meksud jemal Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

meksud jemal shared a
ترجمہ ممکن نہیں

الـــــــــسلام علــــــيكم ورحمة الله وبركاته🏝🍒🍃

~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

👉 እናንተ በሌሊት እና ቀን ማለፍ ዉስጥ ናችሁ!

እድሜያችሁ እየቀነሰነዉ።

ስራችሁ እየተመዘገበነዉ።

ሞት ድንገት ይመጣል።

መልካም የዘራ መልካም ያጭዳል።

መጥፎ የዘራ ፀፀት ያጭዳል።

ሁሉም የዘራዉን ብቻ ነዉ የሚያጭደዉ።

የዘገየ ድርሻዉ አያመልጠዉም።

የፈጠነም ከተወሰነለት ዉጭ አያገኝም።

መልካም ያገኝ አላህ ሰጠዉ።

ከመጥፎ የተጠበቀ አላህ ጠበቀዉ።

በመጥፎ ነገር ከፊት ከምትሆን ፣

በመልካም ነገር ከኋላ ሁን።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
meksud jemal shared a
ترجمہ ممکن نہیں

አጂብ የሆነ ታሪክ

--------//----------

ነብዩላህ ዳውድ በዙፋናቸው ላይ ተቀምጠው ሳለ አንዲት ሴት መጣችና

ጌታህ ፍትሀዊ ነው ወይስ በዳይ ብላ ጠየቀቻቸው?

እኔ አባታቸው የሞተባቸውን ( 3 ) የቲም ልጆችን አሳድጋለሁ። ጉሮሮዋቸውን

የምደፍነውም ጥጥ በመፍተልና በመሸጥ ከማገኘው ገንዘብ ነው።

ዛሬ ግን ጥጤን ፈትዬ በጨርቅ ከረጢት ቋጥሬ ልመሸጥ ወደ ገበያ በመሄድ

ላይ ሳለሁ አንድ አሞራ ልሸጥ የቋጠርኩትን ጥጥ ይዞብኝ በረረ።

አሁን ለልጆቼ ዳቦ መግዣ አጣሁ ልጆቼ በረሀብ እየተንገላቱ ነው ብላ

ንግግሯን ሣትጨርስ..... በሩ ተንኳኳ ፍቃድ ተሠጣቸውና ወደ ውስጥ ገቡ።

በሩን ያንኳኩት 10 ነጋዴዎች ነበሩ። በእጃቸው አንድ ሺህ ዲናር ይዘዋል

ከመሀከላቸው አንዱ መናገር ጀመረ

አንቱ የአላህ ነብይ ሆይ! ባህር ላይ እየተጓዝን ሳለ መርከባችን መስመጥ

ጀመረች ሞታችንን በመጠባበቅ ላይ ሳለን አንድ አሞራ በጨርቅ የተቋጠረ

የጥጥ ፈትል ከላይ ጣለልን በጨርቁም ቀዳዳውን ደፈንን መርከባችንም

ከመስመጥ ይልቅ ወደ ላይ ተንሳፈፈ በአላህ ፍቃድ ከሞት ዳንን አላህ ለዋለልን

ውለታ ምስጋና ይሆን ዘንድ እያንዳዳችን መቶ ዲናር በድምሩ አንድ ሺህ ዲናር

ለመስጠት ቃል ገባን እና ይህው ገንዘባችን ለፈለጉት ሠው ሠደቃ ይሥጡት

በማለት ብሩን እንዲቀበሏቸው እጃቸውን ዘረጉ።

ነብዩላሂ ዳውድም ወደ ሴትየዋ በመዞር << ጌታሽ አንቺን ከድካም አሳርፎ

በየብስና በባህር ይነግድልሻል አንቺ ግን በዳይ ትይዋለሽ በይ ገንዘቡን

ተቀብለሽ ይዘሽ ሂጂ>> በማለት አዘዟት

ሴትየዋም በተናገረችው ቃል እየተፀፀተች ውስጧ በደስታ ተሞልቶ መንገዷን ቀጠለች።

ስንቶቻችን ነን የምንቀበለውን ሳናውቅ ባጣነው ነገር ፈጣሪያችንን

የምናማርረው? መልእክቱን ከወደዱት ለወዳጅ ዘመዶዎ ሼር ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
meksud jemal shared a
ترجمہ ممکن نہیں

🇵🇸ሩቅ አይደለም!!

