kemal mohammed Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ሴት ልጅ በደደቦች ሸሪዓ እና

በነቢያቶች ሸሪዓ

⚡️በየ መድረኩ መዝፈንን ሀላል አደረጉላት፣

አላህ ግን አዛን፣ ኢቃማና አሚን በማለት ድምጿን ከፍ ከማድረግ ከልክሏታል።

⚡በሲኒማ ቤቶች እና በመድረክ ላይ እንድትሰራ ፈቀዱላት አላህም የጁምአ ሰላት እና የጀመዓ ሰላትን በሷ ላይ ግዴታ እንዳይሆን አድርጓል ።

🩸የኦሎምፒክ እና የማራቶን ሻምፒዮን አደረጓት አላህ ግን በሁለቱ ምልክቶች መካከል በሰፍዋና እና በመርዋ መካከል እንዳትሮጥ የከለከላት ጨዋነቷን እና ንፅህናዋን ለመጠበቅ ነው።

⚡በቴሌኮሙኒኬሽን ድርጅቶች እና ሌሎችም ደንበኞችን ለመሳብ በድምፅዋ ጥሪን በመመለስ ላይ በኤሌክትሮኒክስ ማስታወቂያ ተጠቅመውባታል።

አላህ ግን በሶላት ላይ ኢማሙ ቢሳሳት እንኳ ከማጨብጨብ ውጪ ድምፃን ከፍ አድርጋ" ሱብሃነላህ" በማለት ድምፃን ከማሰማት ከልክሏታል።

🩸በመዝናኛ ጉዞ ላይ ያለ መህራም( ያለ ወንድ ቤተሰብ) እንድትጓዝ አደረጓት።

አላህ ከእርሷ ላይ አንድ መህረም ካላገኘች ከእስልምና ማእዘን ውስጥ የሆነውን ሀጅን እንኳን አውርዶላታል።

⚡️የስፖርት ቡድኖችን ለማበረታታት እና ለመደገፍ ወሰዷት፤ አላህም ለጂሃድ ሃይማኖትን ለመደገፍ እንዳትወጣ ከልክሏታል።

🩸ከቤቷ ሽቶ የተቀባች፣ የተዋበች ውበቷን ለአደባባይ የገለፅች ሆና እንድትወጣ አደረጓት ።

አላህ ግን በእግሮቿ ላይ ያደረገችውን ጌጥ ለሰዎች ይሰማ ዘንድ መሬትን በእግሮቿ እየደበደበች እንዳትሄድ ከልክሏታል።

✍ ከሸይኽ አብድገንይ ገፅ ተወስዶ የተተረጎመ

👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://t.me/AbuEkrima

Telegram: Contact @AbuEkrima

Telegram: Contact @AbuEkrima

ይህ ቻናል የተለያዩ አስተማሪና አነቃቂ የሆኑ ትምህሮችን፣ ሙሃደራዎችን፣ የቀደምት አኢማዎችን ንግግሮች እንዲሁም የተለያዩ በጊዜያችን ያሉትን የሱና ዑለማዎች ፈትዋና ንግግር የምናቀርብበት ቻናል ነው።
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የምቀኝነት ጥግ

ሀቢል እና ቃቢል የተሰኙት የአድም ልጆች አስደማሚ ታሪክ

ጌታችን አላህ ጥራት ይገባውና አባታችን አደምን(ዐ.ሰ) ከጭቃ ፈጥሮ እናታችንን ሀዋን ከአደም(ዐ.ሰ) ከጎኑ ካስገኘ በኋላ በጀነት በተድላ እንዲኖሩ አደረጋቸው። አንዲትን ቅጠልም እንዳይቀርቡ በጥብቅ አዘዛቸው። የአላህ እርግማን በርሱ ላይ ይሁንና የምንግዜም የአደም(ዐ.ሰ) እና ልጆቹ ግልፅ ጠላት የሆነው ኢብሊስ አሳስቶ ይህን የተከለከሉትን ተግባር እንዲፈፅሙ በማድረግ ከጀነት ወደ ምድር እንዲወርዱ አስደረጋቸው።

