እንዲሰጡት እንደሚፈልግ የየራሱን ሀሳብ እንደሚኖረው እገምታለሁ።በዚህ ላይ ይህንን ጽሑፍ መነሻ በማድረግ በጉዳዩ ላይ ዉይይት እያደረጉ ሀሳቡን ማዳብር እንዲሁም ከዚህ አንጻር ምን ዓይነት አመራሮችን ለመጀሊስ እንምረጥ? በሚል እየተወያዩ መዘጋጀት ተገቢ ይሆናል። በተይም የመጅሊስ ጉዳይ የሚያሳስባችና በመጅሊስ ጉዳይ ዋጋ የከፈላችሁ ከታች እሰከ ላይ ባሉት ሁሉም የመጅሊስ እርከኖች ተገቢው ሰው እንዲመረጥ ትጉ።
እንዲሁም በመጅሊስ ስልጣን ላይ ያላችሁም ሆነ ወደ መጅሊስ መሪነት ለመምጣት ፍላጎቱ ያላችሁ ከዚህ አንጻር ራሳችሁን በመገምገም ጉዳዩ አማናና በአላህ ዘንድ ተጠያቂነት ያለበት መሆኑን በመረዳት የተሻለ ተቋም ለመገንባት የየበኩላችሁን ታሪካዊ ሚና እንድትወጡ እጠይቃለሁ።
በዚህ ረገድ ከፌደራል መጅሊስ የአሁኑ ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱህፋ አንስቶ እስከ የወረዳ መጅሊስ እርከን ያላችሁ ሁሉም የመጅሊስ አባላትና አመራሮች፥ የመጅሊስ ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት፥ እንዲሁም ለመመረጥ የመጅሊስን ደጅ እየጠናችሁና ቤት ለቤት ጥረት እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት፥ እንዲሁም የምርጫ ካርድ ያልወሳዳችሁም ሆነ የወሰዳችሁ እያንዳንዱ ሙስሊም መራጮች የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መሪ ድርጅት ከላይ የተጠቀሱትንና እናንተ የምታስቧቸውን ሚናዎች መወጣት የሚችል፥ የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት ያማከለና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የሚችል፥ የሀገርና የህዝብ ኩራት የሚሆን ጠንካራ ተቋም እዉን ለማድረግ የሚያግዙ
መሪዎችን ለመምረጥ ታሪካዊ ኃላፊነት በጫንቃችሁ ላይ ወድቋል።ስለሆነም ኃላፊነታችሁን ተወጡ!
ስለመጅሊስ ጽሑፌ ቀጥላል። አላህ ካለ በቀጣይ በተመሳሳይ የዑለማ ምክር ቤት ሚናና ተግበራት ጋር በተያያዘ ጽሑፍ እስክንገናኝ እሰከዚያው ቸር እንሰንብት!
https://t.me/Seyfel_Islam
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ስለጋዛ አዳድስ መረጃዎችን ለማጋራት ያክል
፨ በዛሬው እለት እስራኤል ወደ ራፋህ ለመግባት ስትዋጋ ነው የዋለቺው ። በዚህም የራፋህ መግቢያ በርን ተቆጣጥራለች ። ሀማስም የመከላከል ጦርነት ሲያደርግ ነው የዋለው ።
ይሁን እንጅ አሜሪካ በሰጠቺው መግለጫ የራፋሁ ጦርነት ሙሉ ወረራ አይደለም የእስራኤል ጦርም ራፋህን ሙሉ ለሙሉ አይወርም የሚል ማስተባበያ ሰጥታለች ። እስራኤል በበኩሏ የራፋህ ጦርነቱን እያካሔድኩ ያለሁት በሀማስ ላይ ጫና ለማሳደርና ምርኮኞቹ እንዲለቀቁ ለማድረግ ነው የሚል መግለጫ ሰጥታለች ። የእስራኤሉ መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንትም ከጦር ሜዳው ተገኝቶ ምርኮኞች የማይለቀቁ ከሆነ ራፋህን እስከ ጥግ እንዘልቃለን ብሏል።
👉 ጀርመንን ጨምሮ በርካታ የአለም ሀገራት እስራኤል የራፋህ ዘመቻዋን በአስቸኳይ እንድታቆም አሳስበዋል ። እስራኤል ከዚህ በተጨማሪ የእርዳታ ቁሳቁሶች ወደ ጋዛ እንዳይገቡ የምታደርገውን ክልከላ በአስቸኳይ እንድታቆም እናሳስባለን ስትል ጀርመን ገልፃለች ።
👉 የፍልስጤማውያን የድጋፍ ሰልፍ ከአረብ ሀገራት ውጭ በመላው አለም ተቀጣጥሎ ሲውል የምስራቅ አውሮፓዋ ግሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የፍልስጤም ድጋፍ ሰልፍን አስተናግዳለች ። በዋና ከተማዋ አቴንስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ግሪካዊያን የፍልስጤምን ባንድራ ይዘው የወጡ ሲሆን የግሪክ ፖሊስ ሰልፈኞቹን በአስለቃሽ ጭስ ለመበተን ሲታገል ነው የዋለው።
