UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ሴቱ ወንዱ ፣ ህፃን አዛውንቱ

ጀግና የሆነበት ሀገር #pale*stine

አላሁ አክበር!

🇵🇸🇵🇸🇵🇸🇵🇸

image
image
image
image
image
image
+1
Send as a message
Share on my page
Share in the group
6 month Translate
Translation is not possible.

ገደልነው ሲሉ ህያው ሞተ ሲሉም እየዳነ ዛሬም ድረስ በህይወት ያለ ተንቀሳቃሹ ሰማዕት። ተራማጁ ሸሂድ። የማይነጥፍ የወንድነት ባህር! የፍልስጤማዊያን ኩራት! የዘመኑ አብሪ ኮከብ! የጦር ሊቅ! የኬምስትሪ ደቂቅ። ፍፁም ትሁት አስተዋይና ለስላሳ ቁጥብነትን የተላበሰ ጀግና። መልካም ልብ፣ ደግ ማንነትን የታደለ ወንድ።

ጌታዬ ሆይ!

ብዕሬን እንደ ኻሊድ ኢብኑልወሊድ ሠይፍ የሰላ አድርግልኝ

Mahi Mahisho

አሰልጥኖ የሚያሰማራቸው ወታደሮች፣ አብላልቶ የሚተኩሳቸው ሮኬቶች የወራሪዋን ራዳር ጥሰው ሰማዩን እየሰነጣጠቁ ጠላትን ማሸበር ከጀመሩ እነሆ 23 አመታት ተቆጠሩ። የእስራኤል የስለላ ተቋም ሮኬቶቹ ሲሰሩ እንኳ አያቅም። ተምዘግዛጊ ሮኬቶችን እንደታጠቁ ያወቁት በ2001 አየሩን ሰንጥቀው ከተማቸው ውስጥ ሲያርፉ ነው።

ከእነዚህ ሮኬቶች ጀርባ አንድ የኬምስትሪ ምሩቅ አለ። ለዚህ ብሎ የተማረ። ብረትን ከፖታሺየም ናይትሬትና የወዳደቁ እቃዎችን ከማዳበሪያ ጋር ቀምሞ በቆርቆሮ ሲሊንደር አብላልቶ ሮኬቶቹን የሚያዘጋጅ ታንክን በዲንጋይ የገጠመ ፍፁም ለአላህ ያደረ ዓቢድ። ባመሸበት ቦታ የማያድር ባረፈደበት መንደር የማይውል። በእናቱ ቀብር ላይ እንኳ ያልተገኘ ፍፁም ጥንቁቅ።

ሞሳዶች አስማተኛው ሰይጣን ይሉታል። ከጠቅላይ ሚኒስቴር ሽሞን ፔሬዝ እስከ ቢኒያሚን ኔታንያሆ በሰማይ በምድር የሚፈለግ ረብጣ ዶላር መድበው ደህንነቶቻቸውን አሰማርተው የዛሬሀያ ስምንት ዓመት እንዲገደል ትዕዛዝ ያስተላለፉበት የጋዛው ኮማንደር።

በማለዳ ተነስተው ከስክስ ጫማቸውን አጥልቀው ተራራውን ሮጠው ያላገኙት፣ የጥይት አሩር እየተኮሱ ቦንብ ከአውሮፕላን ቢያዘንቡ ፍፁም ሊገሉት ያልቻሉት የፍልስጤማዊያን ቁልፍ ሰው።

በእግሮቹ የሚራመድ ሸሂድ ቢሉት አትገረሙ። በእርግጥም ልክ ናቸው። ብዙ ጊዜ ከሞት ድኗል። የሞሳድ ደህንነቶች ከጓደኞቹ በአንዱ የእጅ ስልክ ላይ የተጠመደውን ፈንጂ ተኩሰው ሲገድሏቸው፣ መኪናው በድሮን ተደብድባ ሁለት ጠባቂዎቹና አንድ ረዳቱ ሲገደሉ እርሱ ተርፏል። የተማረበትን ዩንቨርስቲ ሊጎበኝ በሄደበት F1 የጦር ጀቶች ዩንቨርስቲውን ዶግ አመድ ሲያደርጉት በህይወት ድኗል። የእስራኤል አየር ኃይል ጋዛ በሚገኘው መኖርያ ቤቱ ላይ ድብደባ ፈፅሞ ሚስቱና ሁለት እንቦቃቅላ ልጆቹን ገድሎ የሙጃሂዶቹን አከርካሪ አጥንት ሰበርነው አዎ አስወገድነው ገደልነው ብለው በደስታ ውስኪ ሲራጩ ነፍሱ አዛኙንና ኃያሉን አላህ ለመገናኘት አልተፈቀደላትም ነበርና አለሁ ብሎ ብቅ ብሏል።

