UMMA TOKEN INVESTOR

Medina Taha shared a
Translation is not possible.

በደቡባዊ ሊባኖስ የሚገኘው ታጣቂ ቡድን ሒዝቦላህ አንድ የእስራኤል ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) መትቶ መጣሉን አስታወቀ።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Medina Taha shared a
Translation is not possible.

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱህ

የተከበራቹ ሙስሊም ወንድም እና እህቶቼ የዚሀ ኢስላሚክ ፕላትፎርም ተጠቃሚ የሆናቹ  ሁላቹም የዚን ፕላትፎርም እድገት እንደምትሹ አምናለው  ነገር ግን አካውንታቸው ጥቂት ፎሎወር ብቻ ሲኖረው የናንተም ሞራል ወደ መዳከም እንደሚያመራ ግልፅ ነው ስለዚህ ይሄን ችግር እንዴት መፍታት እንምንችል አብረን እንየው ↓ 

 

1.ማወቅ ያለብን ለግዜው በዚ ላይ ፖስት የሚደረግ የትኛውም ነገር ተደራሽ የሚሆነው (viral ) የሚወጣው በፎሎወር ብዛት ሳይሆን በተፖሰተበት ጊዜ ነው ግዜው እየቆየ በሄደ ቁጥር እየጠፋ ይመጣል።

 

# ለዚህ መፍትሄው

1.ፖስት ማብዛት ፖስት ሲበዛ አካውንታቹ በየተፖሰተ ቁጥር viral ላይ ስለሚወጣ ፎሎ የማግኘት እድል ይኖራል።

2. Comment ሴክሽን በመጠቀም  

ሁላቹም በዚህ ፖስት ኮሜንት ስር በመግባት የራሳቹን link or user name ትፅፋላቹ ለምሳሌ የኔ = Abubekr Ibn Fulan ሁላቹም የራሳቹን ከፃፋቹ በውሃላ የሌሎችን በመንካት ገብታቹ ፎሎው ትደራረጋላቹ።

ይህ በጣም ቀላሉ ዘዴ ነው  

 

#በተጨማሪም ይህ ፖስት ከቆየ እየጠፋ ስለሚሄድ ሼር ሼር በማድረግ አቆዩት ለሌሎችም እንዲዳረስ

 

ቢስሚላህ አሁን እንጀምረው የኔንም account ፎሎው አድርጉኝ →Abubekr Ibn Fulan

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የዓለም ህዝብ ግን አይገርምም⁉️

=======================

(ዓለም በዚህ ዘመን አይታው የማታውቀው የጦር ወንጀልና የዘር ጭፍጨፋ በጘዝ'ዛ)

||

✍ 365 km² ስፋት ባላት አነስተኛ ከተማ ውስጥ 2.3+ ሚሊዮን ዜጎች ተጠጋግተው ይኖሩባታል። በዚህች densely populated በሆነች ከተማ ላይ ለተከታታይ 3 ሳምንታት ያላባራ ከ12 ሺህ ቶን በላይ ቦምብ ሲዘንብ፤ በዚህም ሳቢያ፦

1) በትንሹ 7,028 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙስሊሞች ሲገደሉ፣

2) ከ70% በላይ የሚሆኑት ህፃናትና ሴቶች ሲሆኑ (2,913 ህፃናትና 1,709 ሴቶች)፣

3) 18,482 የሚሆኑት ለከፍተኛ የአካል ጉዳት ሲዳረጉ፣

4) ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ 481 የሚሆኑት ሲገደሉ (ከመካከላቸው 209 የሚሆኑት ህፃናት ናቸው።)፣

5) ከ1,650 በላይ የሚሆኑት ጀናዛቸው እንኳ ሳይገኝ እስካሁን ድረስ በቦምብ በፈራረሱት ህንፃዎች ስር ሲሆኑ (ከመካከላቸው 940 ህፃናት አሉበት።)፣

6) 731 የሚሆኑ ፈለስጢናዊ ሙሉ ቤተሰቦች ሲገደሉ፣

⑦) 101 የጤና ባለሙያዎች ሲገደሉና 100 የሚሆኑት ሲቆስሉ፣

⑧) 12 ሆስፒታሎችና 32 የጤና ማዕከላት በነዳጅ እጥረትና በቦምብ ጥቃት ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ፣

9) በኢንኩቤተር ውስጥ የሚገኙ ከ130 በላይ የሚሆኑ ህፃናት ያሉበት ሆስፒታል ባጋጠመው በነዳጅ እጥረት ሳቢያ ነፍሳቸው በእንጥልጥል ላይ ሲገኝ፣

⑩) ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ንጹሐን ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች፣ በት/ቤቶች፣ በሆስፒታል ግቢዎች፣ በመስጂዶችና ቤተ ክርስቲያን ተጠልለው ሳለ በዛው ባሉበት ጥቃቱ ሲያገኛቸው…(ከሰው ነፍስ አይበልጥምና ወደ አመድነት ስለተቀየሩት ውብ ህንፃዎችና መሠረተ ልማቶችማ አውርተን አንዘልቀውም።)

የሰለጠነ ተብዬው ዓለም አሁንም «ጦርነቱ ይቁም!» ከማለት ይልቅ «እስራኤል ራሷን የመከላከል መብት አላት፣ ሐማስ መጥፋቱን ማረጋገጥ አለባት፣ ከጎንሽ ነን፣ ሐማስ ሽብርተኛ ነው፣ በሐማስ ጥቃት ለሞቱተረ እስራኤላዊያን አዝነናል!…» እያሉ ነው።

