Abuamar Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Abuamar пайларӗ
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

ሐማስ አቅሙን ሳያውቅ ለምን ወደ ጦርነት ገባ⁉️

================================

✍ ዛሬ ሸይኽ ኢልያስ አሕመድ በኢማሙ አሕመድ መስጅድ በነበረው የፈታዋ ፕሮግራም ላይ «ያለ አቅም ጦርነት መጀመር እንደት ይታያል? ጥቅምና ጉዳትን ማመዛን አይገባም ወይ?» የሚል ይዘት ያለው ጥያቄ ተጠይቆ ነበር። ያው የጥያቄው ዐውድ ወቅታዊውን የሐማስና የእስራኤል ጉዳይ እንደሚያሳይ ግልፅ ይመስለኛል።

ሸይኹም ጠያቂው ከዚህ ተጨባጭ ጋር ማያያዝ እንደፈለገ ስለተረዳ በዚያው አውድ ነው ምላሹን የሰጠው። ይህ ጥያቄ ብዙዎቻችሁ ጋር እንደሚፈጠር ስለገመትኩና እዚሁ ማኅበራዊ ሚዲያም ላይ አልፎ አልፎ ስላጋጠመኝ፤ ቃል በቃል ባይሆንም በይዘት ደረጃ መልሱን ላካፍላችሁ።

√ በመጀመሪያ ደረጃ አንድ ሰው አቅሙ የማይችለውን ነገር ነፍስያውን ማሸከም እንደሌለበት ሓዲሥ አጣቅሶ ካስረዳ በኋላ ጥቅምና ጉዳትን አመዛዝኖ መወሰንም ተገቢ ሸሪዓዊ መርህ መሆኑን ተናግሯል። ይህ የወል እውነታ እንዳለ ሆኖ፤ ነገር ግን ዝርዝር መረጃ በሌለን ጉዳይ ላይ ይህን መርህ እንደወረደ ተግባራዊ አድርጎ ብይን መስጠት ተገቢ አይደለም።

ማለትም በሩቅ ሆነን በሚዲያ በሰማነው ብቻ ተመርኩዘን ሐማስ ጥፋተኛ ነው አንልም። ምናልባትም ሌሎች ሃገሮች እናግዝሃለን ብለው ቃል ገብተውለት በኋላ ከድተውት ሊሆን ይችላል፣ (ወይም ወራ'ሪዋ የተለመደውን ጥቃቱን ልትፈጽምበት መዘጋጀቷን አውቆ ቀድሞ ራሱን ለመከላከል ይሆናል… ብቻ አላሁ አዕለም)።

እንደ ጥቅል ደግሞ መታወቅ ያለበት ነገር ሐማስ ያኔ ኦክቶበር 7 ጥቃት ባይፈጽምም ወራ'ሪዋ ፈለስጢናዊያንን ከማጥቃት አልተወገደችም። ጋዛንም ላለፉት 16 አመታት ገደማ በሽቦ አጥርና በኮንክሪት ዙሪያዋን አጥራ ያለርሷ ፈቃድ ጋዛዊያን መውጣትም ሆነ መግባት አይችሉም። ይህም ጋዛ ጣራ የሌለው የዓለማችን ክፍት እስር ቤት ነው፤ ምዕራባዊያን ራሳቸው ይሄን ያምናሉ።

የወራ'ሪዋ ጋዛዊያንንም ሆነ መላው ፈለስጢናዊያንን የማጥ'ፋትና ከምድራቸው የማስወገድ እቅድ ባለፈ የተጀመረ ሳይሆን ገና ከ1948 በፊት የነበረና ተጠናቅሮ የቀጠለ ፖሊሲ ነው። ስለዚህ ሐማስ ጥቃቱን ጀመረም አልጀመረም ጭካኔዋ የነበረና ያለ ነው።

በቅርበትና በተጨባጩ መረጃ ሳይኖረን ብይን መስጠት የማይገባን መሆኑ እንዳለ ሆኖ ጥፋተኛ ነው ብንል እንኳ ይሄን የቁርኣን አንቀፅ እናስታውስ።

(يَسْأَلُونَكَ عَنِ الشَّهْرِ الْحَرَامِ قِتَالٍ فِيهِ ۖ قُلْ قِتَالٌ فِيهِ كَبِيرٌ ۖ وَصَدٌّ عَن سَبِيلِ اللَّهِ وَكُفْرٌ بِهِ وَالْمَسْجِدِ الْحَرَامِ وَإِخْرَاجُ أَهْلِهِ مِنْهُ أَكْبَرُ عِندَ اللَّهِ ۚ وَالْفِتْنَةُ أَكْبَرُ مِنَ الْقَتْلِ ۗ وَلَا يَزَالُونَ يُقَاتِلُونَكُمْ حَتَّىٰ يَرُدُّوكُمْ عَن دِينِكُمْ إِنِ اسْتَطَاعُوا ۚ …)

