UMMA TOKEN INVESTOR

Mohamed seid baham ko'rdi
Tarjima qilib boʻlmadi.

🔎| መህዲ ማነው❓ |⚡️

▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬

✅:‹‹መህዲ›› በመጨረሻው ዘመን ከደጃልና ዒሳ መምጣት አስቀድሞ የሚነሳ ታላቅ ‹‹ኸሊፋ›› ነው። ‹‹መህዲ›› የማዕረግ ስሙ ሲሆን ‹‹ሁዳ›› ከሚለው ቃል የተገኘና ‹‹የተመራ ቅን ኸሊፋ›› ማለት ነው። መጠሪያ ሙሉ ስሙ ደግሞ ‹‹ሙሐመድ

ኢብን አብዱላህ አል-መህዲ›› ነው።

🔰:ስለ መህዲ በቁርኣን የተነገረ ምንም ነገር አናገኝም። መረጃዎቹ በሙሉ ከሐዲስ የተገኙ ሲሆን #ከሃያ በላይ የተረጋገጡ ዘገባዎች ይገኛሉ። ብዙ የሱንና ዑለማዎች ስለ መህዲ የፃፉ ሲሆን ቲርሚዚና አቡ-ዳውድ ራሱን የቻለ ምዕራፍ ሰጥተውታል። ከሁሉም ታዋቂው ሐዲስ አቡ-ዳውድ የዘገቡት ሲሆን ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፡-

‹‹ትንሳኤ(የውመል ቂያማ) ሊቆም አንድ ቀን ቢቀረው እንኳን አላህ ከቤተሰቤ የሆነን፤ ስሙ ከእኔና ከአባቴ ጋር የሚመሳሰል መሪን ሳያስነሳና በበደል የተዋጠችውን ምድር በፍትህ ሳይሞላት አይተዋትም።››

📕|(አቡ-ዳውድ 4282)|📕

🔭:ከዚህ ሐዲስ እንደምንረዳው መህዲ የነቢዩ (ﷺ) ቤተሰብ ነው። ስሙም የነቢዩን (ﷺ) እና አባታቸውን የያዘ ሲሆን ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ›› ወይም ‹‹አህመድ ኢብን አብዱላህ›› ነው። የሚመጣውም ዓለም በዙልም በተዋጠችበት በመጨረሻው ዘመን ሲሆን የአላህን ቃል ከፍ በማድረግ ፍትህን ያነግሳል።

📮:ኡሙ ሰለማ (ረዲየሏሁ አንሃ) እንደተናገረችው ነቢዩ (ﷺ) ‹‹መህዲ #በፋጡማ በኩል የሚገኝ ቤተሰቤ ነው።›› ብለዋል።

🔎:ኢብኑል ቀይም ይሄንን▽ሐዲስ ሲያብራሩ ࿐

‹‹መህዲ የሐሰን ዘር ሲሆን አል-ሐሰን ለሙስሊሙ አንድነት ሲሉ ኸሊፋነታቸውን አሳልፈው በመስጠታቸው ምክንያት አላህም በመጨረሻው ዘመን ከቤተሰባቸው ታላቅ ኸሊፋ በማስነሳት ክሷቸዋል።›› ሲሉ ፅፈዋል።

📕|(አቡ-ዳወድ 11/373)|📕

🔖:አቡ-ሰዓድ አልኩድሪ በዘገቡት ሐዲስ ነቢዩ (ﷺ) ስለ መህዲ ገፅታ ሲናገሩ ༻

‹‹ቁመቱ ረጂም፣ ትከሻው ሰፊ፣ አፍንጫው አጠፍ ያለ ነው።›› ብለዋል።

📕|(አቡ-ዳውድ 4265)|📕

✅:መህዲ የሚነሳበትን ቦታ በተመለከተ የተለያዩ ዘገባዎች አሉ። ከፊሎቹ ከሻም ከፊሉ ከኹራሳን ሌላው ደግሞ ከመዲና እንደሆነ ይናገራሉ። ኢብን ከሲር የሁሉንም ሐዲሶች ጥቅል ሀሳብ ሲያስቀምጡ ‹‹የሚነሳው ከምስራቅ ነው። ከዚያም ወደ መካ ይሄዳል። ሰዎችም በከዓባ ዙሪያ ቃልኪዳን ይገቡለታል።›› ብለዋል። እንዲሁም በሌላ መጽሐፋቸው ‹‹በሐዲስ በተጠቀሰው መሰረት