ትንሽ አሻሻልን የሚሉት ደግሞ ጦርነቱ መቆም የለበትም፤ ግን የተወሰነች እርዳታ ይግባላቸው ይላሉ።

እስካሁን በጋዛ መብራት የለ፣ ውሃ የለ፣ ምግብ የለ፣ ነዳጅ የለ…። በዚህ የተነሳ የቆሰሉትና መደበኛ ህመም የሚታመሙትም መታከም አልቻሉም።

ዙሪያውን በከበባ ስለሆነ ለጠናበት ታማሚ የውጭ ሕክምና እንዲያገኝ ማድረግ አልተቻለም።

እስራኤል ከላይ በአየር ከምታዘንበው የቦምብ ዝናብ ባሻገር ከምግብና ውሃ እንዲሁም ከሕክምና ከልክላ በጅምላ ጭፍጨፋ የጦር ወንጀልና የዘር ማፅዳት ወንጀል በመፈጸም ላይ ትገኛለች። ይህ ሁሉ የሚሆነው ዓለም እያዬ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ነው። ተመድ ተብዬውም ሆነ የትኛውም የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ነኝ የሚል ተቋም ሁሉ የውሃ ሽታ ሆኗል። የነርሱ ህግ እነርሱን ለማዳን እንጂ ለሌላው አይሠራም። እነርሱ ዘንድ የሙስሊም፣ የዓረብና የአፍሪካዊ ሞት ከውሻቸው ሞት በታች ነው።

ግን ነፍስ ሁሉ እኩል ናትና የእጃቸውን አንድ ቀን ማግኘት አይችሉም። ነገ ላይ በሌላ የነርሱ አካል ላይ ጥቃት ሲፈጸም በሚዲያቸውም ሆነ ባልተጻፈው ህጋቸው ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ሲለፍፉ እናገኛቸዋለን።

አላህ ውርደታቸውን ያቅርበው፤ ለተበዳዮች ነስሩን ያፍጥነው።

አላህ የአሸናፊዎች ሁሉ አሸናፊ የሆነ ጥበበኛና ታጋሽ ጌታ ነው። አንድ ቀን አይርላቸውም።

||

https://ummalife.com/MuradTadesse

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

وَلَا تَحْسَبَنَّ اللَّهَ غَافِلًا عَمَّا يَعْمَلُ الظَّالِمُونَ ۚ إِنَّمَا يُؤَخِّرُهُمْ لِيَوْمٍ تَشْخَصُ فِيهِ الْأَبْصَارُ

አላህንም በደለኞች ከሚሠሩት ግፍ ዘንጊ አድርገህ አታስብ፡፡ የሚያቆያቸው ዓይኖች በእርሱ እስከሚፈጡበት ቀን ድረስ ብቻ ነው፡፡(ሱረቱል ኢብራሂም 42)

የቂያማ ቀን ባይኖር ምን ይውጠን ነበር 😔

ያረብ ቅጣታቸውን እጥፍ ድርብ አድርገው

የመጎዳዳት ቀን ላይ ያረብ ከተጎጂዎች አታድርገን

❤️❤️❤️اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين ❤️❤️❤️

ለገዳዮች ውርደትን ለተጨነቁት ወንድሞቻችን ድልን ለታመመ መዳንን ለሞቱት ሸሂድነትን  የሚወፈቁበት  በሰለዋት በካህፍ በዱዓ የተዋበ ጁምዓ ይሁንልን

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Medina Taha shared a
Translation is not possible.

የእስራኤል ምርቶች በደቡብ አፍሪካ እንዲታገዱ ጥሪ ቀረበ

የደቡብ አፍሪካ ሶስተኛው ትልቁ የፖለቲካ ፓርቲ የኢኮኖሚ ፍሪደም ተዋጊዎች በዋና ከተማዋ ፕሪቶሪያ በሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ደጃፍ የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል። የፓርቲው መሪ ጁሊየስ ማሌማ የእስራኤል መንግስት “ለሰብአዊነት ምንም ክብር የለውም” ካሉ በኋላ ኤምባሲው እንዲዘጋ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።

ማሌማ በአገሪቱ ውስጥ ያሉ ቸርቻሪዎች በጥቅምት ወር መጨረሻ ላይ በእስራኤል የሚመረተውን ዕቃ ከመደርደሪያቸው እንዲያወጡ አሳስበዋል። "ከእስራኤል ምርቶች ካላነሱ እኛ እራሳችንን እናስወግዳለን፣የእስራኤል ምርቶች በደቡብ አፍሪካ እንዲሸጡ አንፈልግም ፣የንፁሀን ደም በእጃቸው ላይ ካሉ ሰዎች ምግብ አንፈልግም" ሲሉ ማሌማ አክለዋል።

ደቡብ አፍሪካን በበላይነት የሚመራው የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ አርብ ዕለት ከእስራኤል ኤምባሲ በራፍ ላይ ተመሳሳይ አድርጓል።የፓርቲው ምክትል ዋና ጸሃፊ ኖምቩላ ሞኮንያኔ ደቡብ አፍሪካውያን ከፍልስጤማውያን ጋር በመተባበር ከእስራኤል የሚገቡትን ምርቶች እንዲከለከሉ ጠይቀዋል።

ወይዘሮ ሞኮንያኔ ደቡብ አፍሪካ በመካከለኛው ምስራቅ የሚካሄደውን ጦርነት አፋጣኝ የተኩስ ማቆም ጥሪዋን ደግማለች። ባለፈው ሳምንት የፓርቲው የሴቶች ሊግ ቃል አቀባይ ፓርቲው በእስራኤል እና ፍልስጤም ግጭት ውስጥ  የአይሁዳውያንን የደረሰባቸውን ጉዳት ማየት ባለመቻሉ ክስ አቅርቧል።

በስምኦን ደረጄ

#ዳጉ_ጆርናል

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group