ሙሐመድ ዲያብ ኢብራሒም ይሰኛል። ፍልስጤማዊያን ደይፍ ይሉታል እንግዳ እንደማለት ነው። በእርግጥም እርሱ በወራሪዋ ደህንነቶች ታድኖ ሊገደል፣ ተጠፍሮም ሊያዝ ያልቻለ አሳዳጆቹ እጅ ሳይገባ ሀያ ስምንት አመታቶችን ያስቆጠረ ሁሌም እንግዳ ሰው ነው።

የሙስሊሞች ለቅሶ የእናቶች እሪታ፣ የልጆች ስቅስቅታ በጆሮው ሲንቆረቆር ለበይክ ብሎ በለጋ ዕድሜው የተነሳ ወጣትነቱን በትግል ያሳለፈ ትንታግ ነው። ወንድሞቹ ሲሞሻለቁ፣ እህቶቹ በድምፅ አልባ መሳሪያ ሲወቁ ትከሻም ልቡም ለመሸከም አልፈቀዱለትም፡፡ ድንቡሽቡሽ ፊት ያላቸው እንቦቃቅላ ልጆቹን ትቶ፣ የእናቱን የእጅ ደበሳ ርቆ በጂሃድ ሜዳ ላይ ተሰየመ፡፡

የብሩህ አዕምሮ ባለቤት የመሐፈዝ አቅሙ ከፍተኛ የሰማውን ቀብ፣ ያየውን ልቅም አድርጎ የሚይዝ ፈጣን ነው። በየትኛውም ቴሌቪዥን ታይቶ አይታወቅም። ምንም አይነት ቴክኖሎጂ የማይጠቀም ባለ ዊልቸሩ የጦር መሪ።

አባቱ ልብስ እየሰፉ በአነስተኛ የዶሮ እርባታ እንቁላል እየሸጡ ያሳደጉት ልጅ ዛሬ ስሙን እንጂ ማንነቱን ለማወቅ ከብዷል። አላህ ረጅም ሐያት ከሙሉ አፊያ ጋር!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

‹አል-አቅሷ› የመጀመሪያው የሙስሊሞች ቂብላ

1. መስጂድ አል-አቅሷ የቦታና የመስጂድ ሥም ብቻ ሳይሆን ከእስልምና ሃይማኖት ጋር የሚያገናኙት በርካታ ቁምነገሮች አሉ፡፡ አላህ (ሱ.ወ.) መስጂድ አል-አቅሷና ዙሪያውን የተባረከና የተቀደሰ አካበቢ ብሎታል፡፡

(አል-ኢስራእ ፡1)

2. ሌላው አል-አቅሷን ከሙስሊሞች የሚያስተሳስረው የኢስራእና ሚዕራጅ ምድር መሆኑ ነው፡፡ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ወደ ሰማዩ ዓለም ጉዞ ባደረጉ ጊዜ ከመካው መስጂድ ወደ መስጂድ አልአቅሷ ከዚያም በመነሳት ነበር ወደ ሰማዩ ዓለም የተጓዙት፡፡ ነቢዩ ከመካ ወደ በይት አልመቅዲስ መጓዛቸው የቦታውን ታላቅነትና ቅድስና ያመለክታል፡፡

3. በአል-አቅሷ መስጂድ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ነቢያትን ኢማም ሆነው አሰግደዋል፡፡

4. የነቢያት አባት ነቢዩ ኢብራሂምን (ዐ.ሰ.) ጨምሮ አል-አቅሷና አካባቢው ብዙ የአሏህ ነቢያት የተላኩበት ምድር ነው፡፡

5. እንደ አብዛኞቹ ዑለማኦች ስምምነት አል-አቅሷን ለመጀመሪያ ጊዜ የገነቡት አባታችን አደም (ዐ.ሰ.) ሲሆኑ ኋላ ላይ ግን ነቢዩ ሱለይማን ኢብኑ ነቢዩ ዳዉድ (ዐ.ሰ.) ግንባታውን በማደስ አጠናከሩት፡፡

6. በምድር ላይ አሏህን ለማምለክ ታስቦ የተገነባው የመጀመሪያው መስጂድ መስጂድ አልሐራም (ከዕባ) መሆኑ ይታወቃል፡፡ አል-አቅሷ በምድር ላይ የተገነባ ሁለተኛው መስጂድ ሲሆን በሱ እና በከዕባ መካከል የአርባ አመት ዕድሜ ብቻ ነው ያለው፡፡

