UMMA TOKEN INVESTOR

nesriya dino shared a
Translation is not possible.

መልካም ሰው ማለት…

ከአቢ በክራ ነፊዓ ቢን አልሃሪስ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ:

﴿أَنَّ رَجُلًا قَالَ : يَا رَسُولَ اللَّهِ، أَيُّ النَّاسِ خَيْرٌ ؟ قَالَ: مَنْ طَالَ عُمُرُهُ وَحَسُنَ عَمَلُهُ ". قَالَ : فَأَيُّ النَّاسِ شَرٌّ ؟ قَالَ : " مَنْ طَالَ عُمُرُهُ وَسَاءَ عَمَلُهُ﴾

“አንድ ሰው እንዲህ አለ፦ አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ‘ከሰዎች ጥሩ ሚባላው ማነው? እድሜው ረጅም ሆኖ በዛው ልክ መልካም ስራው ያማረለት ነው’ አሉት። ‘ከሰዎች መጥፎ የሚባለውስ? እድሜው ረጅም ሆኖ በዛው ልክ ስራው መጥፎ የሆነበት ነው’ አሉት።”

📚 ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል: 2330

Send as a message
Share on my page
Share in the group
nesriya dino Changed her profile picture
6 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
nesriya dino shared a
Translation is not possible.

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ግዜ ሁለት

ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ

እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ።

<<ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!!

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት

ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን

እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ>>

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም

<<ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ

አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ

ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ>>

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው

_____

___

ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል

ደብዳቤ ፃፈለት

<<ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን

የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ

እመጣለሁ።>>

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ

ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት።

የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት።

<<ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም

ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።>>

# ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ

_____

____

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር

መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ

አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ

እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ

ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር።

#ያኔ_ጀግና_ሳለን

_____

____

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ

ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ

ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት

ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ

አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች።

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ

ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ

እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን

ዝቅ ያደርጉ ነበር።

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር !!!

_____

_

ግዜው ሰላሁዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ

ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው

ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል

ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ።

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት

ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ።

#ማንተኛበት_ዘመን

_____

___

ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር።

1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤

በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል።

2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን

ያሳምርለታል።

3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም

የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል።

_____

_

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ

ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ትልቅ

ኪሳራ ነው።

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን እንድታነቃው ይከጀላል!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
nesriya dino shared a
Translation is not possible.

ጠያቂ፡- የተከበሩ ሸይኽ! የቁርኣን አንቀፆችን ግድግዳ ላይ ማንጠልጠል ምንድን ነው ብይኑ?

ኢብኑ ዑሠይሚን፡ ለምንድን ነው የቁርኣን አንቀፆችን ግድግዳ ላይ የምናንጠለጥለው?

ጠያቂ፡ ለጌጥ!

ኢብኑ ዑሠይሚን፡ ለውበት ከሆነ እንግዲያው (ይህን የሚያደርገው) የአላህ አንቀፆችን መቀለጃ አድርጎ ይዟቸዋል ማለት ነው!! እንዴት ተብሎ በልብ ውስጥ ላለ ህመም ፈውስ ሆኖ እንዲሁም መገሰጫ ሆኖ የወረደው የተከበረውና ታላቁ ቁርኣን ለግድግዳ ማስጌጫ ይውላል?!!

ጠያቂ፡- ለበረካ ፍለጋ ከሆነስ?

ኢብኑ ዑሠይሚን፡ ቀደምቶች በንዲህ አይነት ተግባር በረካን ይፈልጉ ነበርን? ማስረጃስ መጥቷል? መልሱ፡- “በጭራሽ አልመጣም” የሚል ነው፡፡ እኛ ዘግይተን የመጣን ትውልዶች ቀደምቶቻችንን የበቃቸው ሊበቃን ይገባል፡፡ ሶስተኛ ምክኒያት ካለ አምጣ

ጠያቂ፡- (የሚያነቡትን ሰዎች) ለማስታወስ

ኢብኑ ዑሠይሚን፡- አንቀፆቹ የሚለጠፉበት ግድግዳ አካባቢ የሚቀመጡ ሰዎች አይተው ያስታውሳሉ? ቀድሞ ነገር ያነባሉ? መልሱ “በጭራሽ!” የሚል ነው፡፡ ምናልባት ጥቂት ካልሆኑ በቀር፡፡ ያውም ከኖሩ ነው፡፡ አራተኛ ምክኒያት ካለ አምጣ

ጠያቂ፡- ከጂን ለመጠበቅ

ኢብኑ ዑሠይሚን፡- መልካም ቀደምቶቻችን በእንዲህ አይነት ተግባር ከጂን ይጠበቁ እንደነበር ማስረጃ መጥቷልን?

ጠያቂው፡- የለም!

ኢብኑ ዑሠይሚን፡- በፍፁም! ስለዚህ እንዴት ሆኖ ነው ይሄ ዘዴ ከቀደምቶቻችን ተሰውሮ ለኛ የተገለጠልን?!!

ስለዚህ ይህን በተመለከተ የምንለው ነገር ቢያንስ ቢያንስ “ቢድዐ ነው!” የሚል ነው፡፡ ይህ እንግዲህ በሆነ መልኩ የቁርኣንን ክብር የሚያዋርድ ከመሆኑ ጋር ነው፡፡ ምክኒያቱም ለምሳሌ የሆነ ገፅ ላይ ወይም ግድግዳ ላይ ((ከፊላችሁ ከፊላችሁን አይማ)) (አልሑጁራት፡ 12) የሚል ይፃፋል፡፡ ስብሰባው ግን በሃሜት የተሞላ ይሆናል፡፡ ይሄ ሹፈት ነው!!

ስለዚህ ግድግዳም ላይ ይሁን ወረቀት ላይ ወይም ሌላ ነገር ላይ የቁርኣን አንቀፆችን ፅፎ ግድግዳ ላይ አንጠልጥሎ ያገኛችሁትን ሁሉ ከዚህ ተግባር እንዲታቀቡ ምከሯቸው፡፡ የአላህ ንግግር ለዚህ ተግባር መገልገል አይቻልም” በለው ወንድምህን፡፡…

(ሊቃኣቱልባቢልመፍቱሕ፡ 25/197)

ሼር ማድረግ እንዳይረሱ፡፡ ጥፋቱ ከብዙ ቤቶች ውስጥ ያለ ነውና ሰዎችን ከጥፋቱ ለመመለስ ያቅሞትን ይጣሩ፡፡

Send as a message
Share on my page
Share in the group