ለመጅሊስ መሪነት ማንን እንምረጥ?
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በአሕመዲን ጀበል
💢💢💢💢💢💢
ሕዝበ ሙስሊሙ የመሪ ተቋሙ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ምርጫ ላይ ይሆነኛል የሚለውን አካል በነጻነት መምረጥ ለድርድር የማይቀርብ መብቱ መሆኑ እሙን ነው። በዚህ ረገድ የሚመርጣቸው አካላት ምን እንዲያደርጉለት ይፈልጋል? የሚመርጣቸውስ ለምን ዓላማ ነው?
ሊመርጣቸው ያሰባቸው አካላትስ ያንን የሚያልመውን ዓላማውን እውን ማሳካት ይችላሉ ወይ? የሚለውን በአግባቢ ማየትና መለየት እጅግ ወሳኝ ይሆናል። ምክንያቱን መጅሊስንም ሆነ መሪዎቹ የሚፈለጉት የሕዝቡ ወኪል አገልጋይ ሆነውለት ከተቋሙ ሕዝበ ሙስሊሙ የሚፈልጋቸውን አገልግሎቶቹ በተገቢው መልኩ እንዲሰጡ ነውና። በመሆኑም መራጮች ይሆኑኛል የሚሉትን አካላት ሲመርጡ አልያም ለመመረጥ ያሰቡ ተመራጮችም ራሳቸውን ለቦታው ሲያጩ ስለተቋሙ ምንነት፥ የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት፥ስለሚጠበቅባቸው ሚና እንዲሁም የራሳቸውን አቅምና ብቃት ከግምት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
በዚህ ጽሑፍ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤትን ምንነትና ሚናን ስለመጅሊስ በቂ ግንዛቤ ለሌላቸው ለማስገንዘብ ፥ግንዛቤው ላላቸው ደግሞ ለማስታወስ እሞክራለሁ።ይህም የመጅሊስን ራዕይ፥ ተልዕኮ፥ ግቦች፥ ዓላማዎችና ተግባራትን በማብራራት ይሆናል። መልካም ንባብ።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች(መጅሊስ) ራዕይ
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥
በሀገሪቱ ውስጥ በእስልምና መርሆች ላይ የተመሰረተ እና ለፍትህ፣ ለልማት እና ለአንድነት ቁርጠኛ የሆነ ሰላማዊ፣ ሁሉን ዓቀፍ እና በሃይማኖቱ የበለጸገ ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ማህበረሰብ ተፈጥሮ ማየት ።
የመጅሊስ ተልዕኮ
🏀🏀🏀🏀🏀
በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኘውን ሙስሊም ማህበረሰብ ኢስላማዊ አስተምህሮዎችን በማስፋፋት ፣የሃይማኖት መብቶችን በማስጠበቅ፣የማህበረሰብን ተጠቃሚነት በማጎልበት ለሀገሪቱ ሃይማኖታዊ፣ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት የመሪነት ሚናውን መወጣት።
የመጅሊስ ግቦች
🔮🔮🔮🔮🔮
1. የሃይማኖት ነፃነት እና እኩልነት በማስጠበቅ ከትንኮሳና ከአድሎ የራቀ ሰላማዊና የተረጋጋ ሕይወት ለሕዝበ ሙስሊሙ እውን እንዲሆን ማድረግ።
2. በመላው ኢትዮጵያ ኢስላማዊ ትምህርቶችን እና እሴቶችን ማሳደግ።
3. በሙስሊሞች መካከል አንድነት እና ትብብርን ማጠናከር።
4. የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ።
5. የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት በብቃት ለመፍታት እንዲያስችል ተቋማዊ አቅምን ቀጣይነት ባለው መልኩ መገንባት።
የመጅሊስ ዓላማዎች
🌺🌺🌺🌺🌺🌺
1. ለሙስሊሞች መብቶች መከበር መቆም
🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅
የህብረተሰቡን ሃይማኖታዊ እና ህዝባዊ ጥያቄዎችን ለመፍታት ከመንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ተባብሮ መስራት።
