UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እስራኤላውያን ሰፋሪዎች በአል-አቅሳ መስጊድ ግቢ ውስጥ ወረራ ፈፀሙ

የፍልስጤም የዜና ወኪል ዋፋ እንደዘገበው እስራኤላውያን ሰፋሪዎች በእስራኤል የፖሊስ መኮንኖች ጥበቃ ስር ሶስተኛውን ቅዱስ ስፍራ አል- አቅሳ ላይ ወረራ መፈፀማቸው ይታወሳል።

በአይሁድ ህግ መሰረት ወደ ግቢው ማንኛውም ክፍል መግባት ለአይሁዶች የተከለከለ ቢሆንም በየጊዜው የሚከሰት አጋጣሚ ነው። የእስራኤል ባለስልጣናት ከጥቅምት 7 ጀምሮ ፍልስጤማውያንን ለዓርብ ፀሎት ወደ ስፍራው እንዳይገቡ ደጋግመው ከልክለዋል ፣ይህም ብዙዎች በብሉይ ከተማ አቅራቢያ ባሉ ጎዳናዎች ላይ እንዲጸልዩ አስገድዳቸዋል ። የእስራኤል ወታደሮች በመስጊዱ ውስጥ በሚገኙ ፍልስጤማውያን ምእመናን ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።

በቀጠለው ውጊያ እስራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ በኩል በሂዝቦላ የሚደርሰውን መጠነ ሰፊ የሮኬት እና ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት ለመመከት የቅድመ መከላከል እርምጃ ወስዳለች። የእስራኤል ጦር እንዳስታወቀው በሺዎች የሚቆጠሩ በኢራን የሚደገፈው የታጠቀ ቡድን የሮኬት ማስወንጨፊያዎችን እሁድ ጠዋት ማውደሙን አስታውቋል። ሂዝቦላህ እና አጋሮቹ ሶስት ተዋጊዎቻቸው መገደላቸውን ተናግረዋል።

ሄዝቦላህ ለተገደለበት ከፍተኛ አዛዥ የበቀል እርምጃ አሁንም መቀጠሉን በመግለፅ 320 ሮኬቶች እና ድሮኖች በእስራኤል ላይ መተኮሱን አስታውቋል። የእስራኤል ጦር እንደገለጸው አንድ የእስራኤል የባህር ኃይል ወታደር በሄዝቦላህ ጥቃት ተገድሏል ብሏል። ዩናይትድ ስቴትስ ከ10 ወራት በላይ የዘለቀው ጦርነት የከፋ ውጊያ ውስጥ እንዳይገባ እየሰራሁ ነው ስትል አስታውቃለች።

በጥቅምት 7 በእስራኤል እና በሃማስ መካከል በጋዛ ጦርነት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በእስራኤል እና በሊባኖስ ድንበር ላይ በየቀኑ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገ ይገኛል። በካይሮ በዩናይትድ ስቴትስ የሚደገፈው የጋዛ የሰላም ድርድር የመጨረሻው ዙር ምንም ውጤት አላመጣም። ሃማስ ወደ ድርድሩ ከመሄዱ በፊት አዲስ የእስራኤልን ቅድመ ሁኔታዎች ውድቅ በማድረግ እስራኤል የገባችውን ቃል ሳትፈፅም ቀርታለች ሲል ከሷል። እስራኤል በሀምሌ ወር መጀመሪያ ላይ ከመጨረሻው የውይይት ዙር በኋላ ጥያቄዎቿን ቀይራለች መባሉን አስተባብላለች።

#gaza #palestine #freepalestine #quran

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

በጎርፍ ለተጎዱ ወገኖች

1000646950647

👉ሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚገኙ በማህበራዊ ሚዲያና በተለያየ መንገድ የሚገናኙ ስለ ጎርፉ አደጋ ድምጻቸውን በማሰማት ላይ የሚገኙ የስልጤ ተወላጆች ለተፈናቃዮች የበኩላቸውን የቁሳቁስ፣ የአልባሳት፣ የምግብ፣ የገንዘብ...ድጋፍ ለማሰባሰብ ነይተው በመነጋገር አስተባባሪ መርጠዋል። ከአስተባባሪዎቹም 3ቱ ተመርጠው በጋራ የባንክ አካውንት ከፍተዋል። ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ ስልካቸውን ፈልገን እናመጣላቹሃለን። የከፈቱት የባንክ አካውንት ደግሞ ከታች የተያያዘው ነው። ሁላችንም የቀኩላችን እናድርግ።