💫ነብዩ ኢብራሂምﷺ እጅ እና እግራቸው ጠፍረው እሳት ውስጥ የወረወሯቸው ሰዎች በዝያች ቅፅበት አላህ አላጠፋቸውም።

💫ፊርዓውን "እኔ ጌታችሁ ነኝ" እያለ ያልተቀበሉት ሰዎች ሰውነታቸው ቆራርጦ ሰቅሎ እየገደለ ሲያሰቃያቸው በዝያች ቅፅበት አላህ አላጠፋውም።

💫አላህ ከሰማይ መልእክት እያወረደላቸው "ጌታችሁ አላህ ነው, ተገዙት" ያሉ ነብያቶች የገደሉ ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።

💫"ጌታችን አላህ ነው, በእሱም አምነናል።" በማለታቸው ብቻ ጎድጓድ ቆፍረው እሳት አንድደው ያቃጠሏቸው “አስሀብ አል_ኡኽዱድ” አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።

💫ለዓለማት እዝነት ተደርገው የተላኩት ውዱ ነብይﷺ ጀርባ ላይ ፈርስ እየጣሉ፣ በተደጋጋሚም የግድያ ሙከራ ያደረጉ ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።

💫አላህ ከፈጠረው ሁሉ በላጭና ክቡር የሆኑት ነብዩﷺን ጦር ሜዳ ላይ ገጥመው ጭንቅላታቸው እስኪደማ የተዋጉዋቸው ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።

💫ቀራሚጣዎች ጀናዛ የያዙ አስመስለው ሰይፋቸው በከፈን ሸፍነው ወደ ኻረም ካስገቡ በኋላ በአንድ ጀምበር ብቻ ከሶስት ሺህ (3000) በላይ ሑጃጆች ገድለው፣ የዘምዘም ውሃ በሑጃጆች ጀናዛ ደፍነው፣ የተከበረው የካዕባ ሽፋን በጣጥሰው፣ መሪያቸው ከፍታ ላይ ቆሞ “የዛሬው ንግስና ለማን ነው?” እያለ ሲፎክር፣ “ጠይረል አባቢል የት አሉ? ሂጃራ ሚን ሲጂል የት አለች?” እያለ ሲፎክር፣ ሱረቱል ቁረይሽ እየቀራ “ከፍራቻ ሰላም ሰጣቸው ይላል ከእኛ ፍራቻ ግን ሰላም አልሰጣቸውም” እያለ ሲያላግጥ፣  ሀጀረል አስወድን ቀምተው ወደ ሀገራቸው ወስደው ሲጫወቱበት አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።

              لا إله إلا الله

በዚች ምድር ላይ ምን ግፍ አልተፈፀመም??

  ታድያ እነዝያ ሁሉ በዳዮች አሁን የት ነው ያሉት⁉️

   ወዴት ነው የሄዱት⁉️

ወላሂ ሁላቸውም ወደ ሰሩት ነገር ሄደዋል!!

ምክንያቱም፦

   ከጌታህ ሊያመልጥ የሚችል የለም!!

እናም ወዳጄ……

   የቁድስን ክብር አዋርደው፣ የሙስሊሞች ሀገር ቀምተው፣ ሴቶችና ህፃናት ጨፍጭፈው; እንዲሁ የሚተዉ ይመስልሀል!?

  ወላሂ አይተዋቸውም‼️

=> ቅጣታቸው የበለጠ አሳማሚ እንዲሆን አመፃቸው እንዲበዛ፣

=> አላህ የያዘላቸው ቀጠሮ እስከ ሚደርስ

     እና

=> አላህ የፈለገው ጥበብ እስኪሟላ ያቆያቸዋል እንጂ

   ሁሉም የጀሀነም ሙኩቶች ናቸው ወደዝያው በቅርብ ይነዳሉ።

  ቅርብ ነው ሩቅ እንዳይመስልህ!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
meksud jemal shared a
ترجمہ ممکن نہیں

#ጋዛ_እንዴት_አደረች?

