abu hanifa Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

abu hanifa shared a
1 month Translate
Translation is not possible.

ኢራን “እስራኤልን መቅጣት” ያለችው ዘመቻ ማብቃቱን ገለጸች።

እስራኤል ከሁለት ሳምንት በፊት በሶሪያ መዲና ደማስቆ በሚገኝ የኢራን ኢምባሲ ላይ ባደረሰችው የአየር ላይ ጥቃት ሁለት ወታደራዊ አዛዦችን ጨምሮ ዘጠኝ ኢራናዊያን መገደላቸው ይታወሳል።

ይህንን ተከትሎ በኢምባሲዋ ላይ ለደረሰው ጥቃት እስራኤልን እንደምትበቀል ስትዝት የቆየችው ኢራን መጠነ ሰፊ የድሮን እና ሚሳዔል ጥቃት ወደ ቴልአቪቭ መተኮሷን አስታውቃለች።

የኢራን አብዮታዊ ዘብ ጥቃቱን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ወደ እስራኤል ድንበር በርካታ ሚሳዔሎችን እና ድሮኖችን መተኮሱን አስታውቋል።

የኢራን አብዮታዊ ዘብ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ሞሀመድ ባግሪ እንዳሉት መግለጫ እስራኤል ለመቅጣት በሚል የተካሄደው ዘመቻ ማብቃቱን አስታውቋል፡፡

ይሁንና እስራኤል የአጸፋ እርምጃ ለመውሰድ ከሞከረች ግን ከእስካሁኑ የከፋ እርምጃ እንደሚጠብቃትም አስታውቋል፡፡

አሜሪካ ከዚህ ጥቃት ራሷን እንድታርቅ ያስጠነቀቁት ዋና አዛዡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ በቀጣይ እርምጃዎች ላይ አሜሪካ ጣልቃ ከገባች ግን በመካከለኛው ምስራቅ ያሉ የአሜሪካ ወታደራዊ ማዘዣዎች ጥቃቱ ኢላማ ይሆናሉ ሲልም አስጠንቅቀዋል፡፡

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በበኩላቸው ከኢራን የተሰነዘረባትን ከ300 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትታ መጣሏን አስታውቃለች፡፡

ሰው አልባ አውሮፓላኖቹ ጥቂት ጉዳት ብቻ አድርሰዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሀገራቸውን አየር ሀይል እና አጋር ሀገራትን አድንቀዋል፡፡

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሀገራቸው ከእስራኤል ጎን መሆኗን ገልጸው የቡድን ሰባት ሀገራት እንዲመክሩበት እንደሚያደርጉም አስታውቀዋል፡፡

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu hanifa shared a
Translation is not possible.

🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸

አንዳንድ ሠው አለ‼️እንደ ሐምዛ ዓይነት‼️

ሐምዛ ባለፉት 40 ዓመታት በአሜሪካ

የሕግ ታራሚ ነው። የሶሻል አክቲቪስቱ

ማልኮም ኤክስ የሕይወት ታሪክ ካጠና

በኋላ የተፈጥሯዊው ኃይማኖት ዕስልምናን

እዚያው ዕስር ቤት ውስጥ እያለ ተቀላቅሏል።

ሐምዛ የጋዛውያን ሰቆቃ ከሰማ በኋላ በሰዓት

15 ሣንቲም ሒሳብ እየሰራ ያጠራቀመውን $17.74 ለጋዛውያን አበርክቷል።

🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸

#gazagenocide

#israelaterroriststate

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu hanifa shared a
Translation is not possible.

🇵🇸⚔️ ዘመቻ አል አቅሳ ማዕበል ለ 149ኛ ቀን ዛሬም ቀጥሏል!