2. ትምህርት እና ግንዛቤ
📀📀📀📀📀📀📀📀
የኢስላማዊ ትምህርት ተደራሽነትን ለማሻሻል ኢስላማዊ ትምህርት ቤቶችን እና ማዕከላትን ማቋቋም፥ያሉትን ማጠናከር እና መደገፍ።
3. አንድነት እና ትብብርን ማጠንከር
🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁
በሙስሊሞች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር በማህበረሰቡ መካከል ውይይቶችን እና ዝግጅቶችን ማድረግ።
4. የበጎ አድራጎት ድርጊቶችንና ተቋማትን ማስተባበር
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶
የተቸገሩና ተጋላጭ የሆኑ ሙስሊሞችን ለመርዳት ተነሳሽነቶችን ማዘጋጀት።
5. ተቋማዊ ልማት
🆙🆙🆙🆙🆙
የአቅም ግንባታና የቴክኖሎጂ ትግበራ በማድረግ የምክር ቤቱን የአሰራር ቅልጥፍና ማሻሻል።
የመጅሊስ ስትራቴጂዎች
🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲
1. በሃይማኖታዊ፥ ማህበራዊ፥ኢኮኖሚያዊና ሀገራዊ ጉዳዮች የሕዝበ ሙስሊሙን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ዉጥኖችን ቀርጾ ንቅናቄን ማድረግ።
2. በሃይማኖታዊና ዓለማዊ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ሙስሊሞች በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ።
3. የመጅሊስ መዋቅርንና ሌሎች ኢስላማዊ ተቋማትን በሁለንተናዊ መልኩ የሕዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች መመለስ እንዲችሉና ፍላጎት ማሟላት በሚችሉበት ቁመና ላይ እንዲገኙ ማጠናከር።
4. ሕዝበ ሙስሊሙ ከድህነት፥ ችግርና ችጋር፥ ኋላ ቀርነትና መሃይምነት የተላቀቀ የተሻለ ሕይወት መኖር እንዲያስችለው የሙስሊሞችን ኢኮኖሚያዊ አቅምና ደረጃን ማጎልበት።
5. በሀገሪቱ ሙስሊሞች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ያሉ አደናቃፊና ችግር ፈጣሪ የሆኑ ፖሊሲዎች፥ሕጎችና አሰራሮች እንዲለወጡ መስራት።
የመጅሊስ ተግባራት
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
1. በኢትዮጵያ ዉስጥ የሃይማኖት ጉዳዮችን በየእርከኑ በተገቢው መልኩ መምራት።
2. የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ፍላጎትና መብት ማስጠበቅን ዓላማ ባደረገ መልኩ በሀገር ዉስጥም ሆነ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሙስሊሞችን መወከል።
3. በዘወትር የሚደረጉ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በተገበው መልኩ ማስተዳደር።
4. የሙስሊሞችን መብቶችና ጥቅሞችን ማስጠበቅ።
5. የሕዝበ ሙስሊሙ ማህበራዊ ችግሮች እንዲቀረፉ የበጎ አድራጎት እና ማህበራዊ አገልግሎቶችን ማስተባበርና በተገቢው መልኩ መተግበር።
6. በኢትዮጵያ ያሉ ኢስላማዊ ቅርሶችና ታሪኮች እንዲጠበቁና እንዲታወቁ ማድረግ።
7. በሁለንተናዊ መልኩ ለሙስሊሙ ማህበረሰብና ተቋማት የአቅም ግንባታ ተግባራት መከወን።
8. የሕዝበ ሙስሊሙን አንድነት፥ ትብብርና ትስስር ማጎልበት የሚችሉ ተግባራትን መከወን።
9. በመላ ሀገሪቱ የሙስሊሞችን ማህበረሰባዊ ልማትን በተቀናጀ መልኩ መተግበር።
10. የሕዝበ ሙስሊሙን መብቶችንና ጥቅሞችን አሳልፎ በማይሰጥ መልኩ በሀገራዊና ሕዝባዊ ጉዳዮች ከመንግስት ጋር ተባብሮ መስራት።
በመጨረሻም!