አልጀዚራ የቀጥታ ስርጭት ከማታ ጀምሮ አዳሩን በሰበር ዜና ያሰራጫቸውን ዋናዋና ዜናዎች መራርጬ ወደ አማርኛ መልሼላችዃለሁ…መልካም ንባብ!

▶️የአልቀሳም ብርጌድ ቃል አቀባይ #አቡ_ዑበይዳህ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል።

“ሰላም ለነዚያ ለጌታቸው ካልሆነ በቀር ጀርባቸውን በማያጎንብሱት ላይ ይሁን!” በማለት የጀመረው ሙጃሂድ አቡ ዑበይዳህ፣“ጥቅምት 7 ቀን የጠላት ምሽጎች እንደ ሸረሪት ድር ሲፈርሱ እና አንድ ተዋጊያችን ሶስት የጠላት ታንኮችን ሲያወድም የአሏህ እርዳታ በአይናችን አይተናል!”በማለት አክሏል።

▶️“ጠላት በመኖሪያ ሕንፃዎችና በሆስፒታሎች ላይ ማነጣጠሩ ውርደትንና ሽንፈትን እንጂ ሌላን አያመላክትም” ያለው የሙጃሂዶቹ ቃል አቀባይ ሙጃሂድ አቡዑበይዳህ አያይዞም

▶️“የጠላት ወታደራዊ እና የስለላ የበላይነት አለ የሚባልበት ዘመን አብቅቷል!እናም የጽዮናዊት የሽንፈት ዘመን ጀምሯል!”በማለት በኦክቶበር 7 ላይ ያስመዘገቡት ድል ትልቅ ሞራል እንደፈጠረላቸውና እስከመጨረሻው ለመዋጋት መወሰናቸውን እወቁልን ብሏል!ጠላት ከጠበቀው በላይ ሽንፈትን እንዲቀምስ እናደርጋለን በማለትም ዝቷል የጀግኖቹ የሚድያ ሀላፊ ጀግናው ሙጃሂድ #አቡ_ዑበይዳህ!

▶️የሐማስ ምክትል ሊቀመንበር ሳሌህ አል አሮሪ የፍልስጤም ተቃውሞ አሁንም የውጊያውን ሂደት እየተቆጣጠረ ነው እናም በዚህ ጦርነት ግቦቹን ከማሳካት ወደኋላ አይልም ብለዋል።

یَـٰلَیۡتَنِی كُنتُ مَعَهُمۡ فَأَفُوزَ فَوۡزًا عَظِیمࣰا

▶️ለአረብ መሪዎች ጠንከር ያለ መልእክት ያስተላለፈው አቡ ዑበይዳህ“እኛ የእናንተን ታንክ፣አውሮፕላንና ወታደር አንፈልግም…ቀቅላችሁ ብሉት አይነት…ነገር ግን ቢያንስ ቢያንስ ትንሽዬ ሀሞት ካላችሁ የእርዳታ ተሽከርካሪዎችን እንዲታንቀሳቅሱ እንጠይቃለን!”በማለት በአረቦች ደዩስነትና ተወዳዳሪ የሌለው ፍርሐት በጣም እንደተበሳጩባቸውና እንዳፈሩባቸው በሚያመላክት ንግግር ክፉኛ ተችቷቸዋል!

“እየሩሳሌምን ነፃ ለማውጣት እና የሀገሪቱን ክብር ለማደስ በታሪካችን ወሳኝ ጦርነት ገጥሞናል!”ያለው የጀግኖቹ ቃል አቀባይ ጀግናው ሙጃሂድ አቡዑበይዳህ

▶️“የፍልስጤም እስረኞች ከየእስር ቤቱ ካልተፈቱ በስተቀር የጠላት እስረኞችን መፍታት አይታሰብም!ጠላት የፍልስጢን እስረኞችን በአንድ ጊዜ ለመፍታት ከፈለገ እኛም ተዘጋጅተናል”በማለት ሰብኣዊ እርዳታ እንድገባ በሚል የፅዮናዊት እስረኞችን መልቀቅ ትክክልና ተገቢ እንዳልሆነ በገደምዳሜው ጠቁሟል!

