UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ምርጥ ተውበት !

የ ታላቁ አሊም ማሊክ ኢብን ዲናር የተውበት ታሪክ 🍃

 ማሊክ ኢብን ዲናር ህይወታቸውን በስካር በመጠጥ ነበር የጀመሩት፣ከዛም በአንድ ግዜ አግብተው ልጅ መውለድ ተመኙ አናም አገቡም አላህ 1ሴት ልጅ ሰጣቸው ስሟንም ፋጢማ አሏት። የዛኔ ልባቸው ወደ ኢማን እየተቃረበ መጣ ውጪ ይጠጡ የነበረውን ቤት መጠጣት ጀመሩ። ፋጢማንም ጭናቸው ላይ አድርገው ነበር የሚጠጡት፣አንድ ቀን ፋጢማ በ2 አመቷ እያለ መጠጡን ገፍታ ደፋችባቸው የዛኔ ይህ አላህ በፋጢማ ተው እያለኝ ነው ብለው አሰቡ፣ ከአመት በኃላም ፋጢማ 3አመት ሞላት ከዛም ፋጢማ ሞተች። ከዛም ድጋሚ እንደበፊቱ መጠጣት መስከር ጀመሩ፣ ታዲያ አንድ ቀን ሸይጧን ወሰወሰኝ አሉ ዛሬ ሰክረኸው የማታውቀውን ስካር ነው የምትሰከረው አለኝ እሺ ብየ መጠጥ መጠጣት ጀመርኩ በጣም ሰከሬ ወደኩ አሉ ። ከዚያም በህልሜ ቂያማ የቆመ መሰለኝ ፀሀይቱ ጠቁራለች፣ ሰወ ሁሉ አላህ ፊት ተሰብስቧል፣ባህሩ ይነዳል የሰው ሁላ ስም ሲጠራ ቆየና ማሊክ ኢብኑ ዲናር ና ለሂሳብ ትፈለጋለህ ተባልኩ ከዛም ትልቅ ዘንዶ ማሳደድ ጀመረኝ እሱን  ለመሸሽ ሰሮጥ አንድ ሽማግሌ አገኙሁ አግዘኝም አልኩት እኔ አቅሜ ደካማ ነው አለኝ ሰሮጥ የእሳት ጫፍ ላይ ደረስኩ፣ ዘንዶውን ፈርቼማ አሳት አልገባም ብየ ተመልሼ ሮጥኩ ድጋሚም ሽማግሌውን አገኙሁት አግዘኝም አልኩት አቅሜ ደካማ ነው እስቲ የምትድን ከሆነ ወደዛ ተራራ ሩጥ አለኝ። ከዚህም እየሮጥኩ እያለ  ከተራራው ላይ ህፃኖች ፋጢማ አባትሽን ዘንዶ ሊበላው ነው ሲሉ ሰማሁ ። ለካ በ 3 አመቷ የሞተች ልጅ አለችኝ ብየ ወደ ፋጢማ ሮጥኩ ፋጢማም ዘንዶውን ገፍታ ጣለችው። እኔም ልጄ ሆይ እስቲ ያ ዘንዶ ምንድነው የሚያባረኝ አልኳት እሷም ያ መጥፎ ስራህ ነው አለችኝ እሺ ያ ሽማግሌውስ ያ ጥሩ ስራህ ነው አለችኝ ጥሩ ስራህ ደካማ ሰለሆነ ከመጥፎ ስራህ ሊያስጥልህ አልቻለም አለችኝ። ከዛም 1የቁርአን አያ ቀራችልኝ።

"እነዛ ምእመናን ልባቸው ለአላህ ግሳፄ የሚፈራበት ግዜ አልደረሰምን?" የሚለውን አነበበችልኝ ። ልክ አኔም ከእንቅልፌ አዎ ግዜው ደርሷል አያልኩ እያለቀስኩ ተነሳሁ ሻወር ወሰድኩ ሱብሂ ወደ መስጂድም ሄድኩ። መስጂድም ኢማሙ ይህንኑ አያ እየቀሩት ነበር አልቅሼ ተመለስኩ ይሉናል ታላቁ ኢማም።