ባንዲራው ጥቁር ነው።›› በማለት አብራርተዋል።

📒|(አልቢዳያህ ወልኒያህ 19/63፤ አልፊታን ወልመላሂም 1/49)|📒

🔰:ኢማም አህመድ እንደዘገቡት መህዲ መሪነት ሲመረጥ ፍላጎቱም ክህሎቱም አልነበረውም። እናም ‹‹አላህ በአንድ ሌሊት ይመራዋል።›› ብለዋል (ﷺ)።

ኢብን ከሲር ሐዲሱን ሲያብራሩ፡- ‹‹ይህ ማለት አላህ ይረዳዋል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረውን ችሎታም ይሰጠዋል ማለት ነው።›› ብለዋል።

📓|(አህመድ 2/58/ አልፊታን ወልመላሂም 1/29)|📓

👑:መህዲ #ኸሊፋነትን ከተረከበ በኋላ ሙስሊም አገራትን በአንድ በማፅናት በቀደመው ኢስላማዊ አስተዳደር ስር ያስገባቸዋል። ከዚያም በቡኻሪ እና

ሙስሊም (2897) እንደተዘገበው ከሮማውያን ጋር የመጨረሻው ታላቁ ጦርነት ‹‹አል-መልሃማ አል-ኩብራ›› ይካሄዳል። ሙስሊሞችም ዳቢቅ ላይ ድል ደርጋሉ። ከዚህ በፊት ያልተከፈቱ አገራትንም ይከፍታሉ። ከዚያ በኋላ ሙስሊሞች በየትኛውም ኃይል አይሸነፉም። አላህ አማኞችን ከፍተኛ የሀብት መትረፍረፍ ይባርካቸዋል።

🌴:ሸይህ ዑመር ሱለይማን አል-አሽቀር ሐዲሱን መሰረት በማድረግ እንደተናገሩት ፦

‹‹ይህ ጦርነት ከባድ ውድመትን ስለሚያስከትል ዓለም አሁን ካለችው ስልጣኔ ወደኋላ በመመለስ እንደ ጥንቱ በጦር በጋሻ በፈረስ መጠቀም ይጀምራሉ።›› ብለዋል።

📘|(አል-ቂያማህ አስ-ሱግራ 275)|📘

📌:መህዲ ታላቅ ጦርነት አድርጎ ሙስሊሞችን የበላይ ቢያደርግም ጊዜው የቂያማህ ቀን መቃረቢያ በመሆኑ ከባባዶቹ ፊትናዎች ይከሰታሉ። ከእነዚህም መካከል ቀዳሚው #የደጃል መነሳት ነው። እሱን ተከትለው የዕጁጅና መዕጁጆች ከጉድጓዳቸው ይወጣሉ። በዚህ ጊዜ አላህ ዒሳን (ዓለይሂ ሰላም) ለእርዳታ ይልከዋል። በሐዲስ እንደተጠቀሰው ዒሳ (ዓለይሂ ሰላም) ወደ ምድር የሚወርደው በፈጅር ሰላት ወቅት ነው። ነቢዩ (ﷺ) ሲናገሩ ‹‹መህዲ ዒሳን አሰግደን ይለዋል። ዒሳም እናንተ መሪዎች መሆናችሁ ከቂያማህ ምልክቱ ነውና አንተ አሰግደን ይለዋል። ዒሳም ከመህዲ ኋላ ተከትሎ ይሰግዳል።›› ብለዋል።