ከዚያ ውጭ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመፅ ዛሬ የበርሊን ዩኒቨርስቲን ሲንጠው ነው የዋለው ። የጀርመን ፀጥታ ሀይሎች ሰልፈኞችን ለመበተን ቢጥሩም አልተሳካላቸውም ። በአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች የሚደረገው ተቃውሞም ተባብሶ እንደቀጠለ ነው ። ከስዊድን እስከ ኖርዌይ የፍልስጤማውያን የድጋፍ ድምፅ እየተስተጋባ ይገኛል ።
👉 የሀማስም የእስራኤልም ተደራዳሪዎች ግብፅ ካይሮ ገብተዋል ። የ CIA ዋና ዳይሬክተርም ድርድሩን ለመከታተል ካይሮ ናቸው። ሀማስ " ኳሷ ያለቺው በእስራኤል እጅ" ነው ያለ ሲሆን ቤኒያማን ኔታኒያሁ የሚያደርገው የእብደት ድርጊት አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱን ማረጋገጫ ነው ብሏል ።
አሜሪካ በበኩሏ ሀማስና እስራኤል ልዩነቱን አጥብበው ለስምምነት እንዲደርሱ አሳስባለች ። የሗይታውስ ቃልአቀባይ ጆን ኪርባይ ማምሻውን በሰጠው መግለጫ ሁለቱም ወገኖች ወደ ድርድር መምጣታቸው ትልቅ እርምጃ ነው ያለ ሲሆን ልዩነቶች ጠበው የተኩስ አቁሙ እንደሚፈፀም ያለውን እምነት ገልጿል ።
👉 የአሜሪካ የኳታርና የግብፅ አደራዳሪዎች በአሁኑ ሰአት ሰፊ ውይይት እያደረጉ ሲሆን እዚያው ከሚገኙት ከሀማስና ከእስራኤል የልኡካን ቡድኖች ጋርም እየተነጋገሩ ይገኛሉ ።
አላህ ለፍልስጤማውያን የሚበጀውን ነገር ይምረጥላቸው !
t.me/Seidsocial
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
“እስረኛ ጁዲ ፌንስታይን ከአንድ ወር በፊት ባጋጠማት ቁስሏ ምክንያት ህይወቷ ያለፈው በሆስፒታሎች ላይ በደረሰው ጥፋት ምክንያት እንክብካቤ ማድረግ ስላልተቻለ ነው።
እስረኛዋ በጥቅምት 7 በጠና ቆስላ በጋዛ ሆስፒታሎች ህክምና ያገኘች ሲሆን ካገገመች በኋላ ወደ እስር ቤት ተመልሳ ነበር።
የ70 ዓመቷ እስረኛ ጁዲ ፌንስታይን ከሌላ እስረኛ ጋር ባጋጠማት ከባድ ጉዳት ህይወቷ ያለፈው በእስር ቦታቸው ከአንድ ወር በፊት ነው።
የጦር ሰራዊታችሁ ሆስፒታሎችን ማውደሙ እና ከአገልግሎት ውጪ ማድረጉ ለታራሚዎቻችሁም ስቃይና ሞት ምክንያት ሆኗል!
ህዝባችን እየተሰቃየበት  ያለው መከራ እንደዚህ ነው”
#አቡ_ዑበይዳህ
https://t.me/Seyfel_Islam
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ሃማስ ከእስራኤል ጋር ያለውን ስምምነት ለመጨረስ የቀረበውን ሃሳብ ካጸደቀ በኋላ እስራኤል የመጀመሪያ ይፋዊ አስተያየት ሰጠች።
የእስራኤል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው የሐማስ ንቅናቄ በጋዛ የተኩስ አቁምን በሚመለከት በአንድ ወገን ሃሳብ ላይ መስማማቱን ገልጾ ቴል አቪቭ ጉዳዩን እያጤነች እንደሆነ ገልጿል።
የእስራኤል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን "በሐማስ የጸደቀው የተሻሻለው የግብፅ ወረቀት እስራኤል ካጸደቀችው የተለየ ነው" ሲል አመልክቷል።
የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን የጦርነት ምክር ቤቱን ምንጭ በመጥቀስ "የሃማስ መግለጫ እስራኤልን ከወረራ አቋሟ እንደማትለወጥ ለማሳየት ሆነ ተብሎ የተደረገ አሳሳች ሙከራ ነው"በማለት ወቅሷል።
ሮይተርስ የእስራኤልን ባለስልጣን ጠቅሶ እንዳስረዳው “በሀማስ የፀደቀው ሀሳብ እስራኤል #ያልተስማማችባቸውን ሰፊ ​​ድምዳሜዎች ያካተተ ሲሆን የተስማማችበትን ስምምነትም ያካትታል!”ብሏል።
የእስራኤል ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን እንዳለው "ቴል አቪቭ ዛሬ ማምሻውን የሃማስን ይፋዊ ምላሽ ተቀብሎ እያጠናው ነው!”ብሏል።
የእስራኤላውያን እስረኞች ቤተሰቦች ግን ሃማስ በስምምነቱ መስማማቱን አረጋግጠዋል፣አሁን መንግስት እስረኞቹን ወደ ትውልድ ቀያቸው የሚመልስበት ትክክለኛው ጊዜ ነው በማለት “ሀገሪቱን ወደማቃጠል የሚወስዱ ግዙፍ ተቃውሞዎች”እንደሚያደርጉ አስጠንቅቀዋል!
