UMMA TOKEN INVESTOR

ترجمہ ممکن نہیں

“የተከበሩ ዶክተር ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) ፍልስጤማውያንን በተመለከተ የመከሩት አስደናቂ ምክር...”

✭✭✭✭✭✭✭✭✭✭

ለተከበሩት ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) የሚከተሉት ጥያቄዎች ቀረበላቸው፡

“በአሁኑ ሰዓት በፍልስጥኤማውያን ወንድሞቻችን ላይ እየተደረገ ያለው መከራና ሰቆቃ...ለነሱ (ለፍልስጤማውያን) ዱዓ ማድረግ፣የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ፣ከነሱ ጋር መታገል ይቻላልን?!”

ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) ምላሽ ሲሰጡ እንዲህ አሉ፦

“በሙስሊሞች ላይ ለሚደርሰው ችግር ዱዓ ማድረግ ግዴታ ነው። በንብረትም ሆነ ቁሳዊ ድጋፍ ማድረግ ግዴታ ነው። ለነሱ የሚጠቅመው ይህ ነው።” ይህንኑ ተከትሎ ለሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀረበላቸው፡

“አላህ ኸይር ጀዛችሁን ይክፈላችሁና ይህ ጠያቂ እንዲህ ይላል፡ “የተለያዩ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግና እንዲሁም ይህ ሰላማዊ ሰልፍ ጂሃድ ከማድረግ ይቆጠራልን?!፤ይህ ሰላማዊ ሰልፍ በአላህ መንገድ ላይ እንደመታገል ይቆጠራልን?!” ከዚያም ሸይኽ ሷሊህ አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁሏህ) የሚከተለውን ምላሽ ሰጡ፦

“በሰለማዊ ሰልፍ ምንም አይነት የሚገኝ ጥቅም የለውም፤ይልቅስ ከሰላማዊ ሰልፍ የሚገኘው ትርምስ፣ግርግር፣ረብሻ...ነው። ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት ጠላቶችን ምን የሚጎዱት ነገር አለ?! ምንም አይጎዱም። በጎዳናዎች ላይ ሰልፎችን ማድረግ ጣላቶችን የሚያስከፋ ሳይሆን የሚያስደስት ተግባር ነው። ኢስላም የተቀደሰ ንፁህ የሆነ ሐይማኖት ነው፤ እንዲሁም ኢስላም በዘፈቀደና በስሜት የሚያስኬድ ሐይማኖት አይደለም። ኢስላም በሸራዓዊ እውቀት ተመርኩዞ የተገነባ እምነት ነው። ኢስላም የትርምስና የውዝግብ ሐይማኖት አይደለም፤ይልቁንም ለተጎዱ ሙስሊሞች ለነሱ የሚያስፈለገው: ዱዓ ማድረግ፣ኢኮኖሚያዊ ድጋፍ ማድረግ፣ ወታደራዊ...ድጋፎችን ማድረግ ነው። ስለዚህ በእነዚህም ሆኑ በሌሎች ጉዳዮች ሙስሊሞች የሰለፎችን መንሐጅ ነው መከተል ያለባቸው። ኢስላም በሰላማዊ ሰልፍ ጋጋታና ረብሻ አይደለም እዚህ ደረጃ የደረሠው፤ እንዲሁም ድምፆችን ከፍ በማድረግ፣ ንብረቶችን በማውደም አይደለም ኢስላም የተገነባው። እነኝህ ተግዳሮቶች ለኢስላም ጉዳት እንጂ ምንም አይነት ጠቃሜታ የላቸውም። እነኝህና የመሳሰሉት ተግዳሮቶች ለሙስሊሞች ውጤቱ የከፋ ነው። በል እንዳውም ካህዲያኖች ይደሰታሉ፤ ሙስሊሞችን ጎዳናቸው፣ አሰቃየናቸው...እያሉ ደስታቸውን ይገልፃሉ...”

ምንጭ፦ [From his lesson on the night of the 2nd/Safar/1423H (15 April 2002), in his open meeting after Maghrib prayer, and also broadcast on Paltalk. This was translated from the live lecture at the time.]