"ከተከበረው ወር (ከረጀብ) በርሱ ውስጥ ከመጋደል ይጠይቁሃል፡፡ በላቸው «በርሱ ውስጥ መጋደል ታላቅ (ኀጢአት) ነው፡፡ ግን ከአላህ መንገድ (ሰዎችን) መከላከል፣ በርሱም መካድ፣ ከተከበረውም መስጊድ (ማገድ) ባለቤቶቹንም ከርሱ ማውጣት አላህ ዘንድ ይበልጥ ታላቅ (ወንጀል) ነው፡፡ ፈተናም (ማጋራት) ከመግደል ይበልጥ ከባድ ነው፡፡ (ከሐዲዎች) ቢችሉ ከሃይማኖታችሁ እስከሚመልሳችሁ ድረስ የሚዋጉዋችሁ ከመሆን አይቦዝኑም፡፡…»"

[አል-በቀረህ: 217]

*

√ ጁንዱብ ኢብኑ ዐብደልሏህ ባስተላለፈው ሓዲሥ ላይ፣ ከኢብኑ ዐባስ፣ ከኢብኑ መስዑድና ከዑርዋህ ቢን ዙበይር እንደተዘገበው፤ የዚህ የቁርኣን አንቀፅ የወረደበት ሰበብ፤ ዐብደልሏህ ኢብኑ ጀሕሽ የተባለ ሶሐባ ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር ሆኖ በጧኢፍና በመካህ መካከል ወደምትገኘው ነኽላህ ቁረይሾችን ለመሰለል በውዱ ነቢይ በተላከ ጊዜ መንገዳቸው ላይ ጥፋተኞቹን የቁረይሽ ቅፍለቶች ሲያገኙ ጦር ወረወሩባቸውና ዐምር አል-ሐዽረሚይን ገድ'ለው፤ ኡስርዋ ዑሥማንንና ሐከም ከይሳንን ማረኳቸው።

ታዲያ የዚህን ጊዜ ወሩ የወርሃ ረጀብ የመጀመሪያ ቀን ነበር። ከጁማዱል ኣኺር የመጨረሻ ቀን መስሏቸው ነበርም ተብሏል። ብቻ ወደ ውዱ ነቢይ ተመለሱና ስለሆነው ነገር ሲነግሯቸው፤ ውዱ ነቢይ ጭራሽ በረጀብ ወር እኔ ሰልላችሁ ኑ አልኩ እንጂ ግደ'ሉ ብያለሁ እንደ ብለው ገሰጿቸው።

የቁረይሽ ሙሽሪኮችም «ሙስሊሞች በተከበሩት ወራት (ረጀብ ከተከበሩት ወራት መካከል ስለሆነ) አንጋደልም ይላሉ እንጂ ይሄ ገደሉ አይደል እንደ?» እያሉ ማስወራት ጀመሩ። በነርሱ ቤት ማነወራቸው ነው።

አላህም ይህን ምላሽ ሰጣቸው።

ምንም እንኳ በተከበሩት ወራት መጋ'ደል እርም ቢሆንም፤ ግን ከአላህ መንገድ (ሰዎችን) ከመከላከል፣ በርሱም ከመካድ፣ ከተከበረውም መስጊድ (ከማገድ)፣ ባለቤቶቹንም ከርሱ ከማውጣት አይበልጥም አላቸው።  አላህ ዘንድ ይበልጥ ታላቅ (ወንጀል) የናንተ ይህ ሥራችሁ ነው አላቸው፡፡ እናንተ ያላችሁበት ፈተና (በአላህ ላይ ማጋራት) ከመግ'ደል ይበልጥ ከባድ ነው ብሎ መለሰላቸው፡፡

ወደ እኛ ጉዳይ ስናመጣው፤ እንደው ሐማስ አቅምን ካለማወቅና ጥቅምን ከጉዳት ካለማመዛዘን አንፃር ጥፋተኛ ነው ብንል እንኳ (ማለት የለብንም)፤ አይሁዳዊያን እየሠሩት ካለው ግፍ፣ ወረራ፣ ፈሳድ… አንፃር የነርሱ ጥፋት ይበልጥ የከበደ ወንጀል ነው።

በዚህ መስክ እየተገ'ደሉ ያሉ የፈለስጢን ወንድሞቻችን በነፍስ ወከፍ ደረጃ ይሄ ነው ይሄ ነው ባንልም በደፈናው ግን አላህ ከሸሂዶች ጎራ እንደሚመድባቸው ተስፋ እናደርጋለን ብሏል። አላህ ይቀበላቸው፤ ድልንም ያቀዳጃቸው።

እኛም እየሆነ ባለው ነገር ከማዘን የተነሳ ተስፋ መቁረጥ ሳይገባን መጨረሻ ላይ ዲሉ የእኛ መሆኑ በቁርኣንና በሓዲሥ ስለተነገረ በዱዓእ እየበረታን ተስፋችንን ልናለመልም ይገባል፤ ምናልባትም አላህ አይሁዶችን በአሁኑ ወቅት አንድ ቦታ ላይ እንዲሰበሰቡ ያደረጋቸው በቁርኣን ላይ ለተነገረው ቃሉ ሊጠፉ ተቃርበውም ይሆናል የሚል ይዘት ያለው መልዕክት ሲናገር ሰምቻለሁ።

አላሁ አዕለም!

