UMMA TOKEN INVESTOR

About me

My name is Jemal Ahmed. I live in Addis Ababa, I'm a software engineer!

Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

بسم الله الرحمن الرحيم

المَوتُ بابٌ وَكُلُّ الناسِ داخِلُهُ

فَلَيتَ شِعرِيَ بَعدَ البابِ ما الدارُ

الدارُ جَنَّةُ خُلدٍ إِن عَمِلتَ بِما

يُرضي الإِلَهَ وَإِن قَصَّرتَ فَالنارُ

هُما مَحلاَّن ماللناس غيرهما

فانظُر لِنفسِك ماذا أنت تَخْتَار

ሞት በር ሲሆን ሁሉም ሰው ገቢው ነው

አይ ዋ ፀፀቴ ከሞትስ በኋላ ሀገሩ ምንድን ነው?

ስራችን ከሆነ አላህ የሚወደው

ሀገሩ ጀነት ነው አትክልት የሞላው

አላህን በማመፅ ከሆነ የኖርነው

ከሞትን በኋላ ሀገሩ እሳት ነው

ከሞት ኋላ ያሉት ሁለት ቦታ ናቸው

ጀነት ወይ ጀሐነም ሶስተኛ የልላቸው

ሌላ ቦታ ምርጫ ለሰወች የልላቸው

ለራስህ አስተውል የቱን ነው የመረጥከው?

ይሄ ሞት የሚሉት የማይዝዘጋ በር

ስንቱን ሰው ወሰደው እዚሁ እኛ ሰፈር

ስንቱን ወዳጅ ዘመድ አስገባ ከ-አፈር!!

ማምለጫ የሌለው የእኩልነት አድማስ

ሀብታም ድሀ ሳይል ሁሉን የሚያድዳርስ!!

ስንቱን ባለ-ጉልበት በቅፅበት የሚጥል

ደካማ ነው ብሎ ልለፈው የማይል

ሀብታም በገንዘቡ ሊያመልጠው የማይችል

ሞት አንገት ይደፋል ሁሉንም በእኩል!!

እድሜ ገደብ የለው መምጫው አይታወቅ

ድንገት ከተፍ-ብሎ አላማን የሚሰርቅ!!

አይ ሞት !!...

አይ ሞት... የሁሉ አባት፣የሁሉ ሰው ድርሻ

ኧረ ገና ልጅ ነኝ...ተብሎ የሌለው መሸሻ!!

ዛሬ... እኔን አልፎ ሰንቱን ሰው ጠለፈው

አልሃምዱሊላህ...አልኩ የዛሬን ቀን ሳልፈው

ግን ለካስ...ነገ ተራው የራሴ ነው!!

ሌላውን ሲወስድ ዛሬ እኔን ያለፈኝ

ነገ ሌላን አልፎ ራሴን ሊወስደኝ!!

የማይቀረው ቀኔ፣ ሞቴ የኔ ድርሻ

ጥም ቆራጩ ቀኔ የኔ መጨረሻ!!

ምን ማምለጫ አለኝ ኪታቡ ተፅፎ

ሞቴ ተወስኖ ሁሉ ነገር አልፎ!!

ብቻ ኢላሂ....

እኔ ከንቱ ሰው ነኝ እዝነትክን የምሻ

ከአንተ ራህመት ውጭ የሌለኝ መሸሻ!!

በዱኒያ ብልጭልጭ አይኔን የተነካሁ

በወንጀል ሰምጨ አኼራን የረሳሁ!!

ልበ-ደረቅ ሆኘ ምክር የማይገባኝ

ከአንተ አምልኮ ይልቅ ስሜት የማረከኝ

በወንጀል ሰምጨ ዱኒያ ያደከመኝ

ምህረትን ፈላጊ ደካማ ባሪያህ ነኝ

አወ ያ ኢላሂ.... ምህረት ፈላጊ ነኝ!!

ወንጀሌ ቢበዛም ከባህር አረፋ

ከጌታየ እዝነት እኔ አልቆርጥም ተስፋ!!

ምህረትህን ከጃይ ነኝ ሰነፉ ባሪያህ

ጌታየ ሸፍነኝ በሰፊው እዝነትህ!!

ከሞቱ አሟሟቱ እንደሚሉት አበው

ያአላህ፣ ያረቢ ሞቴን አሳምረው!!

መንገዲህን ምራኝ ሰጥተህ እስቲቃማ

ያረቢ ወፍቀኝ መልካሙን ኻቲማ!!

✍Ibnu Ahmed(አቡል_ፋሩቅ)

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

((يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَلْتَنظُرْ نَفْسٌ مَّا قَدَّمَتْ لِغَدٍ وَاتَّقُوا اللَّهَ إِنَّ اللَّهَ خَبِيرٌ بِمَا تَعْمَلُونَ))

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ማንኛይቱም ነፍስ ለነገ ያስቀደመችውን ትመልከት፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡ ሱራ አልሃሽር-18

አባት ለልጆቹ ለነገ ይቅርና ለወደፊት ሂዎታቸው የሚሆነ ሀብትን ለማስቀደም ዛሬ ደፋ ቀና ይላል።

እኛስ? ለነፍሳችን ምን አስቀድመናል? ያስቀደምነው መልካም ስራ አለን? አሁን ያለንበት ሁኔታስ እውነት ነፍሳችንን ለጀነት እጮኛ ያደርጋታል?ወይስ በወንጀል ውስጥ ሰምጠን ነፍሳችንን ለጀሐነም እሳት አጋልጠናታል?

"አላህ ፊት ቀርበን ከመመርመራችን በፊት ራሳችንን እንፈትሽ"!

