hussein Worku Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

hussein Worku shared a
Translation is not possible.

ወላሂ አንብቡና ሼር አርጉ 👌

ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ተናገሩ"አንድ ሰው በሞተ ጊዜ ዘመዶቹ በቀብር ሥነስርአቱ ላይ ሲጨናነቁ አንድ እጅግ ያማረ ቆንጆ ሰው በጭንቅላቱ በኩል ይቆማል።ጀናዛውም እንደተከፈነ ያ ሰው በከፈኑ እና በሞተው ሰው ደረት መሀል ይሆናል።ከቀብር ሥነስርአቱም በህዋላ ቀባሪ ቤተሰቦቹ ወደ ቤት ሲመለሱ ሁለት ሙንከር እና ነኪር የተባሉ ምላኢኮች ወደ ቀብሩ በመምጣት ጀናዛውንና ያንን ቆንጆ ሰው በመለያየት ያንን የሞተውን ሰው በእምነቱ ጉዳይ ብቻውን በጥያቄ ሊያፋጡት ይሞክራሉ ። ሆኖም ያ ቆንጆ ሰው ይናገራል "ይህ ሰው አጋሬም ጋደኛዬም ነው ብቻውንም ልተወው አልችልም። እናንተ እንድትጠይቁት ከተመደባቹ ስራችሁን መሥራት ትችላላቹ እኔ ግን ወደ ጀነት መግባቱን ሳላረጋግጥ ትቼው እልሄድም"። ከዝያም ወደ ሞተው አጋሩ በመዞር እንዲህ ይለዋል "እኔ አንዳንዴ ድምፅህን ከፍ አርገህ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቀስ ብለህ ስታነበኝ የነበርኩት ቁርአን ነኝ ምንም አትጨነቅ፤ ከሙንከርና ነኪር ጥያቄና መልስ በኃላ ምንም ጭንቀት አይኖርብህም"፤ጥያቄና መልሱም ካለቀ በኃላ ያ ቆንጆ ሰው አል ማሉል አላ በተባሉ የጀነት መላኢኮች የተዘጋጀ በመልካም ሽታ የሚያውድ እና ከ ሀር በተሰራ ልብስ የተዘጋጀ አልጋ ያዘጋጅለታል።

2. ረሰል(ሶ.ዐ.ወ) እንደተናገሩት በቂያማ ቀን በአላህ ሱ.ወ ፊት ስንቆም ከቁርአን የበለጠ ለኛ ሚከራከርልን አይኖርም ከነብይያትም ከ መላኢኮችም በበለጠ።

3. እባክዎን ይህን መልእክት የቻሉትን ያህል ያስተላልፉ። ረሱል (ሶ.ዐ.ወ) እውቀትን ከኔ ለሌላው አስተላልፉ አንድም አረፍተ ነገር ብትሆን እንኩዋን ብለዋል።

4. ይህ መልእክት በ አላህ ፍቃድ በቀጣይ 7 ቀናት ቢያንስ 5 ሚልዬን ሰዎች እንዲዳረስ ዱአ እያደረግን ነው።

እባክዎን ይህን መልእክት ለ ቤተሰብዎ፣ ለዘመድዎትና ላሚያውቅዋቸው ሁሉ በማስተላለፍ ከተትረፈረፈው የአላህ ምንዳ ተጠቃሚ ይሁኑ።

*እርስዎ ቁርአንን ሲይዙ ሰይጣን ራሱን ያመዋል።

*ሲከፍቱት ይወድቃል።

*እያነበቡት ሲያይ ራሱን ይስታል።

*ይህንን መልእክት ሊያስተላልፉ ሲያስቡ ላማዳከምና ለማስነፍ ይሞክራል።

እኔ አሸነፍኩት ምክንያቱም ለእርስዎ መላክ ችያለሁ።

5. እባክዎን ሸይጣንን ያሸንፉና ይህንን መልዕክት ጠቃሚ ነው ብለው ካመኑበት ሼር!!

ለ አላህ ብላችሁ share አርጉ 🙏🙏

Send as a message
Share on my page
Share in the group
hussein Worku shared a
Translation is not possible.

ከረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የተላለፉ 10 ትልላቅ የቂያማ ቀን ምልክቶች:-

1 የደጃል መምጣት !

