UMMA TOKEN INVESTOR

Teleha Muhammed Profil rasmini o'zgartirdi
7 oy
Tarjima qilib boʻlmadi.

image
Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Teleha Muhammed Profil rasmini o'zgartirdi
7 oy
Tarjima qilib boʻlmadi.

image
Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish
Teleha Muhammed baham ko'rdi
Tarjima qilib boʻlmadi.

እስራኤል በጋዛ ባለፉት 24 ሰዓታት በፈፀመችው ጥቃት ከ400 በላይ ሰዎች ተገደሉ

እስራኤል ባካሄደችው የአየር የቦምብ ጥቃት ምክንያት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ከ400 በላይ ፍልስጤማውያን በጋዛ ሰርጥ ተገድለዋል። ይህም እስራኤል የአየር ድብደባ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ የከፋው ጥቃት ተብሏል።

ጥቃቶቹ በጃባሊያ እና በቤቴ ላሂያ በስተሰሜን ጋዛ ሰርጥ፣ በማእከላዊ ጋዛ አል-ረማል ሰፈር፣ በምዕራብ አል ሻቲ ካምፕ እና በደቡብ ካን ዩንስ እንዲሁም ራፋህ ላይ ያተኮሩ ነበሩ። የሕክምና ምንጮች እንደተናገሩት ከተቀሰቀሰ 16ኛ ቀኑን ባስቆጠረው ጦርነት በእስራኤል ጥቃት በጋዛ ሰርጥ ከ400 በላይ ዜጎች ህይወት የቀማ ሲሆን ሲሆን ከእነዚህም አብዛኞቹ ሕፃናትና ሴቶች ናቸው ብለዋል።

እስራኤል በጃባሊያ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያ ላይ ባደረገችው ጥቃት ቢያንስ 30 የሚሆኑ አስከሬኖች ከፈራረሱ ሁለት ቤቶች ላይ ተገኝተዋል። በሰሜን ጋዛ የሚገኘው የኢንዶኔዥያ ሆስፒታል አቅራቢያ የእስራኤል የአየር ድብደባን ተከትሎ ከባድ ጉዳት መድረሱን የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ለአልጀዚራ ተናግረዋል። የእስራኤል ሚሳኤሎችም ሁለት ዋና ዋና ሆስፒታሎችን የመታ ሲሆን እነዚሁ ሆስፒታሎች በአል-ሺፋ እና አል-ቁድስን በተባሉ አካባቢ ይገኛሉ።

የእስራኤል መከላከያ ሃይል በበኩሉ ባወጣው መግለጫ ሀማስ የፈፀመውን ጥቃት ተከትሎ ከ500 በላይ ከቡድኑ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች በዌስት ባንክ ውስጥ ወደ 800 የሚጠጉ ፍልስጤማውያንን ማሰሩን ይፋ አድርጓል። የመከላከያ ሃይሉ እንዳለው 37 የሃማስ አባላትን ጨምሮ 64 ሰዎች በአንድ ሌሊት ታስረዋል።የእስራኤል ጦር በጋዛ የታጋቾችን ቁጥር በተመለከተ አዲስ መረጃም ሰጥቷል። አሁን ላይ 222 ሰዎች በሀማስ መያዛቸው የተረጋገጠ ነው ብሏል።

የፍልስጤም ጠቅላይ ሚንስትር ሙሀመድ ሽታይህ በሰጡት መግለጫ የፍልስጤም የነጻነት ጥያቄ የእስራኤል እርምጃ ምንም ይሁን ምን አይቆምም ብለዋል። ሽታይዬህ በራማላህ የካቢኔ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር በጋዛ ሆስፒታሎች ውስጥ ነዳጅ እያለቀ በመሆኑ በሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናት እና ታካሚዎችን በአስፈሪ ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ ብለዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

image
Xabar sifatida yuborish
Sahifamda baham ko'rish
Guruhda ulashish