▶️በጋዛ የሚገኘው የሃማስ እንቅስቃሴ ሃላፊ ያህያ ሲንዋር ለአል-አቅሳ ቲቪ እንደተናገሩት በተቃውሞው የተያዙ እስረኞችን በሙሉ ለመልቀቅ በወረራ የተያዙ እስረኞችን መፍታትን የሚያካትት የልውውጥ ስምምነት ለመደምደም ተዘጋጅተናል በማለት የአቡዑበይዳህን ንግግር ደግመዋል።

▶️የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ እስረኞቹን አስመልክቶ ለሐማስ መግለጫ በሰጠው መልስ“ሃማስ በእስራኤላውያን ላይ ጫና ለመፍጠር የስነ ልቦና ጦርነት እያካሄደ ነው!”ብሏል።

▶️በእየሩሳሌም የሚገኘው የእስረኞች ክለብ ሃላፊ ለአልጀዚራ ቀጥታ እንደተናገሩት ከጥቅምት 7 በፊት በእስራኤል እስር ቤቶች ውስጥ የነበሩት እስረኞች ቁጥር 5,200 ሲሆኑ ከእነዚህ መካከል 400 ህጻናት እና 32 ሴት እስረኞች ይገኙበታል።

▶️ትላንት ቅዳሜ በብዙ መቶሺህዎች በተገኙበት የኢስታንቡል ሰልፍ ላይ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ጠንከር ያሉ ንግግሮችን በመናገራቸውና ሀማስ የነፃነት ታጋይ እንጅ ፈፅሞ አሸባሪ አይደለም…በዚህ አቋማችን እስራኤል ብትቀየምም የራሷ ጉዳይ…እንዳውም አሸባሪዋ ራሷ ፅዮናዊቷ መሆኗን ለዓለም ህዝብ እናሳውቃለን…በማለት በተናገሩት ንግግር ምክናየት የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከቱርክ ጋር ያለንን ዲፕሎማሲያዊ ተልዕኮ እና ግንኙነት እንደገና እንገመግማለን!”በማለት ቲውተር(X)ላይ ፅፏል።ማን ሊጎዳ?

▶️በጋዛ ውስጥ የመንግስት ሚዲያ ኃላፊ“ፍልስጤማውያን ለወረራ ማስፈራሪያዎች አይንበረከኩም፣እስከ መጨረሻው እስትንፋስ ድረስ እንታገላለን!”ብሏል።

▶️የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ ከግብፁ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ጋር በመካከለኛው ምስራቅ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በስልክ ተወያይተዋል።

▶️ሃማስ በጋዛ ውስጥ 8 ሩሲያውያን-እስራኤላውያን እስረኞችን ለማግኘት እየሞከረ ሲሆን ላቭሮቭ “ለአስር አመታት የሚቀጥል አደጋ” እንዳለ አስጠንቅቋል።

▶️የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ ከሳዑዲ አቻቸው ጋር በጋዛ ወታደራዊ ዘመቻዎችን ማስፋፋት ያለውን አደጋ እና አፋጣኝ የእርቅ ስምምነት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ተወያይተዋል።

▶️የኩዌት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የእስራኤል ወረራ በጋዛ ላይ እያደረሰ ያለው ጥቃት እና የአለም አቀፍ ህጎችን መጣስ ጥልቅ ስጋት እንዳለን እንገልፃለን ብሏል።

▶️የኳታር ኤሚር እና የኢራን ፕሬዝዳንት በፍልስጤም ስላሉ ለውጦች ተወያይተዋል!