2 የመርየም ልጅ ነብዩሏህ ኢሳ (ዐሰ) ደጃልን ለማጥፋት ከሰማይ መውረድ!!

3. የየዕጁጅ እና መዕጁጅ መምጣት !

4. በስተ ምስራቅ የ 1ከተማ መሬት መደርመስ ክስተት ማለትም ከተማዋ የት እንደገባች እስማይታወቅ ትጠፋለች። (ትሰምጣለች)

5 ደግሞ እንደዚሁ በስተ ምዕራብ አንድ ትልቅ ከተማ ተገለባብጣ ትጠፋለች።

6 ብዙ የአረብ ግዛት መሬት ይደረመሳል ሰዎች ምድር ምን ነካት?? እያሉ ይነጋገራሉ !

7 ብርቱ የሆነ ጭስ ይነሳል በሰማይ ና በምድር ይሞላዋል ለአማኞች ወረርሽኝ ሲሆን ለከሃዲዎች ቅጣት የሆነ።

8 ፀሀይ በመግቢያዋ ትወጣለች ያኔ መላኢካዎች ብዕራቸውን ያስቀምጣሉ። የተውበት በር ይዘጋል። የመልካም ስራ የመጥፎ ስራ የሁሉ ነገር መቀበያ መዝገብ ይዘጋል።

9 አንድት እንሰሳ ትወጣለች ሰዎችን ምታናግር የሆነች ከሃ* ዲውን ከሃ* ዲ ሙዕሚኑን ሙዕሚን ያለች ምትናገር።

10 ሰዎችን ሁሉ አንድ ቦታ ምትሰበስብ እሳት ትከሰታለች ሰዎች ከሷ የሸሹ አንድ ቦታ ይሰበሰባሉ። አላህም አንድት ምርጥ ንፋስ ይልካል በ ላኢላሀ ኢለሏህ ያመነውን ሁሉ ነፍስ ምትወስድ የሆነች የአላህ የሆነን ነገር ሁሉ ምትወስድ የሆነች!! ሙእሚኖች እንዳለ ያልቃሉ በአሽራሮች በክፉ ከሃዲዎች ላይ ቂያማ ትቆማለሽ። የዛኔ የዱንያ ነገር ያበቃለታል።

ጌታችን ሆይ የተውበት በርህ ሳይዘጋ በፊት እውነተኛ ተውባን ስጠን።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
hussein Worku shared a
Translation is not possible.

ስለ አቅሷ ምን ያውቃሉ??

🕌አቅሷ ማለት፦

   ነብዩﷺ ከጌታቸው ሰላት ለመቀበል ወደ ሰማይ ሲወጡ ጉዞ ያደረጉባት መስጂድ ናት።

{سُبْحَانَ الَّذِي أَسْرَى بِعَبْدِهِ لَيْلًا مِّنَ الْمَسْجِدِ الْحَرَامِ إِلَى الْمَسْجِدِ الْأَقْصَى الَّذِي بَارَكْنَا حَوْلَهُ لِنُرِيَهُ مِنْ آيَاتِنَا إِنَّهُ هُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ}

{ያ ባሪያውን ከተከበረው መስጂድ ወደዚያ ዙሪያውን ወደ ባረክነው ወደ አቅሷ መስጂድ በሌሊት ውስጥ ያስኼደው (ጌታ) ጥራት ይገባው። ከተዓምራቶቻችን ልናሳየው (አስኼድነው)፡፡ እነሆ እርሱ ሰሚው ተመልካቺው ነው፡፡}

    [አል_ኢስራእ:1]

🕌አቅሷ ማለት፦

  ሙስሊሞች ከሂጅራ በኋላ ለአስራ ሰባት ወራት አካባቢ ተቀጣጭተው የሰገዱባት የመጀመሪያዋ ቂብላ ናት።

🕌አቅሷ ማለት፦

  መካ ከምትገኘው መስጂደል ሓራም እና መዲና ከምትገኘው መስጂደል ነበዊ ቀጥሎ ጓዝ ጠቅልሎ መሄድ የተደነገገላት ሶስተኛዋ መስጂድ ናት።

