UMMA TOKEN INVESTOR

Followings
1
Abu Mohammed shared a
Translation is not possible.

ወላጆቻችን እኛ የነሱን እንክብካቤ ባስፈለገን ወቅት ከአላህ እርዳታ በመቀጠል ወላጆቻችን ያላቸውን አሟጠው ለዚ አበቁን ዛሬ ላይ ወላጆቻችን የእኛ እንክብካቤ ያስፈልጋቸዋልና፣ችላ አንበላቸው እንጠቀምባቸው።

    የብዙሃኖቻችን ጀርባ የተቃናው

የወላጆቻችን ጀርባ ጎብጦ ነው።

{وَقُل رَّبِّ ارْحَمْهُمَا كَمَا رَبَّيَانِي صَغِيرًا}

ጌታህንም አላህን ብለህ ለምነው ጌታዬ ሆይ ወላጆቼን እዘንላቸው ህፃን እያለሁኝ ያዝኑልኝ እንደ ነበር🤲

አላህ ሆይ ረጅም እድሜ ከተሟላ ኢማን እና አፍያ ጋር ወላጆቻችንን አጎናፅፍልን🤲🤲🤲ኢብኑ ተማም አቡ ማሂ🌹

https://t.me/httsibnutemamAbumahi114

https://t.me/Abmahimukeibnutemam114

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Mohammed shared a
Translation is not possible.

ጾመኛ ሆነህ ረስተህ ከበላይ ወይም ከጠጣህ ያበላህና ያጠጣህ አላህ ነውና ዝም ብለህ ጾምህን ቀጥል!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Mohammed shared a
Translation is not possible.

🌙

     የረመዷን ዝሆኖች ተጠንቀቁ!!

  ኢማሙ ማሊክ አላህ ይዘንላቸው መስጂድ አል_ነበዊ ውስጥ ተቀምጠው የረሱልﷺ  ሐዲስ ያስተምሩ ነበር። ከዕለታት በአንዱ ቀን በማስተማር ላይ ሳሉ አንዱ ድምፁን ከፍ አድርጎ

  "መዲና ውስጥ ዝሆን ገብቷል… መዲና ውስጥ ዝሆን መጥቷል"

እያለ ይጮሃል።

ጩኸቱን የሰሙ ተማሪዎች ከአንዱ በስተቀር ሁሉም እየሮጡ ዝሆኑን ለማየት ወጡ። ምክንያቱም ከዝያ ቀን በፊት ዝሆን አይተው አያውቁም ስለ ነበር አጓጓቸው።

  ሁሉም ሲወጡ ብቻውን የቀረው

የሕያ ኢብኑ የሕያ አል_ለይሲ ነበር።

ኢማሙ ማሊክ: 

   "ለምን አብረሃቸው አልወጣህም?"

ብለው ጠየቁት;

የሕያ:

  "ኢማም ሆይ! እኔ ወደ መዲና የመጣሁት ማሊክን ለመገናኘት እንጂ ዝሆን ለማየት አይደለም።"

ሲል መለሰላቸው።

  እንደ ሚታወቀው የኢማሙ ማሊክ ሙወጣእ ከየሕያ ኢብኑ የሕያ አል_ለይሲ በኩል የተላለፈው ጠንካራው እና ተመራጩ ነው።

እናም ወዳጄ………

   ረመዷን ላይ የሚመጡ ብዙ ዝሆኖች አሉ።

ሩጠው እንደ ወጡ ብዙ ተማሪዎች አላማውን የረሳ ዝሆኖች እያየ ረመዷን ሲያመልጠው; ከረመዷን መቅሰም ያለበትን የሚያውቅ የሆነ ሰው ዝሆኖች በማየት ረመዷኑን አያስመልጥም።

  በእርግጥም በአራት እግሩ የሚሄድ ግዙፍ ዝሆን ላይመጣ ይችላል፦

ግን…………

💫በረመዷን የሚለቀቁ ተከታታይ ፊልምና ድራማዎች;

💫የብልሽት መናኸሪያ የሆኑ የብዙኋን መገናኛዎች;

💫ነሺዳ እና መንዙማዎች;

💫በስርዓት ያልገደብከው እጅህ ላይ ያለው ስልክህ;

💫የረመዷን ትርጉምና አላማ ያልገባቸው ጓደኞችህ;

:

:

:

:

    እና የመሳሰሉ ብዙ የረመዷን ዝሆኖች አሉ።

🚫አውቀህ ተ ጠ ን ቀ ቃ ቸ ው!!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Mohammed shared a
Translation is not possible.

