UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ያልተወሱ ታሪኮች

=======

የአላህ መልእክተኛ(ﷺ) ከሞቱ በኋላ እስልምና ከአረብ ደሴት አልፎ በምእራብ እስከ አውሮፓ በምስራቅ እስከ ቻይና ድንበር ደርሷል።ከረሱል (ﷺ) ሞት በኋላ ሙስሊሞች አውሮፓ ለመግባትና ስፔንን ለ700 አመት ማስተዳደር ለመቻል 80 አመት ብቻ ነው የወሰደባቸው።

ታድያ ግን ሙስሊሞች በተቆጣጠሩዋቸው ቦታውች ላይ የሀገሬውን ሰዎች ቅርስና ስራዎቻቸውን ጠብቀው አቆይተዋል።ነገር ግን የሙስሊም ስርወ-መንግስት በተዳከመ ጊዜ መስሊሞች ያበረከቱትን ስራ እና በጣም ብዙ የተራቀቁ የሳይንስ ግኝቶችን እነዚህ ካሃድያን አውድመዋቸዋል። ሞንጎሎች የኢስላም የሳይንስ ማዕከል የነበረችውን ባግዳድን በጣም አፀያፊ በሆነ መልክ ድምጥማጡን አጥፋተዋል። ስፔኖችም የሙስሊሞችን ቅርስ አውድመዋል።

የኢስላም ስርወ-መንግስት ለአንድ ሺ አመት ያህል በአለም ሀያልና የሰለጠነ መንግስት ሆኖ ቆይቶዋል።አረብኛ አለምአቀፋ የትምህርትና የዲፕሎማሲ ቋንቋ ሆኖዋል። ሳይንስም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አዘንብሎ ባግዳድ የሳይንስ መቀመጫ ለመሆን በቅታለች።

ሙስሊሞች በጣም ተክነውበት ከነበረና ስለ ስልጣኔያቸው ከሚጠቀሱት ዋነኛ የሆነው በህክምና የደረሱበት ምጥቀት ነበር።የኋላ ኋላ የኢስላም ስርወ-መንግስት ሲዳከም ምእራባውያን አብዛኛውን አጥፍተው ቀሪውን ወደ ቋንቋቸው ቀይረው የራሳቸው አስመስለዋል።

እኛ ሙስሊሞች አብዛኛው ታሪካችን ተቀምቶ እና ተሸፋኖ ይገኛል። ታሪካችንን አናውቅም የቀደምቶቻችን ጀብድ ዛሬ ለኛ ስንቅ ይሆነን ዘንድ አናወሳም። አላህ ፋቃዱ ከሆነ ሙስሊሞች የሰሩትን ዘመን ተሻጋሪ ስራዎች በሳይንስና በህክምና የደረሱበትን ምጥቀት በክፋል ከፋፍዬ አቀርባለሁ። የትላንቶቹ መልካም ታሪክን ሰርተው አልፈዋል። ዛሬ ምድር ላይ የተተካን እኛ አላህ ጥሩ አሻራን አኑረው ከሚያልፋት ያድርገን።

ኡማ ላይፋ

======

ummalife.com/marufabadir

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሀድያ ኢስላማዊ ተቋም

ሆሳዕና:ሀድያ

አላህ እውን ያድርግልን።ሀድያም ወደ ቀድሞ ታላቅነቱዋ አላህ ይመልሳት።

image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የአላህ ቀደር እንዲህ ነው

የሕክምና ተማሪ ነው። ከሚማርበት ኮሌጅ ፊት ለፊት ከጓደኞቹ ጋር ቆሞ በመልካም ነገር ይተዋወሱ ይዘዋል። አላህን የሚፈሩ ሷሊህ ጓደኛሞች ናቸው። በድንገት ሲበር ከፊትለፊቱ በመጣ መኪና ተገጭቶ መሬት ተዘረረ። ደሙ ያለማቋረጥ እየፈሰሰ ከመሬት ተዘረረ። እሱን ብቻ ነጥሎ አጋደመው። አፋፍሰው ወደ ሆስፒታል ይዘውት ሄዱ። የቀኝ ኩላሊቱ እየደማ ነበር። ዶክተሮቹ ከኩላሊቱ አሊያም ከነፍሱ አንዱን መምረጥ ግዴታቸው ስለነበር በአላህ ፈቃድ ህይወቱን ታደጉለት።

ከሀያ ሁለት ቀናት በኋላ በክፍሉ አልጋ ላይ እንደተጋደመ ቀዶ ጥገና ያደረገለት ዶክተር ወደተኛበት አልጋ ፈገግ ብሎ ተጠጋ፡-

"ስለቀደር ምን ያህል ሰምተሀል?" ሲል ጠየቀው።

"ብዙ ጊዜ ሲወራ ሰምቻለሁ ከመጽሐፍቶችም ላይ አንብቤያለሁ" ሲል መለሰ።

ዶክተሩ ፀጉሮቹን እያሻሸ "ባንተ ላይ እስካየው ድረስ እኔም ስሰማው ኖሬያለሁ። የሆነውን ልንገርህማ ቀዶ ጥገናውን እያደረኩ ሳለ ኩላሊትህ ላይ እንግዳ የሆነ ነገርን አስተዋልኩ። ናሙናው ለምርመራ ወደ ላብራቶሪ ተላከ። ውጤቱ ሲመጣ በአላህ ስራ በእጅጉ ተገረምኩ። በጣም ዘግይቶ ሊታወቅ የሚችልና በፍጥነት ገዳይ የሆነ የካንሰር ምልክት በኩላሊትህ ላይ ተገኘ። በእርግጥም የመጀመርያ ደረጃ ላይ ያለና በቀላሉ የሚድን ቢሆንም አደጋው የህይወትህ ዋጋ ነበር የካንሰር በሽታው ኩላሊትህ ላይ ነበር" አለና ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ።