🕌አቅሷ ማለት፦

ነብዩﷺ ኢስራእ ባረጉበት ሌሊት  ሁሉም ነብያቶች ተሰብስበውላቸው ኢማም ሆነው ያሰገዱባት መስጂድ ናት።

🕌አቅሷ ማለት፦

መስጂደል ሓራም እና መስጂደል ነበዊ ሲቀር ሌላ ቦታ ከሚሰገድ ሰላት እሷ ላይ ሲሰገድ አምስት መቶ እጥፍ በላጭነት ያለው መስጂድ ናት።

🕌አቅሷ ማለት፦

   ከመስጂደል ሓራም ቀጥሎ ምድር ላይ የተገነባችው ሁለተኛዋ መስጂድ ናት።

🕌አቅሷ ማለት፦

   አላህ እሷንም ዙሪያዋንም በረካ ያደረጋት የሆነች መስጂድ ናት። {…الَّذِي بَارَكْنَا حَوْلَهُ…}

🕌አቅሳ ማለት፦

    ነብዩላህ ሙሳﷺ አላህ ወደ እሷ አስጠግቶ እንዲያሞተው እና እዝያው አካባቢ እንዲቀበር የተማፀነው ቦታ ናት።

🕌አቅሷ ማለት

  ቡኻሪ በዘገበው ነብዩﷺ እንዲህ ይላሉ፦

  «ነብዩ ሱለይማን መስጂደል አቅሷ ገንብቶ ካጠናቀቀ በኋላ ለአላህ ሶስት ነገር እንዲሰጠው ለመነው። "ፍርዱ የአላህን ፍርድ እንዲገጥም፣ ለማንም ሰው የማይሰጥ የሆነ ንግስና እንዲሰጠው እና ማንኛውም ሰው ሰላትን ለመስገድ ብቻ ፈልጎ ወደዚህ መስጂድ የመጣ እንደሆነ ከመስጂዱ ሲወጣ እናቱ እንደ ወለደችው ቀን ከወንጀሉ የነፃ ሆኖ እንዲወጣ" ነብዩﷺ ሁለቱ እንኳ በእርግጥም ተሰጥቶታል፤ ሶስተኛውም እንደ ተሰጠው እከጅላለሁ» ብለዋል።

🕌አቅሷ ማለት፦

  የቂያማ ቀን መቀሽቀሻዋ ምድር ናት። መይሙና ቢንት ሳዕድ አስተላልፋው ኢማሙ አልባኒ ሰኺኽ ብለውታል።

🕌አቅሷ ማለት፦

   የሚያረጋግጥ ግልፅ መረጃ ባይገኝም: ለመጀመሪያ ጊዜ የገነባው ከፊሎች አባታችን ኣደም፣ ከፊሎቹ የነብዩ ኑሕ ልጅ፣ ሌሎቹ ደግሞ ነብዩ ኢብራሂም እንደ ገነቧት ይዘግባሉ። ከዝያም ነብዩላህ ሱለይማን አሳምረው እንደገነቧት ታሪክ ዘጋቢዎች ያወሳሉ።

  ይህም የመስጂዷ ትልቅነት ከሚያሳዩ ነጥቦች አንዱ ነው።

ዓለም የካዳት ሙስሊሞች የረሷት አቅሷ እነሆ ዛሬ ውሻ ሆኖ ከመኖር  አንበሳ ሆኖ መሞት ምርጫቸው ያደረጉ ጀግና ልጆቿ "ለበይኪ ለበይኪ ያ አቅሷ" ብለው ተነስተዋል።

  አላህ የድል ባንዲራ ያስጨብጣቸው!!

ለበይኪ ለበይኪ ለበይኪ ያ አቅሷ

{وَأُخْرَى تُحِبُّونَهَا نَصْرٌ مِّنَ اللَّهِ وَفَتْحٌ قَرِيبٌ وَبَشِّرِ الْمُؤْمِنِينَ}

አብሽሩ ኢንሻ አላህ ድሉ ቅርብ ነው!!

image
image
image
image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
hussein Worku shared a
Translation is not possible.