(የቁርኣን አንቀፁን ሰበበ ኑዙል ማንበብ ለምትፈልጉ፦

«جامع البيان» (3/ 650- 660)، و«تفسير ابن أبي حاتم» (2/ 384- 386)، و«أسباب النزول» للواحدي، (ص41)، و«السيرة النبوية» لابن هشام (1/ 601- 605)، و«دلائل النبوة» للبيهقي (3/ 18، 19)، و«تفسير ابن كثير» (1/ 368- 372).)

||

Via: murad tadesse

image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
Abuamar пайларӗ
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

ስለ የሁዳዎች ክፋት ከማንም በላይ የሚያውቀው አላህ ብቻ ነው።ለዚህም የቁርኣን ታሪክ አብዛኛው ስለየሁዳዎች ነው።በመቀጠልም ረሱልﷺ ናቸው። በመዲና ውስጥ አብረዋቸው ኖረዋል። ተንከሲስነታቸውንም ተገንዝበው የሚባረረውን አባርረው የሚገደለውን ገድለው ከመዲና አስወግደዋቸዋል።

ይሄ ኡማ የረሱሉን ሲራ ስለማያውቅ  የየሁዳዎችን ማንነት ጠንቅቆ በመረዳት ረገድ ካሀዲውን ሂትለር አርአያው ያደርጋል።

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
7 уйӑх Куҫарас
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

⏱‏( ساعة إجابة كل ليلة )

🖋قالﷺ:" إن في الليل لساعة،لا يوافقها رجل مسلم يسأل الله خيرا من أمر الدنيا والآخرة إلا أعطاه إياه، وذلك كل ليلة"

📗أخرجه مسلم في "صحيحه"(٧٥٧)

📝قال #النووي : "فيه إثبات ساعة الإجابة في كل ليلة، ويتضمن الحث على الدعاء في جميع ساعات الليل رجاء مصادفتها"

#منبه_الطاعات

#وبستان_العبادات

#قيام_الليل_

#الوتر_جنة_القلوب

منقول...

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
Abuamar пайларӗ
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

ዛሬ የጉራጌ ዞኗ አስኩት በነዚህ ውብ ሐፊዞቿ ምርቃት ፍክት ብላ ውላለች።

በጉራጌ ዞን ጌቶ ወረዳ እስኩት ከተማ የሚገኘው ዑመር መርከዝ ላለፉት ተከታታት 3 አመታት ያክል የአላህን ቃል ቁርኣንን የሐፈዙ እና መሠረታዊ የዲን ትምህርቶችን የተማሩ ተማሪዎችን አስተምሮ ለማኅበረሰቡ አበርክቷል።

በአካባቢወወ ያለው ማኅበረሰብ መሠረታዊ የዲን ትምህርት ላይ እጅግ በጣም ክፍተት ያለበት እና ብዙ ሥራዎች የሚጠይቅ ቦታ በመሆኑ ይህን የመልካም ሥራ ፍሬ ማየት በጣም የሚያስደስት ነው። ለዚህ ሰበብ የሆናችሁ ሁሉ አላህ ኢኽላሱን ሰጥቶ ምንዳችሁን ከፍ ያድርገው። አላህ ይቀበላችሁ።

መሰል መልካም ተግባራት ሊጠናከሩና ሊበዙ ይገባል። ማሻ አላህ!

image
image
Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас
Abuamar пайларӗ
Çĕнĕ çулахне йывăçлăх

Assalamu alaykum, brothers and sisters!

Since we have received many Muslims from Ethiopia and other Arabic countries on our social network in recent days, our team has decided to add another language — Amharic. If any of you are translators or those willing to help with translations into the Amharic language, please write to us in a private message at the link: 👉 https://ummalife.com/ummalife.

አሰላሙ አላይኩም፣ እኅቶችና ወንድሞች!

ከቅርብ ጊዜያት ጀምሮ በሶሻል ኔትወርክችን ላይ ከኢትዮጵያ እና ከሌሎች ዓረብ ሀገሮች ብዙ ሙስሊሞችን ስንቀበል፣ ቡድናችን አማርኛ ቋንቋ እንዲጨመር ወስኗል። ከእናንተ መካከል ማንኛውም አስተርጓሚ ወይም በአማርኛ ትርጉም ላይ መረዳት የሚፈልጉ ከሆኑ፣ እባኮትን በሚከተለው ሊንክ በግል መልእክት ይጻፉልን፡

👉 https://ummalife.com/ummalife.

Хыпар пек ярас
Ман тетелӗ питра пайлас
Ушкӑнта пайлас