አደም(ዐ.ሰ) እና ባለቤቱ ሃዋ ምድር ላይ መኖር ከጀመሩ ሰነባብተዋል። በጣም ብዙ ልጆችንም አፍርተዋል። ሃዋም በምትወልድ ጊዜ መንታ ነበር የምትወልደው አንድ ወንድ እና አንድ ሴት። ኋላ ላይም ለትዳር ሲደርሱ አንዱ ወንድ ልጅ ከሌላኛው ልጅ ጋር አብራ የተወለደችውን ነው የሚያገባው። ከሱ ጋር አብራ የተወለደችውን ደግሞ እርሱ ያገባት ልጅ ጋር አብሮ የተወለደው ልጅ ያገባታል። ከራሱ ጋር አብራ የተወለደችውን ልጅ ማግባት አይችልም።

ከአደም(ዐ.ሰ) ልጆች ውስጥ ቃቢል እና ሀቢል የተባሉ አሉ። ቃቢል በግብርና ስራ የሚተዳደር አርሶ አደር ሲሆን ሀቢል ደግሞ በእንስሳት እርባታ ሚተዳደር አርብቶ አደር ነው።

ከቃቢል ጋር አብራ የተወለደችው ልጅ በጣም ቆንጆ እና መልከ መልካም ናት። ከሀቢል ጋር የተወለደችው ግን መልኩዋ እንብዛም ነበር። ለትዳር በደረሱም ጊዜ አባታቸው አደም(ዐ.ሰ)  ሀቢል የቃቢልን ቃቢል ደግሞ የሀቢልን እህት(አብራ የተወለደች) እንዲያገቡ አዘዛቸው። ቃቢልም የራሱን እህት ማግባት ፈልጎ ነበር እና ይህን ሲሰማ በጭራሽ አይሆንም አለ። እህቴን(ከኔ የተወለደችውን) እኔ እራሴ ነው ማገባት አለ። አደምም(ዐ.ሰ) እንዲተው ቢነግረው ሊሰማ አልቻለም አሻፈረኝ አለ። በዚህን ጊዜ አደም(ዐ.ሰ) መፍትሔ ይዞ መጣ። ሁለቱም ምፅዋት እንዲያቀርቡ እና ምፅዋቱ ተቀባይነት ያገኘ ለርሱ ሊፈረድለት እና ልጅቱዋንም ሊያገባ ተስማሙ። ቃቢል ከንብረቱ የማይፈልገውን ቆሻሻ የሆነ ሰብል ይዞ ሲመጣ ሀቢል ግን ከንብረቱ ውስጥ በጣም የሚወዳትን ሙክት በግን አቀረበ። ከዛም ከሰማይ እሳት ወርዳ የሀቢልን ይዛው ስትሄድ የቃቢልን ምንም ሳትነካ ተወችው። ቃቢልም እጅጉን ተበሳጨ። ወደ ሀቢልም በመዞር ያንተ ምፅዋት ተቀባይነት አገኘ የኔ አላገኘም እህቴንማ አታገባም እገድልሀለሁ ብሎ ዛተበት። ቃቢልም ታድያ አላህ ሚቀበለው እኮ ከጥንቁቆች(አላህን ፈሪ ከሆኑ አካላት) ነው ብሎ መለሰለት።

{ وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ ابْنَيْ آدَمَ بِالْحَقِّ إِذْ قَرَّبَا قُرْبَانًا فَتُقُبِّلَ مِنْ أَحَدِهِمَا وَلَمْ يُتَقَبَّلْ مِنَ الْآخَرِ قَالَ لَأَقْتُلَنَّكَ ۖ قَالَ إِنَّمَا يَتَقَبَّلُ اللَّهُ مِنَ الْمُتَّقِينَ}