እኝህ ሰው ህዝቡን የሚያስተምሩ ታላቅ ኢማም ሆኑ። ሁሌም መስጂድ አንተ አላህን ያመፅክ ባሪያ ሆይ ወደ ጌታህ ተመለስ ይሉ ነበር።

‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌‌copy

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

🗞ከምርጦቹ አንደበት🗞

{ዝምታም ጥበብ ነው...}

"ጥበብ አስር ክፍሎች አሉት ከአስሩ ዘጠኙን ሚያጠቃልለው ዝምታ ነው ፤ አንዱ ደግሞ ከሰዎች ገለል ማለት ነው"

ዉሀይብ ኢብኑል ወርድ

📖አሰምት ሊብኒ አቢዱንያ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#ለታሪክ ይቀመጥ!

👌ለሸሀዳ የተቀሰረች ጣት

ከፍርስራሽ መሐል ቦግ ብላ የምታበራ ጣት !የእሳት አረሩ ያላጠፋት የድሮን ቦንብ ያላደበዘዛት አመላካች ጣት

ኣጃዒብ እኔስ ቃል ያጥረኛል

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የለሊት ሶላት እና የአሰጋገድ ሁኔታው‼️

▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬

✍ሶላት በእስልምና ዋነኛው

አላህ በባሮቹ ላይ የደነገገው ተግባር ነው።

||

የሌሊት ሶላት አንዱ የተረጋገጠ ሱና እና ትልቅ ፋይዳ ያለውና ከምርጥ ኢባዳዎች አንዱ ነው ከሌሊቱ መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ሱብሒ ሶላት ድረስ ከመስገድ በፊት በመጨረሻው አንድ ሶስተኛው ላይ ቢገኝ ይመረጣል።

*

የለሊት ሶላት እና አሰጋገዱ:

✔️ በየሁለት ረከዓው እያሰላመቱ የቻሉትን የፈለጉትን ያክል ይሰግዱና መጨረሻ ላይ አንድ ረከዓ ብቻ በመጨመር በዊትር ያጠናቅቃሉ።

*

የ"ለይል" (ለሊት) ሶላት ተብሎ በውስጥ "ተነይቶ" (ታስቦ) ፋቲሓ ይቀራል።

ከፋቲሓ በኋላ የቻሉትን ሱራ ይቀራል። "ሓፊዝ የሆነ ስው በሒፍዙ አርዝሞ ይቀራል፤ "ሓፊዝ ያልሆነ ስው የሚችለውን ይደጋግማል ካልሆነ ደግሞ ቁርኣን ይዞ መቅራት ይችላል።

በዚህ መልኩ ሁለት ረከዓ ከሰገዱ በኋላ - እንደ "ቀብልያ"፣ "ባዕዲያ" ሱንና ሶላቶች ማለት ነው - አተሕያቱ ቀርተው ማሰላመት ነው።

°

✅ ከዛም በኋላ በዚሁ መስረት የቻሉትን ያክል ሁለት ሁለት ረከዓ እየሰገዱ አስርም ይሁን፣ አስራ ሁለትም፣ አስራ አራትም፣ አስራ ስድስትም፣ ሃያ እና ሃያ ሁለትም ሰግደው  መጨረሻ ላይ አንድ ነጠላ ቁጥር በመስገድ ዊትር አድርገው ማጠናቀቅ።

ዊትር ማለት ደግሞ ኢ—ተጋማሽ ቁጥሮች ማለት ነው (1፣3፣5፣7...) ማለትም 1 ረካዓ ሰግደው ተሽሁድን በመቅራት ሶላቱን ዊተር አድርገው ማጠናቀቅ ይችላሉ።

:

እንደው ጠቅለል ሲደረግ ሶላተል-ለይል ማለት ከኢሻ በኃላ እስከ ፈጅር ድረስ ባለው ወቅት ውስጥ የሚሰገድ፣ ቁርአን በዛ ተደርጎ የሚቀራበት ትርፍ የሆነ የሌሊት ሶላት ሲሆን ይህ ሶላት ተራዊህ ወይም ተሀጁድ ተብሎ ሊጠራ ይችላል።

:

