UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

«የእስራኤል ሀገረ-መንግስት የቆመው በደም እና እንባ ላይ ነው!

ሙሉ ታሪክ እና እውነታ ሳናውቅ አንፍረድ።

የእስራኤል አገረ-መንግስት(the Jewish state) በደም እና እንባ ላይ የቆመች ናት። የዓለምአቀፍ ሚዲያዎች ከፍታችሁ ብትመለከቱ ስለ ፍልፄም ህዝብ መከራ እና ስቆቃ የሚያወሩት በጣም ጥቂት ነው። ምክንያቱም እስራኤል በወንጀል ላይ ወንጀል፣ በበደል ላይ በደል እየፈፈፀመች እራሷን ሁል ጊዜው እንደ ብቸኛ ተበዳይ ስለምታቀርቅ! ዘመናዊ የአፓርታይድ ስርዓት ዘርግታ፣ የፍልፄም ዜጎችን ከሰው በታች እየቆጠረች( subhuman) ጎፈሬዋን አበጥራ የአለም ድግስ ላይ ትቀርባለች። በፍልፄም ህዝብ ላይ ከተፈፀመው ያገጠጠ ግፎች መካከል በጥቂቱ:-

-ከ3.5 ሚልዮን በላይ ህዝብ ከራሱ መሬት ተፈናቅሎ፣ በገዛ አገሩ እንደ ስደተኛ እንዲኖር ተደርጓል፣

-የአይሁድ አገር ለመመስረት የዘር ማፅዳት ፖሊሲ ላለፉት 75 ዓመታት ሲፈፀም ቆይቷል።

-የጋዛ ፀርጥ ላለፉት 18 ዓመታት በከበባ ውስጥ እየኖረ ነው፣

-የተባበሩት መንግሥታት እና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች የአለምአቀፍ ወንጀሎች በእስራኤል እየተፈፀመ መሆኑን በየጊዜው ቢያሳስቡም የምዕራቡ ዓለም ጆሮ ዳባ ብሏል፣

-የፍልፄም ህጋዊ ግዛት( በ1947 በተመድ የተሰመረው) በየወቅቱ እንደ ፌስታል እየሟሸሸ የበሬ ግንባር አክሏል፣

-በራሳቸው ግዛት ላይ እንኳን በየእርምጃው ፍተሻ አለ፣ ፍልፄሞች የማይረግጡት ጎዳና አለ( ለምሳሌ ሄብሮን ግዛት ውስጥ ተመልከቱ)፣

-የፍልፄም ህዝብ ማንነት እና ታሪክ ተነፍጓል፤ ነገር ግን የምዕራቡ ዓለም ለሌላው የራስን ዕድል በራስ መወሰን ብሎ ይሰብካል፣

-እስራኤል የጉልበተኛ አስተዳዳሪ (occupying force) ሆኖ እንኳን ትንሹን የዓለም አቀፍ ግዴታ አለተወጣም፣

-የሰሞኑን ሁኔታ ብቻ ብንመለከት እንኳን ሐማስ ካደረሰው ጥቃት በኋላ እስራኤል የወሰደችው እርምጃ የተገኘውን ፍልፄማዊ የማጨድ ፖሊሲ ነው። እሁድ ጦርነት አውጀናል አሉ፣ ቀጥለው ትናንት ሙሉበሙሉ ጋዛ ከበባ ውስጥ እንድትገባ ታዘዘ(complete siege of Gaza)፣ ይሄንን ያደረጉት ደግሞ ፍልፄሞች እንሰሳ ስለሆኑ ነው አለ የእስራኤል የመከላከያ ሚንስትር። ይሄ ሁሉ እየሆነ፣ አሰቃቂ የዓለምአቀፍ ወንጀሎች እየተፈጸሙ ሳለ፣ ምዕራባውያን በአንድ እግር ቆመው ለሚስኪኗ እስራኤል ድረሱ እያሉ ነው።

በታሪክ የመገፋትን ስሜት የሚያውቅ ሌላውን አይገፋም ይባል ነበር፤ ይሄ ግን ለአይሁዳዊያን እስራኤል አይሰራም!