በነርሱም ላይ የአደምን ሁለት ልጆች ወሬ ቁርባንን ባቀረቡና (አላህ) ከአንደኛቸው ተቀብሎ ከሌላው ባልተቀበለ ጊዜ (የኾነውን) በእውነት አንብብላቸው፡፡ «በእርግጥ እገድልሃለሁ» አለው፡፡ (ተገዳዩ) «አላህ የሚቀበለው እኮ ከጥንቁቆቹ ብቻ ነው» አለ፡፡

                     [አል-ማኢደህ:27]

👉አላለቀም ኢንሻአላህ ይቀጥላል............

=-=-=-=

whatsApp

https://whatsapp.com/channel/0....029Va9evBFFy7269vAij

Ummalife

https://ummalife.com/marufabadir

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

➡️ዱዓ አድርገን ለምንድነው አላህ የማይቀበለን?

  - ኢብራሂም ኢብኑ አድሀም በበስራ ገበያ በኩል እያለፈ ሰው ወደርሱ ተሰበሰበና… " አቡ ኢስሃቅ ሆይ! ዱዓእ አድርገን ለምንድነው ተቀባይነት ያላገኘነው?" ብለው ጠየቁት

- እርሱም "ልቦቻችሁ በ10 ነገሮች ስለሞተች ነው"

ብሎ መለሰላቸው

- " ምንድ ናቸው?" ብለው ጠየቁት

- እርሱም…

1️⃣ አላህን አውቃችሁ

ሀቁን በደንብ አልተወጣችሁም

2️⃣ ረሱልን (ሰ.ዐ.ወ) እንደምትወዱ ተናግራችሁ

ከዚያም ሱናውን መከተል ተዋችሁ

3️⃣ ቁርአንን ቀርታችሁ አልተገበራችሁትም

4️⃣ የአላህን ፀጋ እየበላችሁ አላመሰገናችሁም

5️⃣ ሸይጣን ጠላታችን ነው ብላችሁ ጓደኛው ሆናችሁ/ተስማማችሁት

6️⃣ ጀነት ሀቅ ነው ብላችሁ ለሷ አልሰራችሁም

7️⃣ እሳት ሀቅ ነው ብላችሁ ከሷ አልሸሻችሁም

8️⃣ ሞትም ሀቅ ነው ብላችሁ ለሱ አልተዘጋጃችሁም

9️⃣ ከእንቅልፋችሁ ተነስታችሁ የራሳችሁን ነውሮች ዘንግታችሁ በሰው ነውሮች ተጨናነቃችሁ

🔟 በነሱ ምንም ሳትማሩ ሙታኖቻችሁን ትቀበራላችሁ

ብሎ መለሰላቸው ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

أسد المقاومة الفلسطينية في غزة العزة والكرامة

8 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

☞ቁርኣን ውስጥ የሰጅደተ ቲላዋ ብዛት

15 ናቸው።

☞የቁርኣን ክፍሎች (ጁዝ)30 ናቸው።

☞የቁርኣን ምዕራፎች ብዛት(ሱወር)114 ናቸው።

☞የቁርኣን አንቀፆች ብዛት(አያ) 6236 ናቸው።

☞የቁርኣን ቃላቶች(ከሊማ)ብዛት77439 ናቸው።

☞የቁርኣን ፊደላት(የሀርፍ)ብዛት323670 ናቸው

በእያንዳንዱ ሀርፍ አንድ ሀሰና(አጅር) አለው

አንዲት ሀሰና ደግሞ በአስር አምሳያው

ትባዛለች።ታዲያ!እናንተ ሙስሊሞች ሆይ

ቁርኣንን ማንበብም ሆነ በሱ መስራትን

ችላ ብላችሁ አትተው።

👍ለሌሎች ሼር ማድረጎን አይዘንጉ

image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group