የኦማን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ወራሪው ሀይል በጋዛ ሊፈጽመው ያሰበውን የመሬት ወታደራዊ ዘመቻ ውጤቱ የከፋ እንደሚሆንና ከአካባቢው አልፎ በአለም ላይ ከባድ አደጋዎችን እንደሚያስከትል በድጋሜ አስጠንቅቋል።

▶️የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አፋጣኝ የተኩስ አቁም እንድደረግና አስቸኳይ የሰብአዊ እርዳታ ለማምጣት ኮሪደሮች እንዲከፈቱ እንጠይቃለን ያለ ሲሆን አያይዞም እስራኤል በጋዛ ያደረገችውን ​​የመሬት ኦፕሬሽን እናወግዛለን በማለት አክሏል።

▶️የኳታር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የእስራኤል ጦር ወደ ጋዛ ወረራ ለማድረግ በያዘው አቋም ላይ ያለንን ጥልቅ ስጋት እና አስከፊ ሰብአዊ መዘዝ የሚያስከትል አደገኛ ሙከራ መሆኑን እንገልፃለን ብሏል።

▶️የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ሆስፒታል፣እንዴ UNRWAአይነት የእርዳታ ማእከል ወይንም ትምህርት ቤት ለሽብር ተግባር የሚያገለግል ማንኛውንም ኢላማ አንተወውም በማለት ከዚህ በፊት በአንድ ግዜ ከ500 በላይ ሰዎች የተገደሉበትን የሆስፒታል ጥቃት በግዜው ያስተባበለች ቢሆንም ዛሬ ግን እርሱን በማመን ለወደፊቱም በእብሪቷ እንደምትቀጥል ይፋ አድርጋለች!

▶️በዋሽንግተን እና በኒውዮርክ የተካሄዱ ሰልፎች እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ላይ ያደረሰችውን ጥቃት በማውገዝ ጦርነቱ እንዲያበቃ ጠይቀዋል።

◀︎የቀድሞ የቱርክ የፍትህ እና ልማት ፓርቲ ዋና አማካሪ የጋዛ ጦርነት የእስራኤል እና የምዕራባውያን አጋሮቿን ጭካኔ የተሞላበት ገጽታ ይፋ አድርጓል በማለት አውግዟል።

◀︎ በለንደን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ፍልስጤምን በመደገፍ እና በጋዛ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት እንዲያቆም ጠይቀዋል።

▶️“እናስታውሳለን” በሚል መሪ ቃል “የአይሁድ ድምፅ ለሰላም” ድርጅት ባለፈው ሐሙስ ጥቅምት 26 ቀን 2023 በእስራኤል የቦምብ ጥቃት የተገደሉ 2,913 የፍልስጤም ልጆችን ስም አውጥቷል።ድርጅቱ በጋዛ ላይ ለደረሰው አስደንጋጭ ነገር ተጠያቂ ናት ሲልም ዩናይትድ ስቴትስን ከሷል።ምክንያቱም በእስራኤል ጦር እጅ ህጻናትን ከሚገድሉት ቦምቦች 80% የሚሆኑት አሜሪካ ሰራሽ ናቸው።እያንዳንዱ ህይወት ውድ እንደሆነ እና ይህን የዘር ማጥፋት ወንጀል ለማስቆም ሁሉም ሰው የተቻለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለበትም አሳስበዋል።

▶️የእስራኤል ሚንስትር #ኤሎንመስክ በጋዛ ለሚገኙ የእርዳታ ድርጅቶች የኢንተርኔት አገልግሎት ለመስጠት መወሰኑን አስመልክቶ ምላሽ ሰጥቷል።

▶️የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የእስራኤል ባለስልጣናት የጋዛን ህዝብ ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ያሰበውን አረመኔያዊ ድርጊት ለማስቆም ለተኩስ አቁም ምላሽ እንዲሰጡ እንጠይቃለን ብሏል።

▶️ሮይተርስ ከዲፕሎማቶች አገኘሁት ባለው መረጃ የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ነገ ሰኞ ይሰበሰባል።

▶️በጋዛ ሰርጥ የኢንዶኔዥያ ሆስፒታል ውስጥ ያሉ ምስሎች የእስራኤል ወረራ በሆስፒታሉ አከባቢ ላይ ባደረሰው የቦምብ ጥቃት የደረሰውን ውድመት አሳይተዋል።

▶️የስፔን ሚንስትር ለአውሮፓውያን #ናታንያሁ የጦር ወንጀለኛ ነው.. በ #ጋዛ የዘር ማጥፋት ወንጀል ስፔንን ተባባሪ እንዳታደርጉን ብሏል።

▶️የእስራኤል እስረኞች ቤተሰቦች ከ # ናታንያሁ ጋር ከተገናኙ በኋላ ዘመዶቻችን እንዲመለሱ የፍልስጤም እስረኞችን ከእስር ቤት እንዲወጡ እንደግፋለን በማለት የሀማስን አቋም ተጋርተዋል።

▶️ግብፅ የእስራኤል መሰናክሎች እርዳታ ወደ #ጋዛ ሰርጥ እንዳይገባ እንቅፋት ሆነዋል በማለት እንደለመደችው ከሳለች።ክስ ብቻ!

▶️የፍልስጤም የዜና አገልግሎት ከራማላ በስተሰሜን በምትገኘው በቢት ሪማ ከተማ ከወራሪው ሃይሎች ጋር በተፈጠረ ግጭት 6 ወጣቶች በቀጥታ በተተኮሰ ጥይት ቆስለዋል(ተገድለዋል?)

▶️የቤልጂየም ፓርላማ አባል የሆኑት ሲሞን ሞትኪን የ#አልጀዚራ ፎቶዎች ባይኖሩ ኖሮ በጋዛ የእስራኤል ዕለታዊ ወንጀሎች ወደ ምዕራቡ ዓለም አይደርሱም ነበር በማለት ለአልጀዚራ ያላቸውን አድናቆት የገለፁ ሲሆን እግረመንገዳቸውንም የምዕራቡ አለም ሚድያዎችን ተችተዋል።

▶️የፍልስጤም ቲቪ እንዳስታወቀው ኮሙኒኬሽን እና ኢንተርኔት ቀስ በቀስ ወደ ጋዛ ሰርጥ እየተመለሱ ነው ብሏል።

▶️አንድ ፈረንሳዊ #ጋዛን በሚደግፉ ተቃዋሚዎች ላይ ጥቃት ከሰነዘረ በኋላ ከፈረንሳይ ፖሊስ ጋር ተጋጭቷል¡

▶️የፍልስጤም ቴሌኮሙኒኬሽን ኩባንያዎች “ፓልቴል”እና “ጃዋል” የጥሪ እና የኢንተርኔት አገልግሎት ቀስ በቀስ በጋዛ ሰርጥ ወደ ሥራ እየተመለሱ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

▶️በጋዛ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ከጋዛ በስተደቡብ በሚገኘው በካን ዩኒስ በሚገኘው የ"ታሞስ" ቤተሰብ መኖሪያ ቤት ላይ የወረራ አውሮፕላኖች ባደረሱት የቦምብ ጥቃት 10 ሰማዕታት እና ከ25 በላይ መቁሰላቸውን አስታውቋል።

https://ummalife.com/AbdelazizBinMuhammed

https://t.me/Seyfel_Islam

Telegram: Contact @Seyfel_Islam
t.me

Telegram: Contact @Seyfel_Islam

????? ?? ????????? ??????? ህዝበ ሙስሊሙን የሚመለከቱ በታማኝ ምንጮች የተዘገቡ ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት Join ያድርጉን! https://heylink.me/AzizoSocialLinks.com
Send as a message
Share on my page
Share in the group
meksud jemal shared a
ترجمہ ممکن نہیں

ምዕራባውያን

በቀጣይ ጊዜያት አይናቸውን በጨው አጥበው

ስለ ሰብአዊ መብት ፣ ህፃናት እና ሴቶች መብት ያስተምሩናል

ይንቀላቸው! አስመሳዮች

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group