አየህ፣ ይህች ዓለም የግብዞች ጥርቅ፣ ጉልበተኞች የሚከበሩባት፣ ድሃ የሚበደልባት ሆናለች። እራሱ በድሎ እራሱ የሚያለቅስበት ሜዳ!

ከማንም ጋር አትለጠፍ፣ አጣርተህ ከተበደለው ጋር ተሰለፍ፣ ከፍትህ ጋር ብቻ ቁም! በሀይማኖት ምክንያት አታሽቃብጥ!!!

*የግርጌ ማስታወሻ: እስራኤል የክርስትናም ሆነ የእስልምና ጠበቃ አይደለችም፣ የአይሁድ ምድር ናት።»

Send as a message
Share on my page
Share in the group
siraju din is feeling Celebrate
7 month Translate
Translation is not possible.

እውነታው ይነገር!

-----

አፈንዲ ሙተቂ

------

የአውሮጳ ሀገራት እና አሜሪካ ለ1900 ዓመታት አይሁዶችን ሲወቁ፣ ሲያስፈራሩ፣ ሲዘልፉ፣ ሲጨቁኑ፣ ሲያሰቃዩ፣ ሲዘርፉ፣ ሲገድሉ እና ሲገርፉ ነበር። አይሁዶች የጭካኔ እና የስግብግብነት ምልክት ተደርገው ሲጻፍባቸው ነበር።

=> ዊሊያም ሼክስፒር በጻፈው "የቬኒሱ ነጋዴ" ውስጥ "ገንዘቤን በጊዜ ካልከፈልከኝ ከሰውነትህ አንድ ኪሎ ስጋ ቆርጬ እወስዳለሁ" ብሎ ገንዘብ የሚያበድረው ሻይሎክ የተባለ አራጣ አበዳሪ አይሁድ ሆኖ ነው የተቀረጸው።

=> "ጄኔራል ድሬይፉ" የተባለው አይሁዳዊ የፈረንሳይ ጄኔራል ምንም ሳያጠፋ "የፈረንሳይን ወታደራዊ ደህንነት መረጃ ለጀርመን አሳልፈህ ሽጠሃል"በሚል ተወንጅሎ የደረሰበት መከራ ዓለምን አነጋግሮ ነበር።

=> የናዚ ፓርቲ በጀርመን ስልጣን ሲይዝ የአይሁዶችን ንብረት ከመቀማት ጀምሮ ስድስት ሚሊዮን አይሁዶችን በእቶን እሳት አቃጥሏል።

------

የምዕራቡ ዓለም አይሁዶችን በሚያሰቃይበት እና በሚፈጅበት የመከራ ዘመን በሐዘኔታ አቅርቦ ያስጠለለው የሙስሊሙ ዓለም ነው። በተለይም የኦቶማን ቱርኮች ኢምፓየር በ15ኛው ክፍለ ዘመን ብዙ መርከቦችን በማሰማራት የስፔን አይሁዶችን ከግድያ ለማትረፍ ጥሯል።

በዛሬው ዘመን ግን ታሪክ ተገለባብጦ በወንጀለኛነቱ የሚታወቀው የምዕራቡ ዓለም የአይሁድ ደጋፊ መስሎ ይታያል። አውሮጳዊያን በአይሁዶች ላይ ለሰሩት ግፍ ዕዳውን የሚከፍለው መከረኛው የፍልስጥኤም ሕዝብ ሆኗል።

------

ይስሐቅ ራቢን እና ያሲር አራፋት በ1993 በኦስሎ የሰላም ስምምነት ሲፈራረሙ ነፃ እና ሉዓላዊት ፍልስጥኤም በአስር ዓመት ውስጥ እንደምትመሠረት ተግባብተው ነበር። ይስሐቅ ራቢን ስምምነቱን ፈርሞ አንድ ዓመት ሳይሞላው ተገደለ። የሰላም ስምምነቱን ያፈራረመው የአሜሪካው ቢል ክሊንተን በጀመረው ጎዳና እንዳይቀጥል ለማድረግ ሲሉ "ሞኒካ ሊዊንስኪ" የተባለች ዱርዬ ልከውባት አሳሳቱትና ስራውን እንዳይሰራ ክፉኛ አወኩት። ክሊንተን በመጨረሻዋ ሰዓት አራፋትንና ኢሁድ ባራክን ለማገናኘት ያደረገውንም ጥረት አከሸፉበት። የኦስሎ የሰላም ስምምነትም ሳይተገበር ሃያ ዓመት አለፈው። በመሃሉ እስራኤል የኒውክለር ቦምብ ታጣቂ ሆና ብቅ አለች።