👉ይህ ጉዳይ የስልጤ ብቻ ጉዳይ ስላልሆነ ሌሎች ማህበረሰቦችንም የበኩላቸውን ወገናዊና ሰባዓዊ ድጋፍ እንዲያደርጉ እናስተባብር።

👉አንድ ሆነን በአንድ ቋት ለተረጂዎች እንድረስ። ይህ በሁለቱም ወረዳ ያሉትን ተፈናቃዮች ያገኛትን ነገር ያደርሳል። በለተይ በተለይ በአይነት መደገፍ የምትፈልጉ ከስር አድራሻ አለላችሁ!!

👇👇👇

አዲስ አበባ የምትገኙ

በአይነት አልባሳት፣ ብርድልብስ፣ ፎጣዎች፣ ፓምፐርስ፣  የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስና ምግብ ነክ ነገሮችን በበጎ ፍቃደኝነት የሚንቀሳቀሱ ወንድም እህቶች አሉ አድራሻም ተዘጋጅቷል መለገስ ማቀበል የምትፈልጉ በስልክ ቁጥሮች ደውሉ ባላችሁበትም መተው ይወስዳሉ።

  +251911079793 አዲስ አበባ ማንኛውም አከባቢ

   +251913442474 አዲስ አበባ

   +251927368484 አለም ባንክ አግኖት ዳዛይን

    +251943892917 ቤተል

    +251912351944  ቤተል

     +251975387161  መርካቶና አከባቢው

ለወገን_ደራሽ_ወገን_ነው!!

ሼር ሼር ሼር በማድረግ እናዳርሰው!!

https://t.me/Ibnugarad

Telegram: Contact @Ibnugarad

Telegram: Contact @Ibnugarad

يا مقلب القلوب ثبت قلبي على دينك
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

*የዓሹራ_ፆም ያለው ትሩፋት*

*فضل صوم يوم عاشوراء*

ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ አንሁ) በዘገቡት ሀዲስ ነቢዩ (ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም) ወደ መዲና በመጡ ግዜ የሁዶች ዓሹራን ሲፆሙ አይተዋቸው ለምን እንደሚፆሙት ሲጠይቋቸው \"ይህ ቀን መልካም ቀን ነው፣ አላህ በኒ ኢስራኢልን ከጠላታቸው ነፃ ያወጣበት ቀን ነው፣ በዚሁ ምክንያት ሙሳ (ዐለይሂ አሰላም) ፆሙት\" በማለት መለሱላቸው። ነቢዩም (ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም) \"እኔ ለሙሳ ከናንተ ይበልጥ የተገባው ነኝ\" በማለት ፆሙት ሌሎችም እንዲፆሙት አዘዙ። (ቡኻሪ) በሌላ

በሙስሊም ዘገባ \"ይህ ታላቅ ቀን ነው። ሙሳንና ህዝቦቹን ነፃ ያወጣበትና ፈርኦንንና ህዝቦቹን ያሰመጠበት\" በማለት ተዘግቧል።

عن ابن عباس رضي الله عنهما قال: قَدِمَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وآله وَسَلَّمَ المَدِينَةَ فَرَأَى اليَهُودَ تَصُومُ يَوْمَ عَاشُورَاءَ، فَقَالَ: «مَا هَذَا؟» قَالُوا: هَذَا يَوْمٌ صَالِحٌ، هَذَا يَوْمٌ نَجَّى اللهُ بَنِي إِسْرَائِيلَ مِنْ عَدُوِّهِمْ، فَصَامَهُ مُوسَى، قَالَ: «فَأَنَا أَحَقُّ بِمُوسَى مِنْكُمْ»، فَصَامَهُ، وَأَمَرَ بِصِيَامِهِ. أخرجه البخاري في صحيحه.

