UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

የጁሙዓ ኹጥባ ተጀምሮ ሚንበር ላይ ኢማሙ ቁመው ሲኾጥቡ ታዳሚዎቹ በፅሞና በማዳመጥ ላይ ናቸው። (ኢማሙ ነቢ ሰዐወ ነበሩ)

ከጀመዓው መሀል የሰልፉን እኩሌታ እያቆራረጡ የሚመጡ ሁለት ቀያይ ተመሳሳይ ቀሚሶችን የለበሱ ህፃናት ይታያሉ። ጨቅላ ከመሆናቸው የተነሳ እየተንገዳገዱ ነበር ሚራመዱት፤ ኢማሙ ይህን ትዕይንት ሚንበር ላይ ሁነው መቋቋም ተሳናቸው።

እኚህ አያት የልጅ ልጆቻቸው እየተንገዳገዱ ሲመጡ ተመልክተው መቻል ቢያቅታቸው ታዳሚውን ትተው ከሚንበሩ ወረዱ። ልጆቹንም በስስት እቅፍ አድርገው በታፋቸው ካስቀመጡ በኋላ ወደ ህዝቡ ዙረው፦‹‹እንደው አላህ ልጆች ፈተና ናቸው ያለው'ኮ እውነቱን ነው። እኔ እኚህ ህፃናትን ሳይ አንጀቴ አልችል ቢለኝ እኮ ነው ሚንበሬን ትቼ የወረድኩት›› ብለው ኹጥባቸውን ቀጠሉ።

--------

ጃቢር የነቢ ሰዐወ የቅርብ ሰው ነው። ቤታቸው ሲገባ የገጠመውን እንዲህ ይተርካል።

ነቢ ሰዐወ ቤት ስገባ ነቢ በሁለት እግራቸው ተንበርክከው በሁለት እጃቸው ደግሞ መሬትን ይዘው ሁለቱን የልጅ ልጆቻቸውን ከጀርባቸው አዝለው እንደ ፈረስ ሲያጫውቷቸው ተመለከትኩ።

ከልጆቹ ልቀልድ ፈልጌ፦‹‹ምንኛ ያማረ ፈረስ ላይ እየጋለባችሁ ነው! ›› አልኳቸው።

ነቢም ሰዐወ ልጆቹን በጀርባቸው እንብርክክ እንደተሸከሙ፦‹‹እነሱስ ቢሆኑ ምንኛ ያማሩ ፈረሰኞች መሰሉህ›› ብለው ቀለዱ።

---------------

እንዲሁ በሌላ ቀን እኒህ ልጅ ወዳድ የሆኑ ነቢይ ተከታዮቻቸውን እያስከተሉ በመስገድ ላይ ሳሉ ቤት የለመደ ህፃን ከመስጂድ ሱጁድ ሲያደርጉ ተመልክቶ ከጀርባቸው ላይ ሊጋልብ ወጣ።

ነቢ ሰዐወ ልጅ ያከብራሉ። ከጀርባቸው ግልቢያውን ጠግቦ እስኪወርድ ሱጁድ አድርገው ጠበቁት። ከብዙ ቆይታ በኋላ ሲወርድ እሳቸውም ከሱጁድ ቀና አሉ።

በመጨረሻም ሰላቱ ሲጠናቀቅ ከኋላ ሁነው ሲሰግዱ የነበሩ ሰሓባዎች ሱጁድ እጅግ ስለረዘመባቸው ለምን እንደረዘመ ጠየቁ።

ነቢም ሰዐወ፦‹‹ይህ ልጄ ሱጁድ ላይ ሳለሁ ከጀርባዬ ወጥቶ ጫወታውን ጀመረ። ጨዋታውን ሳይጨርስ እንዳላቋርጠው ብዬ ሱጁዴን አስረዘምኩት›› አሉ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የከሰረው ነጋዴ‼️

አስመዒ የተባለው አሊም الله ይዘንለት መንገድ እየሄደ ያጋጠመውን ገጠመኝ እንዲህ ብሎ ያጫውታል።

👇

👇

👉" መንገድ ላይ እየሄድኩኝ አንዲት ልጅ በዘንቢል ነገር ሩማን የተባለው ፍሬ ተሸክማ ትሄዳለች።

አንድ ጎረምሳ ከኋላዋ ይከተላትና እሷ ሳታየው ከያዘችው ሩማን አንድ አንስቶባት(ሰርቆ) ይሄዳል። እኔም ጎረምሳውን ተከትዬ መሄድ ጀመርኩኝ።

ከሆነ ቦታ ላይ ሲደርስ አንድ ምስኪን ሰውዬ ያገኝና ከልጅቷ የሰረቀውን ሩማን ለምስኪኑ ሰውዬ ሰጠው።እኔም ተገረምኩኝና እንዲህ ብዬ ጠየኩት።