ተማሪው ዶክተሩን እየተመለከተ

"መኪናው እኔን ብቻ መርጦ የገጨኝ የካንሰር በሽታው ሰውነቴ ውስጥ ሳይዛመት በፊት አንዱን ኩላሊቴን አጥቼ በቀላሉ ከካንሰር ድኜ በህይወት እንድኖር ሁለተኛ ዕድል አላህ ሊሰጠኝ ፈልጎ ነው ማለት ነው?!" አለ።

ዶክተሩ ከዓይኑ ላይ ዕንባውን እየጠራረገ "ታዲያ የጌታህ መድኃኒት በድንገትና በአጋጣሚ የተከሰተ ይመስልሀልን?!" ሲል ጠየቀ።  ተማሪው በፈገግታ "በእርግጥም ይህ ነው ቀዳእና ቀደር" እያለ አላህን ደጋግሞ አመሰገነ።

Copy

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

🔶ከኢብኑል ቀይም ድንቅ ምክሮች🔶

"ንግግር ለአንተ እንደ ባሪያ ሆኖ ይኖራል፣ ነገር ግን ከአፍህ በወጣ ጊዜ አንተ የእሱ ባሪያ ትሆናለህ!"

📖 (አል-ጀዋብ አል-ካፊ)

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የቁርአን ተዓምር ሚዘለቅ አይደለም

የቀጠለ......

🔶የፕሮፌሰሩ ምላሽ🔶

ፕሮፌሰሩ(Dr. Moore) ስለ ክሊኒካል ፅንስ ጥናት(clinical embryology ) መጽሃፍም ጽፈዋል እና ይህንን መረጃ በቶሮንቶ ሲያቀርቡ በመላው ካናዳ ብዙ ግርምትን ፈጥሮ ነበር።  በካናዳ ውስጥ ባሉ አንዳንድ ጋዜጦች የፊት ገጽ ላይ በሰፊው ወጥቶ ነበር እና አንዳንድ አርዕስተ ዜናዎች በጣም አስቂኝ ነበሩ።  ለምሳሌ አንድ ርዕስ እንዲህ ይላል፡- “በጥንታዊ የጸሎት መጽሐፍ ውስጥ የተገኘው አስገራሚ ነገር!” ከዚህ ምሳሌ እንደምንረዳው ሰዎች ነገሩ አልገባቸውም።አንድ የጋዜጣ ዘጋቢ ፕሮፌሰሩን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፣ “ምናልባት አረቦች ስለእነዚህ ነገሮች - ስለ ፅንሱ ገለፃ፣ መልክ እና እንዴት እንደሚለወጥ እና እንደሚያድግ ያውቁ ይሆናል ብለው አያስቡም? ምናልባት ሳይንቲስቶች ከነበሩና  በዚህ ጉዳይ በሰዎች ላይ ጥናት አድርገው ከነበረ። ፕሮፌሰሩ  ዘጋቢው አንድ በጣም አስፈላጊ ነጥብ እንዳመለጡ ወዲያውኑ ጠቆሙ።ሁሉም የፅንሱ ስላይዶች የታዩት እና በፊልሙ ውስጥ የተነደፉት በአጉሊ መነጽር(microscope)ከተነሱ ምስሎች የተገኙ ናቸው። ስለዚህ አንድ ሰው ከአስራ አራት መቶ አመታት በፊት ፅንሱን ለማወቅ ቢሞክር ሊያየው አይችልም"

በቁርአን ውስጥ ያሉት ሁሉም መግለጫዎች የፅንሱ ገጽታ በአይን ለማየት የማያስችሉ ናቸው። ስለዚህ አንድ ሰው ለማየት ማይክሮስኮፕ ያስፈልገዋል።ምክንያቱም እንዲህ ዓይነቱ መሣሪያ ከሁለት መቶ ለማይበልጡ ዓመታት ብቻ ስለነበረ ፕሮፌሰሩም እንዲህ ሲሉ ተሳለቁ፦

"ምናልባት ከአስራ አራት ክፍለ ዘመን በፊት አንድ ሰው በድብቅ ማይክሮስኮፕ ነበረው እና ይህን ምርምር አድርጓል የትም ቦታ ላይ ምንም ስህተት አልሰራም። ከዛ እንደምንም ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) አስተምሮ ይህንን መረጃ በመጽሃፉ ውስጥ እንዲያስቀምጠው አሳምኖታል። ከዚያም መሳሪያውን አጥፍቶ ለዘላለሙ ሚስጥር አድርጎታል።  ይህን ታምናለህ? ማስረጃ እስካላመጣህ ድረስ ማመን የለብህም ምክንያቱም ይህ የማይመስል ነገር ነው"

እንዲያውም፣ “ይህን በቁርኣን ውስጥ ያለውን መረጃ እንዴት ያብራራሉ?” ተብሎ ሲጠየቁ።  "በመለኮት ብቻ ነው የሚገለጥ!" ነበር ምላሻቸው።

የመጀመርያ ክፍል ለማንበብ

https://ummalife.com/post/199362

follow our page inshallah you will benefit.

https://ummalife.com/Marufabadir

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group