ለዛም ነው የሌሊቱ መጀመሪያም ይሁን መካከል ይሁን መጨረሻ ላይ መስገድ ቢቻልም በላጩ ግን የሌሊቱ የመጨረሻው አንድ ሶስተኛ ላይ መስገድ በላጭ ነው።

*

ምክንያቱም በዚህ ወቅት በሀዲስ እንደተገለፀው አላህ ወደ ቅርቢቱ ሰማይ የሚወርድበትና "ማን ነው የሚለምነኝ የምቀበለው⁉️ ማን ነው የሚጠይቀኝ የምሰጠው⁉️  ማን ነው ማሀርታን የሚጠይቀኝ የምምረው⁉️" የሚልበት ሰአት በመሆኑና በርካታ ኡለሞች ዘንድ ከተኙ ቡኃላ ተነስቶ መስገድ በላጭ ስለሆነ ይህን ሱና ለማግኘት ሲባል ነው።

ﻳَﻨْﺰِﻝُ ﺭَﺑُّﻨﺎ ﺗَﺒﺎﺭَﻙَ ﻭﺗَﻌﺎﻟَﻰ ﻛُﻞَّ ﻟَﻴْﻠﺔٍ ﺇﻟﻰ ﺍﻟﺴَّﻤﺎﺀِ ﺍﻟﺪُّﻧْﻴﺎ ﺣِﻴﻦَ ﻳَﺒْﻘَﻰ ﺛُﻠُﺚُ ﺍﻟﻠَّﻴْﻞِ ﺍﻵﺧِﺮُ، ﻳﻘﻮﻝُ : ﻣَﻦ ﻳَﺪْﻋُﻮﻧِﻲ، ﻓﺄﺳْﺘَﺠِﻴﺐَ ﻟﻪ؟ ﻣَﻦ ﻳَﺴْﺄَﻟُﻨِﻲ ﻓﺄُﻋْﻄِﻴَﻪُ؟ ﻣَﻦ ﻳَﺴﺘَﻐْﻔِﺮُﻧﻲ ﻓﺄﻏْﻔِﺮَ ﻟﻪ؟

ﺍﻟﺮﺍﻭﻱ : ﺃﺑﻮ ﻫﺮﻳﺮﺓ - ﺍﻟﻤﺤﺪﺙ :

ﺍﻟﻤﺼﺪﺭ : ﺻﺤﻴﺢ

📒ﻣﺴﻠم ‏(758)

በተጨማሪም ይህ የቁርአን አንቀፅ የሚያመለክተው ሁሉንም የሌሊት ሶላቶች ነው።

”وَمِنَ اللَّيْلِ فَتَهَجَّدْ بِهِ نَافِلَةً لَّكَ عَسَىٰ أَن يَبْعَثَكَ رَبُّكَ مَقَامًا مَّحْمُودًا“

"ከሌሊትም ላንተ ተጨማሪ የሆነችን ሶላት በርሱ (በቁርአን) ስገድ፣ ጌታህ ምስጉን በሆነ ስፍራ በእርግጥ ያቆምሃል።"

📒ሱረቱል ኢስራእ [79]

*

በመጨረሻም እስከ ሌሊቱ አጋማሽ በሗላ (ማለትም ከ 7 ሰዐት በሗላ) እንቅልፍ በተለያዩ ስራዎችና ምክንያቶች ሳትተኙ ከቀራችሁ ሁለት ረካዓና አንድ ውትር ወትራችሁ ሀጃም ያላችሁ ዱዓችሁን አድርጋችሁ ብትተኙ ለስኬታችሁ ቁልፍ፣ ለኢማናችሁ ትርፍ፣ ወንጀልን ለማርገፍ፣ ለጭንቃችሁ መውጫ እና ከአላህ ጋር ያላችሁን ግንኙነት ለማጠናከር የተመረጠ ግዜ ነውና ተጠቀሙበት።

||

ይህንን ያነበባችሁ ወንድምና እህቶች በሙሉ:-

ሌሎች አንብበው ከሰገዱ የአጅሩ ተካፋይ ናችሁና፤ መልክቱን ለሌሎችም እንዲደርስ ሁላችሁም ሼር አድርጉት‼️

||

የቴሌግራም ቻናል:

t.me/AbuHiba

Send as a message
Share on my page
Share in the group