▫️ጃዕፈር ኢብን አቡጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁ

┈┈•••✿❒🌹❒✿•••┈┈

           ክፍል አንድ 1⃣

            ✿•••✿•••✿

《ጀዕፈርን፥ ጀነት ውስጥ ሁለት በደም የደመቀ ክንፎች ባለቤት ሆኖ አየሁት።》

       «🎤ነብዩ ሙሐመድ ﷺ»

ምንም እንኳን በቁረይሾች ታላቅ የክብር አይን ቢታዩም የረሱል ﷺ አጎት አቡ-ጧሊብ በሀብት ረገድ ድሀ ነበሩ።

ቤተሰባቸውን መቀለብ የተሳናቸው የብዙ ልጆች አባት የሆኑት አቡጧሊብ ምድረ ዓረቢያን ድርቅ ሲመታት ችግሩ ተባባሰባቸው። ሰብሎችን ያጠፋውና ከብቶችን የፈጀው ረሃብ፥ ህዝቡ ከሞት ለማምለጥ ሲል አጥንት እንዲቆረጥም አስገድዶት ነበር። ነብዩ ረሱል ﷺ ለነብይነት ገና ባልታጩበት በዚህ ቀውጢ ወቅት አጎታቸውን አባስን «የወንድምህ የአቡ-ጧሊብ ቤተሰቦች ብዙ ናቸው።   ሰው በረሃብ እያለቀ ስለሆነ የተወሰኑትን በመውሰድ እንርዳው»  በማለት ሀሳብ አቀረቡ።

   አባስም በሀሳቡ ተስማማ አባስ ከረሱል ﷺ ጋር ወደ አቡ ጧሊብ ሄደው ሀሳባቸውን አቀረቡ። አቡ ጧሊብ የዓሊይን (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ታላቅን አቂልን ትተው ከሌሎቹ መርጠው መውሰድ እንደ ሚችሉ ነገሯቸው።

   ረሱል ﷺ #ዓሊይን ረ.ዐ  አባስ ደግሞ #ጃዕፈርን ረዲየሏሁ ዐንሁን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለመቀላቀል ወሰዷቸው።

ከሃሺም ጎሳ #አምስት ሰወች ነብዩ ሙሀመድን ﷺ በመልክ በጣም ይመስሉ ነበር ይባላል።

    ያጎታቸው ልጆች #አቡሱፍያን ኢብን አል-ሃሪስና #ቁሳም ኢብን አል አባስ፤ የኢማሙ ሻፊኢይ አያት #አስ-ሳኢብ ኢብን ኡበይድ እንዲሁም ከሁሉም በጣም የሚመስሏቸው የልጃቸ ው ልጅ #ሐሰን ኢብን ዓሊይና የአጎታቸው ልጅ #ጀዕፈር ኢብን አቡ ጧሊብ ረዲየሏሁ ዐንሁም ነበሩ።

   የትዳር እና የኢስላም ህይወት

┈┈•••✿❒🌹❒✿•••┈┈

   ጀዕፈር ረዲየሏሁ ዐንሁ በወጣት እድሜው #አስማ ቢንትዑመይስን ረዲየሏሁ ዐንሀ አግብቶ ከአባስ በመለየት ጎጆ መሰረተ። በአቡበክር አስ-ሲዲቅ ረዲየሏሁ ዐንሁ አማካኝነት ከሚስቱ ጋር ኢስላምን በመቀበል ከመጀመሪያወቹ ሙስሊሞች ሆነ። የጀነት መንገድ በሾክ መሞላቷን የተረዱት ጀዕፈርና ሚስቱ ረዲየሏሁ ዐንሁም በቁረይሽ የሚደርስባቸውን ጭካኔና ግፍ በትዕግስት ሊወጡት ቢሞክሩም ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ የመጣው የ ቁረይሽ ሴራ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ፦

«ጌታችን አላህ አንድ ነው» ስላሉ ብቻ በደል እየተፈፀመባቸው ያሉት ንፁሃን ሰዎች ዕጣ ያሳዘናቸው ነብይ ﷺ ወደ ሀበሻ እንዲሰደዱ ትዕዛዝ ሰጡ።

▫️     ስደት ወደ ሐበሻ  ▫️

┈┈•••✿❒🌹❒✿•••┈┈

  

🌹 ክፍል ሁለት ይቀጥላል🌹

https://t.me/UmuNuhBintdarsema

Telegram: Contact @UmuNuhBintdarsema

Telegram: Contact @UmuNuhBintdarsema

አስተያየትም ሆነ ስህተት ካለዎት ✍️?? @Haymanot_Darsema_Umu_Nuh
Send as a message
Share on my page
Share in the group