🌹🌹🌹🌹🌹
ከላይ የተጠቀሱት የሕዝበ ሙስሊሙ መሪ ድርጅት የሆነው መጅሊስ በአስተዳደር ረገድ የሚጠበቅበትን ሚናን ለማብራራት የተሞከረበት ነው።እያንዳንዱ አንባቢ መጅሊስም ሆነ መጅሊሱን የሚመሩ አካላት ምን ዓይነት አገልግሎቶች እንዲሰጡት እንደሚፈልግ የየራሱን ሀሳብ እንደሚኖረው እገምታለሁ።በዚህ ላይ ይህንን ጽሑፍ መነሻ በማድረግ በጉዳዩ ላይ ዉይይት እያደረጉ ሀሳቡን ማዳብር እንዲሁም ከዚህ አንጻር ምን ዓይነት አመራሮችን ለመጀሊስ እንምረጥ? በሚል እየተወያዩ መዘጋጀት ተገቢ ይሆናል። በተይም የመጅሊስ ጉዳይ የሚያሳስባችና በመጅሊስ ጉዳይ ዋጋ የከፈላችሁ ከታች እሰከ ላይ ባሉት ሁሉም የመጅሊስ እርከኖች ተገቢው ሰው እንዲመረጥ ትጉ።
እንዲሁም በመጅሊስ ስልጣን ላይ ያላችሁም ሆነ ወደ መጅሊስ መሪነት ለመምጣት ፍላጎቱ ያላችሁ ከዚህ አንጻር ራሳችሁን በመገምገም ጉዳዩ አማናና በአላህ ዘንድ ተጠያቂነት ያለበት መሆኑን በመረዳት የተሻለ ተቋም ለመገንባት የየበኩላችሁን ታሪካዊ ሚና እንድትወጡ እጠይቃለሁ።
በዚህ ረገድ ከፌደራል መጅሊስ የአሁኑ ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱህፋ አንስቶ እስከ የወረዳ መጅሊስ እርከን ያላችሁ ሁሉም የመጅሊስ አባላትና አመራሮች፥ የመጅሊስ ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት፥ እንዲሁም ለመመረጥ የመጅሊስን ደጅ እየጠናችሁና ቤት ለቤት ጥረት እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት፥ እንዲሁም የምርጫ ካርድ ያልወሳዳችሁም ሆነ የወሰዳችሁ እያንዳንዱ ሙስሊም መራጮች የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መሪ ድርጅት ከላይ የተጠቀሱትንና እናንተ የምታስቧቸውን ሚናዎች መወጣት የሚችል፥ የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት ያማከለና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የሚችል፥ የሀገርና የህዝብ ኩራት የሚሆን ጠንካራ ተቋም እዉን ለማድረግ የሚያግዙ
መሪዎችን ለመምረጥ ታሪካዊ ኃላፊነት በጫንቃችሁ ላይ ወድቋል።ስለሆነም ኃላፊነታችሁን ተወጡ!
ስለመጅሊስ ጽሑፌ ቀጥላል። አላህ ካለ በቀጣይ በተመሳሳይ የዑለማ ምክር ቤት ሚናና ተግበራት ጋር በተያያዘ ጽሑፍ እስክንገናኝ እሰከዚያው ቸር እንሰንብት!
https://t.me/Seyfel_Islam
ለመጅሊስ መሪነት ማንን እንምረጥ?
