UMMA TOKEN INVESTOR

Abu Ehsan shared a
Translation is not possible.

13 views
1 view
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Ehsan shared a
Translation is not possible.

ጠራራ ፀሀይ ላይ ከመቃብሮች መሀል ባህሉል የተባለ የከተማው

ዕውቅ እብድ ቁጭ ብሏል። (160 አመተ ሂጅራ)

በግዜው የሙስሊሙን አለም ሲያስተዳድር የነበረው ሀሩነ-ረሺድ

ድንገት ከመቃብር መሀል የተቀመጠውን እብድ ይመለከተዋል።

ንጉስ ሀሩን የማፌዝ ገፅታ እየተነበበበት፦ «አንተ ባህሉል! እንተ

ቆይ መች ነው ሰው ምትሆነው?» ብሎ ጠራው።

ከመቃብሮች መሀል ብድግ አለ። ዙርያውን በአይኑ ቃኘ'ና

ከአጠገቡ ከምትገኝ ዛፍ ላይ በርጋታ ወጥቶ፦ «አንተ ሀሩን! አንተ

ቀውስ! ቆይ ግን መች ይሁን ሰው ምትሆነው?» ብሎ ጮኸበት።

ንጉስ ሀሩን የተቀመጠባትን ፈረስ በዝግታ እየጋለበ መጥቶ ከዛፏ

ስር ቆመ።

እዝያው ፈረሱ ጀርባ ላይ ተንደላቅቆ፦ «እንዴ! እኔ ነኝ እብድ ወይስ

በዚ ጠራራ ፀሀይ መቃብሮች ላይ ምትቀመጠው አንተ ነህ

እብድ?»

«እኔማ ጤነኛ ነኝ» አለ ባህሉል፤ ሙሉ መተማመን ፊቱ ላይ

እየተስተዋለበት።

«እንዴት ሆኖ...?» ሀሩን የማሾፍ ስሜት የተቀላቀለበት ጥያቄ

ጠየቀ።

ባህሉልም ወደ ንጉሱ ቤተ-መንግስት እያመላከተ፦ «ያኛው ጠፊ

እንደሆነ አውቃለሁ። ይኸኛው ደግሞ (መቃብር) ዘውታሪ

እንደሆነም አውቃለሁ።

ስለዚህ እኔ ይኸኛውን ከዝያኛው አስበልጬ ገንብቸዋለሁ። አንተ

ደግሞ እንደሚታወቀው ያኛውን ብቻ ገንብተህ ይኸኛውን

አፍርሰኸዋል።

ምንም እንኳን ከገነባኸው ህንፃ ተነቅለህ ወዳፈረስከው መቃብርህ

ወራጅ እንደሆንክ ብታምንም ግን መሄድን አትሻም» ብሎ በአውላላ

የትካዜ ሜዳ ላይ ንጉሱን አደናገረው።

ባህሉል ንግግሩን ቀጥሏል፦ «ታድያ ከኔ እና ከንተ ማናችን ነን

እብድ መባል ያለብን...»

ካማረው ፈረስ ላይ በክብር ቁጭ ያለው ንጉስ ከጉንጮቹ እንደ

ጅረት የሚፈሰው እንባው ፂሙን አረጠበ።

ንጉስ የሀፍረት ስሜት ውስጥ ሆኖ፦ «ባህሉል ሆይ! ወላሂ አንተ

ትክክል ነህ። እባክህ ትንሽ ምክር ጨምርልኝ» አለው።

«ቁርአን ይበቃኻል፤ ምክሮቹን ጠበቅ አድርገህ ያዝ» አለው

ባህሉል።

«እሺ ምትፈልገውን ንገረኝ'ና ልፈፅምልህ» አለው ንጉስ ከግዛቱ

ሊያስጠቅመው።

«አዎን! 3 ምፈልገው ነገር አለ። ከፈፀምክልኝ አመሰግንሃለሁ»

አለው ባህሉል ከዛፉ ላይ ቁጭ ብሎ።

ንጉስም፦«ጠይቀኝ» አለ፤ ሙሉ መተማመን ፊቱ ላይ እየተነበበ።

ባህሉል፦«እድሜዬን ጨምርልኝ»

ንጉስ፦ «ይኸንን እንኳን አልችልም»

ባህሉል፦ «ከመለከል መውት ጠብቀኝ»

ንጉስ፦ «ኧረ አልችልም»

ባህሉል፦ «እሺ ከእሳት ታድገኸኝ ጀነት አስገባኝ»

ንጉስ፦ «በምን አቅሜ...!»