📘|(ሙስሊም 225)|📘

🪩:ከዚያ በኋላ ዒሳ ከሙስሊሞች ጋር በመሆን የዕጁጆችንና ደጃልን በመጋደል በአላህ ዕርዳታ ያጠፋቸዋል። ነቢዩ (ﷺ) እንደተናገሩት ‹‹ሙስሊሞች ለሰባት ዓመታት ያህል የየዕጁጆችን አጥንት ቀስትና ጋሻ ለማገዶነት ይጠቀሙበታል። መህዲ በኸሊፋነት የሚቆይባቸው ዓመታት ‹‹ሰባት›› እንደሆኑ አብዛኛዎቹ የሐዲስ ምሁራን ይናገራሉ። ከእነሱ መካከል አንዱ የኢብኑ ማጃህ ሲሆኑ ነቢዩ (ﷺ)

‹‹መህዲ ሰባት አጭር ጊዜያትን ይቆያል።›› ማለታቸውን ዘግበዋል።

📙|(ኢብን ማጃህ 4039)|📙

🔖:አል-መህዲ እስኪመጣ ሙስሊሙ ጂሐድን በመተው መጠበቅ ይኖርበታል? ለሚለው ጥያቄ ሸይህ ሙሐመድ ሷሊህ አል-ሙነጂድ በፈትዋ ገፃቸው እንዲህ ብለዋል ፦

‹‹ከጂሐድ መዘንጋት ከከባባድ ወንጀሎች አንዱ ነው። አላህ ያዘዘው ሁሉም የራሱን ግዴታ እንዲሞላ ነው። መህዲ የራሱ ጂሐድ አለው። ይሄም ህዝብ የራሱን ጂሐድ ማድረግ ግዴታው ነው። አላህ በቁርኣኑ እንዲህ ብሏል፡-

‹‹ሁከትም እስከማትገኝ ሃይማኖትም ሁሉ ለአላህ ብቻ እስከሚሆን ድረስ ተጋደሏቸው። ቢከለከሉም አላህ የሚሰሩትን ሁሉ ተመልካች ነው።››

[አንፋል፡ 39]

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Mohamed seid baham ko'rdi
Tarjima qilib boʻlmadi.

ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ጊዜ ሁለት ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ ፦

" ከሮም ንጉሰ ነገስት ለሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!! 

ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭትሰምተናል ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት 

ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ "

ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም :-

" ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ 

እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ "

#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው‼️

============================

ኻሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈለት፦

"ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ 

እመጣለሁ።" 

ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት። የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት። 

"ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ 

ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።"

#ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ ‼️

============================

በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር። 

#ያኔ_ጀግና_ሳለን‼️

============================

በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዱ ቤት ደጅ ላይ ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነውና በሩን ሊከፍት 

የሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች። 

በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ 

እዚያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን ዝቅ ያደርጉ ነበር። 

#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር ‼️

============================

ጊዜው ሰላሀዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው ሰላሀዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ። 

ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ጊዜ ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች 

ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ። 

#ማንተኛበት_ዘመን‼️ 

___ 

ቀደምት ዑለማዎች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር። 

1.ሰውዬው በሱ እና በአሏህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል። 

2.ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አሏህ ይፋዊ ተግባሩን ያሳምርለታል። 

3፦ሰውዬው የአኺራው ጉዳይ ካስጨነቀው አሏህ የዱንያውንም የአኺራውንም ጉዳይ ያግራራለታል። 

============================

#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው‼️ 

ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።  አዎ ትልቁ ኪሳራ ይህ ነው!!

በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ይህም ትልቅ ኪሳራ ነው። 

ይህን ፅሁፍ በማሰራጨት ጓደኛህን/ሽን እንድታነቃው ይከጀላል!

Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Mohamed seid Profil rasmini o'zgartirdi
7 oy
Tarjima qilib boʻlmadi.

image
Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish