UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

TOO BAD! ========= ✍

After the Zionists bombed the international internet cable of the only jewelry company that connected Gaza to the international community, the voices of Gazans were suppressed and they were bombarded continuously for more than 3 hours. In addition, fire is raining down on them in the sea, in the air, and on the earth.She(Israel) also visited(Destroyed)the main Alshifa Hospital, where more than 40,000 patients are present. You don't want to see a single Palestinian in your life. Even the ambulances were unable to pick up the dead and wounded. Israel is killing our people by turning off its voice so that its crimes and horrible attacks are not recorded in the media‼

(Translated copy of Ibrahim Seid or Murad)

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ረሡል ﷺ እንዲህ ብለዋል

አራት ነገራቶች ባንተ ላይ ከተገኙ ዱንያ ላይ ምንም ያለፈህ ነገር የለም!

1-እውነትን መናገር

2- አደራን(አማናን) መጠበቅ

3- ጥሩ (መልካም) ስነ-ምግባር

4- ከሃራም ነገር ንፁህ የሆነን ምግብ መመገብ

{#ምንጭ ሰሂህ አልጃሚ የሃዲስ ቁጥር 873}

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ጊዜ ሁለት ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ ፦

" ከሮም ንጉሰ ነገስት ለሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!! 

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭትሰምተናል ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት 

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ "

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም :-

" ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ 

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ "

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው‼️

============================

ኻሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈለት፦

"ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ 

እመጣለሁ።" 

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት። የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት። 

"ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ 

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።"

#ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ ‼️

============================

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር። 

#ያኔ_ጀግና_ሳለን‼️

============================

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዱ ቤት ደጅ ላይ ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነውና በሩን ሊከፍት 

የሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች። 

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ 

እዚያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን ዝቅ ያደርጉ ነበር። 

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር ‼️

============================

ጊዜው ሰላሀዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው ሰላሀዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ። 

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ጊዜ ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች 

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ። 

#ማንተኛበት_ዘመን‼️ 

___ 

ቀደምት ዑለማዎች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር። 

1.ሰውዬው በሱ እና በአሏህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል። 

2.ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አሏህ ይፋዊ ተግባሩን ያሳምርለታል። 

3፦ሰውዬው የአኺራው ጉዳይ ካስጨነቀው አሏህ የዱንያውንም የአኺራውንም ጉዳይ ያግራራለታል። 

============================

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው‼️ 

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።  አዎ ትልቁ ኪሳራ ይህ ነው!!

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ይህም ትልቅ ኪሳራ ነው። 

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን/ሽን እንድታነቃው ይከጀላል!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Muzemil Abdulhafiz Сhanged his profile picture
6 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group