7. አል-አቅሷ የመጀመሪያው የሙስሊሞች ቂብላ ነው፡፡ ሙስሊሞች ቂብላ/የሶላት መቀጣጫ/ ወደ ከዕባ/መካ/ እንዲሆነ ከመደረጉ በፊት ለአሥራ ስድስት ወይም ለአሥራ ሰባት ወራት ወደዚያ ዞረው ሰግደዋል፡፡

8. ጓዝ ተጭኖና ስንቅ ተቋጥሮ ለጉብኝትም ሆነ ለሶላት ከሚኬድባቸው ሶስት መስጊዶች ውስጥ አንዱ አል-አቅሷ ነው፡፡

9. በአልአቅሷ ውስጥ የሚሰገድ ሶላት በሌላው መስጂድ ውስጥ ከሚሰገደው በደረጃ በአምስት መቶ እጥፍ ይበልጣል፡፡

10. በአል-አቅሷ መስጂድ ውስጥ የሚሰገደውን ሶላት ሊበልጥ የሚችለው በመካ (መስጂድ አልሐራም)ና በመዲና የነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) መስጂድ ውስጥ የሚሰገደው ሶላት ብቻ ነው፡፡

11. አሏህ ሐቅ ላይ ሆነው ለሚዘልቁ በበይት አልመቅዲስ ጉያ ለሚገኙ ሙስሊሞች ድልን ድል እንደሚሰጣቸው ቃል ገብቷል፡፡

12. በርካታ ሶሓቦችና ትላልቅ ደጋግ ሰዎች የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ስለ አል-አቅሷ ደረጃና ቅድስና ያስተማሩትን በመከተል ወደዚያ ሄደዋል፡፡ ጎብኝተውታል፡፡ ሰግደውበታል፡፡

13. አል-አቅሷ በታሪክ በተለያዩ ገዥዎች ሥር በቅብብሎሽ ከቆየ በኋላ ሙስሊሞች የከፈቱት በኸሊፋ ዑመር ኢብኑ አልኸጣብ (ረ.ዐ.) ዘመን ነበር፡፡

14. ከዚያ በኋላ በርካታ ሶሓቦች በበይት አልመቅዲስ በመገኘት ተምረዋል፣ አስተምረዋል፡፡ እዚያው ቆይተው ከሞቱት ታላላቅ ሶሓቦች መካከል ዑባዳ ኢብኑ አስሷሚት እና ሸዳድ ኢብኑ አውስ (ረ.ዐ.) ይገኙበታል፡፡ የተቀበሩትም ከመስጂዱ ቅጥር ግቢ ውጭ በሚገኘው ባብ አር-ረሕመህ በሚሰኘው ቦታ ላይ ነው፡፡

15. አልአቅሷን ከጎበኙ ታላላቅ ሶሓቦች መካከል ዑመር ኢብኑ አልኸጣብ፣ አቡ ዑበይዳ፣ የምእመናን እናት ሶፍያ ፣ ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል፣ ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር፣ ኻሊድ ኢብኑ አልወሊድ፣ አቡ ዘር፣ አቡ ደርዳእ፣ ሰልማን አልፋሪሲይ፣ ዐምር ኢብኑ አልዓስ፣ ሰዒድ ኢብኑ ዘይድ፣ አቢ ሁረይራ፣ ዐብዱላህ ኢብኑ ዐምር እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡

16. በርካታ ትላልቅ የሙስሊሙ ዓለም ሊቃውንትም ለትምህርትና ለኑሮ ወደዚያው ተጉዘዋል፡፡ ታዋቂው ሙፈሲር ሙቃቲል ቢን ሱለይማን፣ ኢማም አልአውዛዒ፣ ኢማም ሱፍያን አስሠውሪይ፣ ኢማም ለይሥ ኢብኑ ሰዕድ፣ ሻፊዒይና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡

17. ይህ አካባቢ የሰው ልጆች ከሞት በኋላ የሚነዱትና እንዲሰበሰቡ የሚደረጉበት ምድርም ነው፡፡

18. አል-አቅሷና ምሥራቅ የአል-ቁድስ ከተማን አይሁዶች የተቆጠጣሩት የግማሽ ምዕተ አመት ዕድሜ አንኳን አልሞላውም፡፡

የፍልስጤም ምድርም ሆነ በአጠቃለይ ሻም የሚባለው ሀገር የበርካታ የአሏህ ነቢያት መፍለቂያ ነው፡፡ አል-አቅሷ ደግሞ ሻም የሚባለው ምድር ልብ ነው፡፡

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group