⚪️ ሙጃሂዲን ብርጌድ ተዋጊዎቹ የጽዮናውያን ጠላት ሃይሎችን በጋዛ ከአል-ዘይቱን ሰፈር በስተደቡብ በሚገኝ ቦታ ላይ በከባድ የሞርታር መሳሪያ ኢላማ ማድረጋቸውን አስታውቋል።

🟡 የአል አቅሳ ሰማዕታት ብርጌድ ቱልከረም ጀግኖች ታጋዮቹ ዛሬ ረፋድ ላይ መትረየስና ፈንጂዎችን በመጠቀም በኑር ሸምስ ካምፕ ዙሪያ ከወራሪ ሃይሎች እና የጦር መኪኖቻቸው ጋር ከፍተኛ ውጊያ መግጠማቸውን ገልጿል።

በተጨማሪም የኛ ተዋጊዎቻች ከፍተኛ የሆነ ፈንጂ በጽዮናውያን እግረኛ ሃይል ላይ ማፈንዳት ችለዋል ይህም በጦር ኃይሉ መካከል ጉዳት ማድረሱን አረጋግጠናል ብሏል።

🔴 አቡ አሊ ሙስጠፋ ብርጌድ በብርጌዱ ውስጥ የሚገኙት የኛ ጦር ኃይሎች የጠላት ጦር ወረራን በሁሉም የውጊያ ግንባሮች በመጋፈጥ ከወታደሮቻቸው እና ከአዛዦቻቸው ጋር ውጊያ በማድረግ በየደረጃቸው በጠላት ላይ ኪሳራ በማድረስ አንዳንድ ትጥቆቻቸውን እየማረኩ ይገኛሉ ብሏል።

🔴 አቡ አሊ ሙስጠፋ ብርጌድ ጽዮናዊያኑ በህዝባችን ላይ ለፈጸሙት ወንጀል ምላሽ ከአል-ዘይቱን ሰፈር በስተደቡብ የጠላት ወታደራዊ ስብስቦችን በከባድ የሞርታር መሳሪያ ኢላማ ማድረጉን አስታውቋል።

🟡 የአል አቅሳ ሰማዕታት ብርጌድ ተዋጊዎቹ በካን ዮኒስ ከተማ የውጊያ ግንባር ላይ በተገቢው መሳሪያ ተጠቅመው ከጠላት ሃይሎች ጋር ከባድ ውጊያ እያደረጉ መሆኑን ገልጿል።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu hanifa shared a
Translation is not possible.

📈ተጨማሪ ሪፖርት!

ሙጃሂዲን ብርጌድ፡ ከጋዛ ከተማ በስተ ሰሜን ምዕራብ የሚገኙ የጽዮናውያን ጠላት ሃይሎችን በሮኬት ደብድበናል ብሏል፡፡

የሶሪያ መከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ላይ የጽዮናውያን ጠላት ከተቆጣጠረው የሶሪያ ጎላን ኮረብታ አቅጣጫ የአየር ጥቃት በደቡባዊ ደማስቆ በሚገኙ በርካታ ቦታዎች ላይ ያነጣጠረ ሲሆን ይህም የሰው ህይወት እንዲጠፋ የቁሳቁስ ኪሳራ እና የአካል ጉዳት አድርሷል።

ሒዝቦላህ፡ የኢስላማዊ ተቃውሞው ተዋጊዎች ከሰአት በኋላ 7፡30 ላይ የ"እስራኤል" የጠላት ወታደሮችን በ"Hunin Castle" በበርካታ ሚሳኤሎች ኢላማ በማድረግ ቀጥተኛ ጉዳት አድርሰዋል ብሏል፡፡

የሂዝቦላህን ጥቃት ተከትሎ የጽዮናውያን ሚዲያዎች እንደዘገቡት ከሂዝቦላህ የተተኮሱትሚሳኤሎች ያለቅድመ ማስጠንቀቂያ ሳይረን በሰሜን በተያዙት የፍልስጤም ምድር በሚገኘው “ሜሮን” የአየር ቁጥጥር ጣቢያ ላይ ጉዳ አድርሷል። ብለዋል፡፡

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
abu hanifa shared a
Translation is not possible.

📈እኩለ ሌሊት ላይ ኢራን ያካሄደችው ዘመቻ ዝርዝር መረጃ!