ከልጅቷ ስትሰርቃት እኮ እርቦህ መስሎኝ ነበር ግን ለሌላ ሰው ሰጠክ ስለው

👉 {እኔማ ከጌታዬ ጋ እየነገድኩኝ ነኝ} አለኝ

እንዴት ነው ከጌታህ ምትነግደው? ስለው

=> {ከልጅቷ ስሰርቃት 1 ወንጀል ተፅፎብኛል፣ ሰደቃ ሳደርገው ግን 10 አጅር ተፅፎልኛል ዘጠኝ አተረፍኩ ማለት ነው} አለኝ

እኔም እንዲህ ብዬ መለስኩለት

👇

👉 ከልጅቷ ስትሰርቃት 1 ወንጀል ተፅፎብሀል ሰደቃ ስታደርገው ግን ምንም አጅር አልተፃፈልህም።

   ምክንያቱም

    👇👇👇👇👇👇

إن الله طيب لا يقبل إلا طيبا

/አላህ ንፁህ ነው ንፁህ የሆነ ነገር እንጂ አይቀበልም/

ብዬው ተለያየን"  ይላል

👌 የሚገርመው ይህ አይነቱ ተግባር በዘመናችን በጣም በዝቶ ይታያል

ብዙሀኖች ለራሳቸውም ይሁን ለሌላው ያለ ዕውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ፣

ለባጢል ይከራከራሉ በነሱ ዕይታ ብቻ ሀቅ ስለ መሰላቸው

   ጠመውም ያጠማሉ

🤲 አላህ ጠቃሚ የሆነ ዕውቀትና ተቀባይነት ያለው ስራ ይወፍቀን

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሹፉ

9 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አስተማሪዎች የማስተማርን ክብደት ይወቁ❗

🚫"ያገኘኸውና የመሰለህን

ሁሉ ዝም ብለህ አትናገር!"

📂አል-ቀዕነቢይ እንዲህ ይላሉ፥["ኢማሙ ማለክ ወዳሉበት ስገባ እያለቀሱ ደረስኩኝ ምነው? ስላቸውም "ከእኔ ይልቅ ማልቀስ የሚገባው ማን አለ?! የምናገረው እየተጻፈ በየአቅጣጫው እየተሰራጨ ነው" ]አሉኝ።

⭕እንግዲህ ኢማሙ ማሊክን ያስለቀሳቸው ዒልማቸው በስፋት መተላለፉ ነው በዚህ ዒልምና ደረጃቸው ዕውቀቴ ተሰራጨ ብለው ሰግተው ይህን ያክል ከተጨነቁ የሳቸውን ዕውቀት ሩቡን እንኳ ያልደረሱ ሰዎች እርግጠኛ ባልሆኑበትና አላህ ዘንድ የሚሰጡት መልስ በሌላቸው ነገሮች ላይ ሰውን የሚያሳስቱና እንደልባቸው የሚናገሩ ሰዎችን ምን እንበላቸው?

🔹ኢማሙ ማሊክ በዚህ ብቻም አላበቁም የሐጅ ወቅት ሲደርስ ማስተማር ያቆሙ ነበር! "ምነው?" ሲባሉም፡-

( "ለሐጅ ከተለያየና ሩቅ ከሆነ ቦታ የመጡ ሰዎች ዛሬ የተናገርኩትን ሰምተው ቢሄዱና ከዛም ስህተት መሆኑን አውቄ ሀሳቤን ብቀይር እነሱን የት አግኝቼ ልነግራቸው ነው?!") ብለው መልስ ሰጡ!!

👉🏻ይህ ነው እንግዲህ የአላህ ፍራቻ ማለት!

እኛስ በምናስተላልፈው ነገር ምን ያክል አላህን እየፈራን ነው !!??

🔎ምንጩ ያልታወቀን ትምህርት የምናስተላልፍ ማስረጃውን ጠንቅቀን የማናውቀውን ንግግር የምንነጋገርና የምናሰራጭ ሰዎች ለራሳችን እንዘን!

🌐ሶሻል ሚዲያ ላይ ዝም ብለው ደስ ያላቸውን ሁሉ የሚለጥፉ ሰዎችም ከታላቁ ኢማም ይማሩ ምንም ነገር ከመልቀቃቸው በፊት ቆም ብለው ያስቡ ደሊሉን (መረጃውንም) ያገናዝቡ!

✍UAA

ሀሙስ 20/2/1439 ዓ.ሂ

@ዛዱልመዓድ

🔸 🔹 🔸🔹 🔸🔹🔸

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group