ምክንያቱም:-

((فَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ خَيْرًا يَرَهُ))

የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

((وَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ شَرًّا يَرَهُ))

የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

" አላህ ፊት ቀርባችሁ ከመመርመራችሁ በፊት ራሳችሁን መርምሩ" ዑምር (رضي الله عنه)

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Ibnu Ahmed Сhanged his profile picture
6 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

بسم الله الرحمن الرحيم

የሰው ልጆች የተፈጠሩበትን አላማ አላህ በተከበረ ቃሉ እንዲህ ሲል ይነግረናል፣ الذاريات

((وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ))

"ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡"

በዚህም እኛ ሰዎች የተፈጠርንበት ብቸኛ አላማ አላህን በብቸኝነት ለማምለክ እንደሆነ እንረዳለን እንድሁም ዱኒያን ማከማቸት እና ለዱኒያ መኖር እኛ ሰዎች የተፈጠርንበት አላማ እንዳልሆነ እንረዳለን!! በዚህም የተፈጠረበትን አላማ ያሳካ የሆነ ለተፈጠረለት አላማ ኖሮ ዱኒያን ችላ ብሎ ጌታውን የተገናኘ ሰው ቀኑ ደርሶ ጠፊ የሆነችውን ዱኒያ ሲሰናበት ማረፈያው ጀነት ትሆናለች!! የተፈጠረለትን አላማ ዘንግቶ ጠፊ በሆነችው በዱኒያ ብልጭልጭ ተሸውዶ ጌታውን ችላ ያለ ሰው ደግሞ ቀኑ ደርሶ ዱኒያ ላይ ያከማቸውን የዱኒያ ብልጭልጭ ጥሎ በሚሞት ጊዜ ይህ ሰው መኖሪያው ጀሐነም ይሆናል ማለት ነው!!

👉👉👉👉የጀሐነም መገለጫዎች

👉## የጀሐነም እሳት ቃጠሎዋ በጣም አደገኛ ነው እኛ እዚህ ዱኒያ ላይ የምናውቀው እሳት ከጀሐነም እሳት ሰባኛው ክፍሏ እንደሆነ በሀድስ ተነግሯል!! ጌታችን አላህም እንድህ ይላል፣

((وَكَفَى بِجَهَنَّمَ سَعِيرًا))

"አቃጣይነትም በገሀነም በቃ፡፡" ሱራ አን-ኒሳእ-55

👉## የጀሐነም ምግብ ዘቁም የሚባል ዛፍ ሲሆን ይሄም ዛፍ ጣእሙ ይቅርና መልኩ ራሱ ለማየት የሚያስጠላ የሆነ

((لَّا يُسْمِنُ وَلَا يُغْنِي مِن جُوعٍ))

"የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡" ሱራ አልጋሲያህ-7

((إِنَّ شَجَرَتَ الزَّقُّومِ، طَعَامُ الْأَثِيمِ، كَالْمُهْلِ يَغْلِي فِي الْبُطُونِ ، كَغَلْيِ الْحَمِيمِ))

የዘቁመ ዛፍ፣የኀጢኣተኛው ምግብ ነው፡፡ እንደ ዘይት አተላ ነው፡፡ በሆዶች ውስጥ የሚፈላ ሲኾን፡፡እንደ ገነፈለ ውሃ አፈላል (የሚፈላ ሲኾን)፡፡ ሱራ አድ-ዱኻን 43-46

ከዚህ ዛፍ ጠብታ የዱኒያ ምድር ላይ ጠብ ብላ ብታርፍ የምድር ሰዎችን ኑሮ ባበላሸችባቸው ነበር ተብሏል በሀድስ!! ይህ ከመሆኑ ጋር ግን የጀሐነም ሰዎች ምግብ ይህ አስቀያሚ ዛፍ ነው!!

👉## የጀሐነም መጠጥ በሙቀቱ ብርታት ድካ የደረሰ የፈላ ውሃ እና የእሳት ሰዎች እዥ ሲሆን፣

((يُصَبُّ مِن فَوْقِ رُءُوسِهِمُ الْحَمِيمُ)) ((يُصْهَرُ بِهِ مَا فِي بُطُونِهِمْ وَالْجُلُودُ))

"ከራሶቻቸው በላይ የፈላ ውሃ ይምቧቧቸዋል:: በሆዶቻቸው ውስጥ ያሉ ቆዳዎቻቸውም በእርሱ ይቀለጣሉ፡፡" ሱራ አልሃጅ 19-20

👉## የቅጣቷ ክፋት የሰው ልጅ ሲስማው እንኳ ጤነኛ ኡእምሮ ካለው በርግጎ ወደጌታው እንድዋደቅ ያደርጋል።

((إِنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِنَا سَوْفَ نُصْلِيهِمْ نَارًا كُلَّمَا نَضِجَتْ جُلُودُهُم بَدَّلْنَاهُمْ جُلُودًا غَيْرَهَا لِيَذُوقُوا الْعَذَابَ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَزِيزًا حَكِيمًا))

እነዚያን በተአምራታችን የካዱትን በእርግጥ እሳትን እናገባቸዋለን፡፡ ስቃይን እንዲቀምሱ ቆዳዎቻቸው በተቃጠሉ ቁጥር ሌሎችን ቆዳዎች እንለውጥላቸዋለን፡፡ አላህ አሸናፊ ጥበበኛ ነውና፡፡ አን-ኒሳእ-56

እንግድህ የጀሐነም ቅጣት እንድህ ነው ቆዳዎች በቃጠሎው እርር እንኩትኩት ባለ ቁጥር ሌላ ቆዳ ይቀየርላቸዋል ይህም የቅጣቱን አስከፊነት እንዲቀምሱ ነው!!

አላህ እኔንም ሙስሊሞችንም ከዚች አስከፊ ጀሐነም ይጠብቀን!! አሚን

6 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group