የኢራን ኢስላማዊ ሪፐብሊክ አብዮታዊ ዘብ ጦር አዳሩን 3 ዘመቻ በማካሄድ 3 የተለያዩ መግለጫዎችን አውጥቷል፡፡

👉1, በቅርቡ የእስላማዊቷ ኢራን ጠላቶች የፈጸሙትን የሽብር ወንጀሎች ምላሽ ለመስጠት በቀጠናው አንዳንድ አካባቢዎች የሚገኙ የጸረ-ኢራን አሸባሪ ቡድኖች የስለላ ዋና መሥሪያ ቤት እና ቡድኖችን እኩለ ሌሊት ላይ በኢስላማዊ ሪፐብሊክ አብዮት ዘብ ጠባቂዎች (IRGC) የባላስቲክ ሚሳኤሎች ኢላማ ተደርገዉ ወድመዋል።

👉2, በኢስላማዊ ሪፐብሊክ አብዮት ዘብ ጠባቂዎች (IRGC) በከርማን እና በራስክ በርካታ ውድ የሀገራችን ወገኖቻችንን በአሳዛኝ ሁኔታ ለሰማዕትነት ሞት ምክንያት የሆኑትን የአሸባሪ ቡድኖች ምላሽ ለመስጠት በድርጊቱ የተሳተፉ የአዛዦችን እና ዋና ዋና አካላትን የመሰብሰቢያ ቦታዎችን በመለየት በማውደም ምላሽ ሰጥቷል በዘመቻው በተለይም ISIS በሚገኝባቸው የሶሪያ ግዛቶች በርካታ የባለስቲክ ሚሳኤሎችን በማስወንጨፍ የተካሄደ ነው።

ማሳሰቢያ፡ ይህ ኦፕሬሽን በኢራቅ ውስጥ ዒላማ ካደረገው ጣቢያ ይለያል። በተመሳሳይ ከኢራን ወደ ኢራቅ እና ሶሪያ በርካታ ባለስቲክ ሚሳኤሎች ተወንጭፈዋል።

👉3, በኢስላማዊ ሪፐብሊክ አብዮት ዘብ ጠባቂዎች (IRGC) እና የመከላከያ ሰራዊት አዛዦችን በሰማዕትነት ለመግደል በቅርቡ የጽዮናውያን አገዛዝ የፈጸመውን ግፍ በመቃወም በቀጠናው በኢራቅ ኩርዲስታን ክልል የሚገኘው የጽዮናዊው አገዛዝ (ሞሳድ) ዋና የስለላ ዋና መሥሪያ ቤት እና የስለላ እና ቁጥጥር ቦታን ኢላማ በማድረግ በባላስቲክ ሚሳኤል አውድሟል።

ይህ ዋና መሥሪያ ቤት በክልሉ በተለይም በውድ ሀገራችን ውስጥ የስለላ ሥራዎችን ለማስፋፋትና የሽብር ተግባራትን የሚነድፍበት ማዕከል ነበር።

🚨ጥቃቱን ስንመለከተው የኢራን ጦር በሰሜናዊ ኢራቅ ውስጥ ቢያንስ ስምንት የአሜሪካ ጣቢያዎችን እና የሞሳድ ጣቢያን በባለስቲክ ሚሳኤሎች ኢላማ አድርጓል። የሞሳድ ሳይት በክልሉ ውስጥ የስለላ ስራዎችን ለመስራት እና የሽብር ጥቃቶችን ለማቀናጀት ይውል ነበር።

የኢራን ጦር በሰሜናዊ ሶሪያ የሥልጠና ካምፖችን እና በሃያት ታህሪር አል ሻም እና በቱርኪስታን እስላማዊ ፓርቲ ቁጥጥር ስር ያሉ የሎጂስቲክስ እና የድጋፍ ጣቢያዎችን ኢላማ በማድረግ ከፍተኛ የተሳኩ ባልስቲክ ሚሳኤሎችን ተጠቅሞ አውድሟል። ይህ ቦታ የአይ.ኢስ.አይ.ኤስ ኮራሳን ታጣቂዎች የሚሰለጥኑበት መሆኑን ምንጮች ለአል-ማያዲን ገልጸው ከስልጠና በመቀጠል አሜሪካውያ እገዛ ወደ አፍጋኒስታን በማጓጓዝ በኢራን ውስጥ ጥቃት ለመሰንዘር የሚጠቀሙበት ቦታ ነው።

በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group