ሃማስ በጋዛ ሰርጥ የተኩስ አቁም ስምምነት የኳታር እና የግብፅ ሸምጋዮች ያቀረቡትን ሃሳብ ማፅደቁን አስታውቋል።
ምንጭ፡ RT + የእስራኤል ሚዲያ
https://t.me/Seyfel_Islam
Telegram: Contact @Seyfel_Islam

Telegram: Contact @Seyfel_Islam

قال ابن تيمية -رحمه الله-: {قوام الدين كتاب يهدي وسيف ينصر وكفى بربك هادياونصيرا} مجموع الفتاوى [10/13] ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት በሚመችዎ የማህበራዊ ሚድያ ይከታተሉኝ? https://heylink.me/AzizoSocialLinks.com/
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
እስራኤል በራፋህ ላይ የጀመረችውን ጥቃት ለማስቆም እና ነዋሪዎችን ባልታወቀ ሁኔታ መፈናቀላቸውን ለመከላከል ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጣልቃ እንዲገባ #ሳዑዲ_አረቢያ ጠየቀች።
የሳዑዲ አረቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር “የእስራኤል ወራሪ ሃይሎች” የራፋህ ከተማን ኢላማ ያደረጉት በ“ስልታዊ የደም አፋሳሽ ዘመቻ” የጋዛ ሰርጥ አካባቢዎችን በሙሉ ለመውረር እና ነዋሪዎቿን ወዳልታወቀ ቦታ ለማፈናቀል በማቀድ ሲሆን ይህም የሚያስከትለውን ከባድ አደጋ አስጠንቅቋል።
የሳዑዲ የዜና አገልግሎት እንደገለፀው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ “የሳዑዲ አረቢያ መንግስት የእስራኤል ወራሪ ሃይሎች በራፋህ ከተማ ላይ እያነጣጠሩት ያለውን አደጋ በማስጠንቀቅ፣ደም አፋሳሽ እና ስልታዊ በሆነ መልኩ ሁሉንም አካባቢዎች ለመውረር የጀመረችውን ዘመቻ ገልጿል።
በጋዛ ሰርጥ ነዋሪዎቿን ወዳልታወቀ ቦታ ያፈናቅላሉ፤ ይህም ካደረሱት ከፍተኛ ውድመት በኋላ አስተማማኝ መሸሸጊያ ቦታ ባለመኖሩ ነው ብሏል በመግለጫው።
ሚኒስቴሩ በማያያዝም “ወራሪው ጦርነቱን የማቆም ሃሳቦችን ውድቅ በማድረግ፤እነዚህን እልቂቶች ለማስቆም የሚጠይቁትን ሁሉንም ዓለም አቀፍ ውሳኔዎች በግልጽ በመጣስና የዓለም አቀፍ ሕግጋትን በመጣስ ሰብዓዊ ቀውሱን የሚያባብስ እና ዓለም አቀፍ የሰላም ጥረቶችን የሚገድብ ነው"ብላ ል።
በተጨማሪም "በተወረሩት የፍልስጤም ግዛቶች” ውስጥ መከላከያ በሌላቸው ሰላማዊ ዜጎች ላይ በወረራ ኃይሎች  የሚካሄደውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ ለማስቆም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ የመንግሥቱ ጥሪ አድሷል።
የፍልስጤም ፕሬዝደንት የራፋህን ወረራ ለመከላከል ከክልላዊ እና አለም አቀፍ ፓርቲዎች በተለይም ከአሜሪካ ጋር ጥብቅ ግንኙነት እያደረገ መሆኑንም ሰኞ እለት አስታውቆ ነበር።
ምንጭ:Saudi Press Agency(SPA)
#rt
https://t.me/Seyfel_Islam
Telegram: Contact @Seyfel_Islam

Telegram: Contact @Seyfel_Islam

قال ابن تيمية -رحمه الله-: {قوام الدين كتاب يهدي وسيف ينصر وكفى بربك هادياونصيرا} مجموع الفتاوى [10/13] ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት በሚመችዎ የማህበራዊ ሚድያ ይከታተሉኝ? https://heylink.me/AzizoSocialLinks.com/
Send as a message
Share on my page
Share in the group