-------

እውነተኛ የፍርድ ተቋም ቢኖር የምዕራቡ በፍልስጥኤማዊያን ላይ ለተሰራው የ75 ዓመት ግፍ ከእስራኤል በላይ ተጠያቂ ይሆን ነበር።

#palestineshallbefree

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አንድ ትንሽዬ ልጅ ለወላጆቹ፦"3 ጥያቄዎቼን የሚመልስልኝ ጠንካራ አሊም አምጡልኝ" አላቸው።

ወላጆቹም በአከባቢያቸው ያለ አንድ ኡስታዝ አመጡለትና አገናኙት።

💠ልጁ፦"ማን ነህ አንተ? እኔ ስለምጠይቀውስ ጥያቄ መልስ እንዳለህ ምን ያህል እርግጠኛ ነህ?"

➣ኡስታዙ፦"ስሜ ዐብዱላህ ይባላል ከአላህ ባሪያዎችም አንዱ ነኝ።ለምትጠይቀኝ ጥያቄዎችም በአላህ ፍቃድ መልስ እሰጥሀለሁ።"

💠ልጁ፦"አንተ ግን ብዙ ዑለማኦች ሊያብራሩልኝ ያልቻሉትን ጥያቄዬን እንደምትመልስልኝ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነህ?

➣ኡስታዙ፦"ልመልስልህ እሞክራለሁ በአላህ እገዛ።"

💠ልጁ፦" 3 ጥያቄዎች አሉኝ።

❶ ➛ እውነት ፈጣሪ አለ? አዎ አለ የምትል ከሆነ አሳየኝ የት ነው ያለው?

❷ ➛ ቀዷ እና ቀደር ምንድነው?

❸ ➛ እውነት ሸይጣን ከእሳት የተፈጠረ ከሆነ እንዴት በእሳት ይቀጣል? ከእሳት ተፈጥሮ እሳት አያቃጥለውም።

"ይሄን ግዜ ኡስታዙ እሳት በሆነች ጥፊ ልጁን አጮለው።

💠ልጁ፦"እንዴ!!! ለምን ትመታኛለህ? ምን ሚያስመታ ነገር ተናገርኩ?

➢ኡስታዙ፦"አረ!!! እኔ አልተቆጣሁም ግን ያሁኗ ጥፊ ለሶስቱም ጥያቄዎችህ መልስ ናት።

💠ልጁ፦"እንዴት? አልገባኝም...

➢ኡስታዙ፦"በጥፊ ስመታህ ምን ተሰማህ?

💠ልጁ፦"በጣም ህመም ተሰማኝ።

➢ኡስታዙ፦"ህመም እንዳለ ታምናለህ?"

💠ልጁ፦"አዎ አምናለሁ።"

➢ኡስታዙ፦"አሳየኝ የት ነው ያለው?"

💠ልጁ፦"አይ አለ ግን ማየት እንኳን አይቻልማ"

➢ኡስታዙ፦"ይህ ለመጀመሪያ ጥያቄህ መልስ ነው።ሁላችንም አላህ እንዳለ እናምናለን ነገር ግን ማየት አንችልም።

እሺ ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ ገምተህ ነበር?"

💠ልጁ፦"አልገመትኩም።"

➢ኡስታዙ፦"እሺ እኔስ አንተን ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ አስቤ ነበር?

💠ልጁ፦"አላሰብክም።"

➢ኡስታዙ፦

Send as a message
Share on my page
Share in the group
siraju din Сhanged his profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group