ባህሉል፦ «አየህ አንተ ባርያ እንጂ ገዢ አይደለህም፤ እኔም ባንተ

የሚፈፀምልኝ ምንም ጉዳይ የለኝም»

-------------------------------------------------------------

ምንጭ፦

ﻛﺘﺎﺏ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Ehsan Сhanged his profile picture
6 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Ehsan shared a
Translation is not possible.

ምዕራቡ አለም በብሪቴይን እርግዝና በፈረንሳይ አዋላጅነት በጥቅመኛ አረቦች አጨብጫቢነት የወለዷትን የግፍና የበደል ልጅ መጠበቅ ላይ መተባበር መያዛቸው ብዙ አያስገርምም። ታማኝነት አልባ፣ የሁለት ሚዛን ባለቤት ከሆኑት የግፍ መሪዎችና ልሂቃን ስብስብ ከዚህ የተለየ መጠበቅም የዋህነት ነው። ቅሉ ሁሉም ነገር ማብቂያ አለው፤ ሁሉም ነገር መጠናቀቂያ አለው።

★ ማብቂያውም ፍትህን ለተነፈጉት ሁሉ ብርሃን መሆኑ ነው። ወላዱም፣ ያዋለደውም፣ ያጨበጨበውም፣ የተወለደውም የበደልና የግፍ ልጅም መዋረዳቸው አይቀርም። በነፍሶቻቸው ውስጥ የነገቡት የበላይነትና ሁሉን አድራጊነት መንፈስ ቅዠት መሆኑ አይቀርም። የአላህ ቃል እንዲህ ይላል።

« إن الذين كفروا ينفقون أموالهم ليصدوا عن سبيل الله فسينفقونها ثم تكون عليهم حسرة ثم يغلبون… »

« እነዚያ የካዱት ሰዎች ከአላህ መንገድ ሊከለክሉ ገንዘባቸውን ያወጣሉ። በእርግጥም ያወጣሉ። (ካወጡም በኃላ) ፀፀት ትሆንባቸዋለች። ከዚያም ይሸነፋሉ። የካዱት ሰዎች ወደ ገሀነምም ይሰበሰባሉ።»

እንዲህም ይላል።

« …عسى الله أن يكف بأس الذين كفروا والله أشد بأسا وأشد تنكيلا »

« … አላህ የካዱትን ሰዎች ኃይል ሊከለክልልህ ይከጀላል (ይከለክልልሃል)። አላህም በኃይል ሲይዝ የበረታ፤ ቅጣቱም እጅግ ጠንካራ ነው። »

★ በተቃራኒው በበደል ውስጥ በትግልና በትእግስት፣ በትእግስትና በትግል ያለፉት ሁሉ የአላህ እርዳታ እየጨመረላቸው፤ እዝነቱንና እገዛውን እያሰፋላቸው፤ የድልን ካባ እንደሚያጎናፅፋቸው እርግጥ ነው።

ለተወዳጁ መልእክተኛው (ሰዐወ) አላህ እንዲህ ይላቸዋል።

« …فسيكفيكهم الله وهو السميع العليم »

« … ከእነርሱም (ከከሃዲያኑ) አላህ ይበቃሃል። እርሱ ሰሚና ዐዋቂው ነው። »

እንዲህም ይላል።

« أليس الله بكاف عبده ويخوفونك بالذين من دونه… »

« አላህ ለባሪያው በቂ አይደለምን? ከእርሱ ውጪ (በታች በሆኑት ጣኦቶቻቸው) በሆኑት ነገሮች ያስፈራሩሃል። … »

اللهم افرغ على المجاهدين الصابرين الصبر وانصرهم على الظالمين الغاصبين

#الأقصى حياتنا

والموت في سبيلها اسمى امانينا

Send as a message
Share on my page
Share in the group