🔰 ዝቅ ማለት (መተናነስ)

● ዋጋህን ከሰው እይታ ውስጥ ሳይሆን ከህሊናህ ውስጥ ፈልገው።

የሰው ልጅ ዝቅ ስትል ይንቅሃል፣ ያዋርድሃል.....

አላህ ግን ስትተናነስና ዝቅ ስትል ከፍ ያደርግሃል።

▶ ስለዚህ አላህ ለሚሰጠን ከፍታ ስንል ለአላህ ብለን መተናነስና ዝቅ ማለትን ልማዳችን እናድርገው።

ummalife.com/ReshadMuzemil

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Abu Mohammed shared a
Translation is not possible.

🔰 ባሮችህ ረገፉ

በፈለስጢን ምድር - በአላህ ቤት

በመስጂደል አቅሳ - ነብዩ ባረፉበት

በካኃዲዋ እስራኤል - ረገፉ ህፃናት

ቦምብ ዘነበባቸው - እንቅልፋቸውን በተኙበት

ዓለምም ችላ አለው - ይህን የዘር ማጥፋት

ያረቢ የአላህ - ሰማዩ ሰማይህ

ያራህማን ያራሂም - ምድሩም ምድርህ

ድረስላቸው ጌታችን - ጀባሩ ያአላህ

ሙስሊም የሆኑ - ኢባዱ ራህማን ናቸው

ሰው ናቸውና ያራሂም - ካጠፉም ማራቸው

መንገድ ስተው እንደሆን - መንገድ አሳያቸው

ሙስሊሞቹም ያንተ - ህፃኖች ያንተው

ካንተ ውጭ ሌላ መጠጊያም ዬላቸው!

አዎ ወጀለኞች ነን - ነብሳችንን በዳይ

ድንበር አላፊዎች ነን - በሰጧን አታላይ

ለብልጭልጭ ህይወት - በርከክ ባይ

ለዚህች ለቀን ጤዛ - ደሞም ለዱንያ

ላትሆነን መንገድ - ጀነትን መዝለቂያ

እያጠለቀችልን - የአዛብ ሜዳሊያ

ግን አንገሰፅም - ከዚህ ሁሉም ነገር

በኛ ወንጀል የተነሳ - ሙስሊሙ ሲሸበር

ጠላት ተጠራርተው - ሁሉም ባአንድ ሲያብር

እኛ ስንባላ - በጎሳ በብሄር

እኛ ስንከፋፋል - በቋንቋ በዘር

አስክሬኖች በርክተው - አፈር ሲለብስ በዶዘር

እኛ ቆይ የት ገባን - ቆይ የትስ አለቅን!?

ቆይ ምን ዋጠን - ምንስ ላይ ሰመጥን!?

ሙስሊም ረገፈ እኮ - እኛ በቁም እያለን

ጂሃዱስ አይሳካ - ያአላህ ማለት አቃተን!

የሙስሊም መሣሪያው - ዱዓ ነው እየተባልን፤

ያራህማን ያራሂም - እኛስ ቀሽሞች ነን፤

ሙስሊሞች ነንና - እባክህን ማረን

አዛኝ ነህና - ያአላህ እዘንልን

ውስጣችን ቆሰለ - ደም ዘነበ ከዓይን

ወንድሞቻችን አለቁ - በከሃዲዎች ረገፉብን

እነዛ የሰው አውሬዎች - ያንተን ቤት ደፈሩብን።

ያረቢ የአላህ - ሰማዩ ሰማይህ

ያራህማን ያራሂም - ምድሩም ምድርህ

ያአላህ ያ! ራህማን - ቤቱም ቤትህ

ድረስላቸው ጌታችን - ጀባሩ ያአላህ

ከጭንቅ ጠብቃቸው - ከጭንቅ አውጪ ነህ

ብዙዎች ቆሰሉ - ብዙዎች አለፉ

በህይወት እያሉ - ባሮችህ ደም ተፉ

በዘረጋሃው ምድርህ - ሙስሊሞች ተገፉ

እነዛ አውሬዎች - ሬሳን አሰለፉ

ሴትም አልቀራቸው - ህፃንም ቀጠፉ

ገደልን እያሉ - በደስታም ደነፉ

⭕️ በባረከው ምድርህ - *ባሮችህ ረገፉ* ።

በረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል

ቀን: ጥቅምት 20/2016 E.C [Oct 31/2023 G.C]

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group