وفي رواية مسلم- ((هذا يوم عظيم أنجى الله فيه موسى وقومه وغرّق فرعون وقومه))

فعَنْ ابْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُمَا قَالَ : مَا رَأَيْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَتَحَرَّى صِيَامَ يَوْمٍ فَضَّلَهُ عَلَى غَيْرِهِ إِلا هَذَا الْيَوْمَ يَوْمَ عَاشُورَاءَ وَهَذَا الشَّهْرَ يَعْنِي شَهْرَ رَمَضَانَ . \" رواه البخاري

ኢብኑ ዐባስ (ረዲየላሁ አንሁ) \"ነቢዩ (ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከዓሹራእ እና ከረመዳን ሌላ አንድንም ፆም ከሌላው አስበልጠው ትኩረት የሰጡበት አላየሁም\" ብሏል። (ቡኻሪ)

فعن عَبْدِ اللهِ بْنِ عَبَّاسٍ رَضِيَ اللهُ عَنْهُمَا قال: حِينَ صَامَ رَسُولُ اللهِ صَلَّ اللهُ عَلَيْهِ وآله وَسَلَّمَ يَوْمَ عَاشُورَاءَ وَأَمَرَ بِصِيَامِهِ قَالُوا: يَا رَسُولَ اللهِ، إِنَّهُ يَوْمٌ تُعَظِّمُهُ الْيَهُودُ وَالنَّصَارَى، فَقَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وآلِهِ وَسَلَّمَ: «فَإِذَا كَانَ الْعَامُ الْمُقْبِلُ إِنْ شَاءَ اللهُ صُمْنَا الْيَوْمَ التَّاسِعَ» قَالَ: فَلَمْ يَأْتِ الْعَامُ الْمُقْبِلُ حَتَّى تُوُفِّيَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وآلِهِ وَسَلَّمَ. أخرجه مسلم في \"صحيحه\"

አብደላህ ኢብኑ አባስ (ረዲየላሁ አንሁ) የአላህ መልእክተኛ ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም የአሹራን ቀን ፁመው ሰሀባዎቻቸውንም እንዲፃሙ ባዘዙ ጊዜ፦ ይህ ቀን እኮ አይሁዶችና ነሳራዎች የሚያልቁት ቀን ነው አሉዋቸው። እሳቸውም፦ \"የአላህ ፍቃድ ሆኖ ቀጣይ አመት ከደረስን ዘጠነኛውንም ቀን እንፃማለን\" አሉ። ነገር ግን የቀጣዩ አመት አሹራ ሳይደርሱ ሞቱ።\" (ሙስሊም)

ዘጠነኛውን ቀን መጨመር የተፈለገበት ምክንያት ከአይሁዶችና ከነሳራዎች ለመለየት ነው።

وقال رسول الله صلى الله عليه وسلم : \" صِيَامُ يَوْمِ عَرَفَةَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ وَالسَّنَةَ الَّتِي بَعْدَهُ وَصِيَامُ يَوْمِ عَاشُورَاءَ أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ \" رواه مسلم

የአላህ መልክተኛ ( ሷለላሁ አለይሂ ወሰለም) \"የዐረፋ ቀን ጾም ያለፈውን አመትና የቀጣዩን አመት ወንጀል እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ። የዓሹራ ፆም ደግሞ ያለፈውን አመት ወንጀል እንደሚያብስ ከአላህ እጠብቃለሁ\" ብለዋል። (ሙስሊም)

በነዚህ ፆሞች የሚታበሱት ወንጀሎች ትናንሽ (ሰጋኢር) ወንጀሎች ናቸው። ትላልቅ ወንጀሎች የተለየ ተውባ ይፈልጋሉ።

በዘንድሮ አመት 1446 አመተ ሂጅራ ዘጠነኛው ቀን ሰኞ ሲሆን አስረኛው ማክሰኞ ስለሆነ ሁላችንም እንዳያመልጠን በጉጉት እንጠባበቅ ።

★ በእነዚህ ቀናት ጾም ከመጾም ውጭ ከወትሮው ለየት ያለ የሚደረግ ኢባዳም ሆነ የሚኬድበት ቦታ የለም ።

አላህ ደርሰው ከሚፆሙት ያድርገን ይወ ፍቀን

✍️ኡስታዝ ሙሀመድ ፈረጅ

Send as a message
Share on my page
Share in the group