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
በአሕመዲን ጀበል
💢💢💢💢💢💢
ሕዝበ ሙስሊሙ የመሪ ተቋሙ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ምርጫ ላይ ይሆነኛል የሚለውን አካል በነጻነት መምረጥ ለድርድር የማይቀርብ መብቱ መሆኑ እሙን ነው። በዚህ ረገድ የሚመርጣቸው አካላት ምን እንዲያደርጉለት ይፈልጋል? የሚመርጣቸውስ ለምን ዓላማ ነው?
ሊመርጣቸው ያሰባቸው አካላትስ ያንን የሚያልመውን ዓላማውን እውን ማሳካት ይችላሉ ወይ? የሚለውን በአግባቢ ማየትና መለየት እጅግ ወሳኝ ይሆናል። ምክንያቱን መጅሊስንም ሆነ መሪዎቹ የሚፈለጉት የሕዝቡ ወኪል አገልጋይ ሆነውለት ከተቋሙ ሕዝበ ሙስሊሙ የሚፈልጋቸውን አገልግሎቶቹ በተገቢው መልኩ እንዲሰጡ ነውና። በመሆኑም መራጮች ይሆኑኛል የሚሉትን አካላት ሲመርጡ አልያም ለመመረጥ ያሰቡ ተመራጮችም ራሳቸውን ለቦታው ሲያጩ ስለተቋሙ ምንነት፥ የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት፥ስለሚጠበቅባቸው ሚና እንዲሁም የራሳቸውን አቅምና ብቃት ከግምት ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
በዚህ ጽሑፍ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤትን ምንነትና ሚናን ስለመጅሊስ በቂ ግንዛቤ ለሌላቸው ለማስገንዘብ ፥ግንዛቤው ላላቸው ደግሞ ለማስታወስ እሞክራለሁ።ይህም የመጅሊስን ራዕይ፥ ተልዕኮ፥ ግቦች፥ ዓላማዎችና ተግባራትን በማብራራት ይሆናል። መልካም ንባብ።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች(መጅሊስ) ራዕይ
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥
በሀገሪቱ ውስጥ በእስልምና መርሆች ላይ የተመሰረተ እና ለፍትህ፣ ለልማት እና ለአንድነት ቁርጠኛ የሆነ ሰላማዊ፣ ሁሉን ዓቀፍ እና በሃይማኖቱ የበለጸገ ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ማህበረሰብ ተፈጥሮ ማየት ።
የመጅሊስ ተልዕኮ
🏀🏀🏀🏀🏀
በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኘውን ሙስሊም ማህበረሰብ ኢስላማዊ አስተምህሮዎችን በማስፋፋት ፣የሃይማኖት መብቶችን በማስጠበቅ፣የማህበረሰብን ተጠቃሚነት በማጎልበት ለሀገሪቱ ሃይማኖታዊ፣ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት የመሪነት ሚናውን መወጣት።
የመጅሊስ ግቦች
🔮🔮🔮🔮🔮
1. የሃይማኖት ነፃነት እና እኩልነት በማስጠበቅ ከትንኮሳና ከአድሎ የራቀ ሰላማዊና የተረጋጋ ሕይወት ለሕዝበ ሙስሊሙ እውን እንዲሆን ማድረግ።
2. በመላው ኢትዮጵያ ኢስላማዊ ትምህርቶችን እና እሴቶችን ማሳደግ።
3. በሙስሊሞች መካከል አንድነት እና ትብብርን ማጠናከር።
4. የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማሳደግ።
5. የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት በብቃት ለመፍታት እንዲያስችል ተቋማዊ አቅምን ቀጣይነት ባለው መልኩ መገንባት።
የመጅሊስ ዓላማዎች
🌺🌺🌺🌺🌺🌺
1. ለሙስሊሞች መብቶች መከበር መቆም
🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅🍅
የህብረተሰቡን ሃይማኖታዊ እና ህዝባዊ ጥያቄዎችን ለመፍታት ከመንግስታዊ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ተባብሮ መስራት።
2. ትምህርት እና ግንዛቤ
📀📀📀📀📀📀📀📀
የኢስላማዊ ትምህርት ተደራሽነትን ለማሻሻል ኢስላማዊ ትምህርት ቤቶችን እና ማዕከላትን ማቋቋም፥ያሉትን ማጠናከር እና መደገፍ።
3. አንድነት እና ትብብርን ማጠንከር
🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁
በሙስሊሞች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር በማህበረሰቡ መካከል ውይይቶችን እና ዝግጅቶችን ማድረግ።
4. የበጎ አድራጎት ድርጊቶችንና ተቋማትን ማስተባበር
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶
የተቸገሩና ተጋላጭ የሆኑ ሙስሊሞችን ለመርዳት ተነሳሽነቶችን ማዘጋጀት።
5. ተቋማዊ ልማት
🆙🆙🆙🆙🆙
የአቅም ግንባታና የቴክኖሎጂ ትግበራ በማድረግ የምክር ቤቱን የአሰራር ቅልጥፍና ማሻሻል።
የመጅሊስ ስትራቴጂዎች
🌲🌲🌲🌲🌲🌲🌲
1. በሃይማኖታዊ፥ ማህበራዊ፥ኢኮኖሚያዊና ሀገራዊ ጉዳዮች የሕዝበ ሙስሊሙን ተሳትፎ የሚያጎለብቱ ዉጥኖችን ቀርጾ ንቅናቄን ማድረግ።
2. በሃይማኖታዊና ዓለማዊ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ሙስሊሞች በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ።
3. የመጅሊስ መዋቅርንና ሌሎች ኢስላማዊ ተቋማትን በሁለንተናዊ መልኩ የሕዝበ ሙስሊሙን ጥያቄዎች መመለስ እንዲችሉና ፍላጎት ማሟላት በሚችሉበት ቁመና ላይ እንዲገኙ ማጠናከር።
4. ሕዝበ ሙስሊሙ ከድህነት፥ ችግርና ችጋር፥ ኋላ ቀርነትና መሃይምነት የተላቀቀ የተሻለ ሕይወት መኖር እንዲያስችለው የሙስሊሞችን ኢኮኖሚያዊ አቅምና ደረጃን ማጎልበት።
5. በሀገሪቱ ሙስሊሞች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደሩ ያሉ አደናቃፊና ችግር ፈጣሪ የሆኑ ፖሊሲዎች፥ሕጎችና አሰራሮች እንዲለወጡ መስራት።
የመጅሊስ ተግባራት
🍀🍀🍀🍀🍀🍀
1. በኢትዮጵያ ዉስጥ የሃይማኖት ጉዳዮችን በየእርከኑ በተገቢው መልኩ መምራት።
2. የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ፍላጎትና መብት ማስጠበቅን ዓላማ ባደረገ መልኩ በሀገር ዉስጥም ሆነ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ሙስሊሞችን መወከል።
3. በዘወትር የሚደረጉ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በተገበው መልኩ ማስተዳደር።
4. የሙስሊሞችን መብቶችና ጥቅሞችን ማስጠበቅ።
5. የሕዝበ ሙስሊሙ ማህበራዊ ችግሮች እንዲቀረፉ የበጎ አድራጎት እና ማህበራዊ አገልግሎቶችን ማስተባበርና በተገቢው መልኩ መተግበር።
6. በኢትዮጵያ ያሉ ኢስላማዊ ቅርሶችና ታሪኮች እንዲጠበቁና እንዲታወቁ ማድረግ።
7. በሁለንተናዊ መልኩ ለሙስሊሙ ማህበረሰብና ተቋማት የአቅም ግንባታ ተግባራት መከወን።
8. የሕዝበ ሙስሊሙን አንድነት፥ ትብብርና ትስስር ማጎልበት የሚችሉ ተግባራትን መከወን።
9. በመላ ሀገሪቱ የሙስሊሞችን ማህበረሰባዊ ልማትን በተቀናጀ መልኩ መተግበር።
10. የሕዝበ ሙስሊሙን መብቶችንና ጥቅሞችን አሳልፎ በማይሰጥ መልኩ በሀገራዊና ሕዝባዊ ጉዳዮች ከመንግስት ጋር ተባብሮ መስራት።
በመጨረሻም!
🌹🌹🌹🌹🌹
ከላይ የተጠቀሱት የሕዝበ ሙስሊሙ መሪ ድርጅት የሆነው መጅሊስ በአስተዳደር ረገድ የሚጠበቅበትን ሚናን ለማብራራት የተሞከረበት ነው።እያንዳንዱ አንባቢ መጅሊስም ሆነ መጅሊሱን የሚመሩ አካላት ምን ዓይነት አገልግሎቶች እንዲሰጡት እንደሚፈልግ የየራሱን ሀሳብ እንደሚኖረው እገምታለሁ።በዚህ ላይ ይህንን ጽሑፍ መነሻ በማድረግ በጉዳዩ ላይ ዉይይት እያደረጉ ሀሳቡን ማዳብር እንዲሁም ከዚህ አንጻር ምን ዓይነት አመራሮችን ለመጀሊስ እንምረጥ? በሚል እየተወያዩ መዘጋጀት ተገቢ ይሆናል። በተይም የመጅሊስ ጉዳይ የሚያሳስባችና በመጅሊስ ጉዳይ ዋጋ የከፈላችሁ ከታች እሰከ ላይ ባሉት ሁሉም የመጅሊስ እርከኖች ተገቢው ሰው እንዲመረጥ ትጉ።
እንዲሁም በመጅሊስ ስልጣን ላይ ያላችሁም ሆነ ወደ መጅሊስ መሪነት ለመምጣት ፍላጎቱ ያላችሁ ከዚህ አንጻር ራሳችሁን በመገምገም ጉዳዩ አማናና በአላህ ዘንድ ተጠያቂነት ያለበት መሆኑን በመረዳት የተሻለ ተቋም ለመገንባት የየበኩላችሁን ታሪካዊ ሚና እንድትወጡ እጠይቃለሁ።
በዚህ ረገድ ከፌደራል መጅሊስ የአሁኑ ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱህፋ አንስቶ እስከ የወረዳ መጅሊስ እርከን ያላችሁ ሁሉም የመጅሊስ አባላትና አመራሮች፥ የመጅሊስ ምርጫ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት፥ እንዲሁም ለመመረጥ የመጅሊስን ደጅ እየጠናችሁና ቤት ለቤት ጥረት እያደረጋችሁ ያላችሁ አካላት፥ እንዲሁም የምርጫ ካርድ ያልወሳዳችሁም ሆነ የወሰዳችሁ እያንዳንዱ ሙስሊም መራጮች የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች መሪ ድርጅት ከላይ የተጠቀሱትንና እናንተ የምታስቧቸውን ሚናዎች መወጣት የሚችል፥ የሕዝበ ሙስሊሙን ፍላጎት ያማከለና ተገቢውን አገልግሎት መስጠት የሚችል፥ የሀገርና የህዝብ ኩራት የሚሆን ጠንካራ ተቋም እዉን ለማድረግ የሚያግዙ
መሪዎችን ለመምረጥ ታሪካዊ ኃላፊነት በጫንቃችሁ ላይ ወድቋል።ስለሆነም ኃላፊነታችሁን ተወጡ!
ስለመጅሊስ ጽሑፌ ቀጥላል። አላህ ካለ በቀጣይ በተመሳሳይ የዑለማ ምክር ቤት ሚናና ተግበራት ጋር በተያያዘ ጽሑፍ እስክንገናኝ እሰከዚያው ቸር እንሰንብት!
Comment
Share
Send as a message
Share on my page
Share in the group