የሸይኽ አቡ ዒያድ (ሀፊዘሁሏህ) እንግሊዝኛ ፅሁፍ በዚህ ሊንክ ያገኙታል።⤵️

https://abuiyaad.com/a/fawzan-....advice-palestinians-

📝 ዶክተር ሸይኽ አቡ ዒያድ (ሀፊዘሁሏህ)

📝 አማርኛ ትርጉም፡ አቡ ሀፍሳህ (ዐፈላሁ ዐንሁ)

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ابو امار Сhanged his profile picture
7 month
ترجمہ ممکن نہیں

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ترجمہ ممکن نہیں

ስለ ፈለስጢን ምን አዲስ ነገር አለ⁉️

========================

✍ የፈለስጢን (የጋዛ ሙስሊሞች) ጉዳይ በየቀኑ አሳዛኝነቱ ቀጥሏል። በየቀኑ የንጹሐን ህይዎት እየተቀጠፈ ነው፣ በርካታ መሠረት ልማቶች እየወደሙ ነው።

ዛሬ ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት እስካሁን 5087 ሙስሊሞች በጽዮናዊቷ ያላባራ የቦምብ ዝናብ ተገድለዋል፣ ከነዚህ መካከል 2055 የሚሆኑት ህፃናት ሲሆኑ 1119 የሚሆኑት ሴቶች ናቸው። 217ቱ አዛውንቶች ነበሩ። 1500 የሚሆኑት በፍርስራሽ ስር እንደጠፉ ናቸው፤ ከመካከላቸው 800 የሚሆኑት ህፃናት አሉ። እስካሁን ድረስ ጀናዛቸው እንኳ አልተገኘም። 15,273 የሚሆኑት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

አጠቃላይ የተፈናቀሉት 1 ሚሊዮን 400 ሺህ አካባቢ ሲሆኑ፤ 685 ሺህ የሚሆኑት ከሌሎች ቤተሰቦቻቸው ጋር ተፈናቅለዋል፣ 565 ሺህ የሚሆኑት ከተባበሩት መንግስታት የስደተኞችና የእርዳታ ሥራ ኤጀንሲ (UNRWA) ጋር ግንኙነት ወዳላቸው ት/ቤቶች ተፈናቅለዋል፣ 101 ሺህ የሚሆኑት በመስጂዶች፣ በቤተ ክርስቲናትና በህዝባዊ ቦታዎች ተጠልለዋል፣ 70 የሚሆኑት በ67 ት/ቤቶች ተፈናቅለው ይገኛሉ።

የተለያዩ ሃገራት መንግስታት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ቢጠይቁም፤ አሜሪካ በጸጥታው ም/ቤት ያላትን ድምፅን በድምፅ የመሻር መብት ተጠቅማ የፈለስጢናዊያን ጭፍጨፋ እንዲቀጥል አድርጋለች።

ምን ያክል የፈለስጢን ህፃናትና ሴቶች ተጨፍጭፈው ሲያልቁ እንደምትረካ አይታወቅም።

ሌላውም ዓለም በሰልፍ ድጋፉ እያሳዬ ቢሆንም ከዚያ የዘለለ ማድረግ አልቻለም።

በጋዛ አሁንም ቢሆን የውሃ፣ የመብራት፣ የምግብና የነዳጅ ማዕቀብ እንደተጣለ ነው። ባለፈ ብቻ 20 የሚሆኑ የጭነት መኪኖች ገብተው ነበር። ግን ለ2+ ሚሊዮን ህዝብ ምንም ማለት አይደለም። የጋዛን ሰብዓዊ ቀውስ ለመመከት በየቀኑ መቶ የጭነት መኪኖች መግባት አለባቸው።

አላህ በጥበቡ ከላይ ፈረጃውን አውርዶ ካሉበት በላእ ይገላግላቸው እንጂ እየተካሄደ ያለው ይፋዊ የዘር ማጥፋት ወንጀል ታሪክ የማይረሳው እጅግ አሰቃቂ እልቂት ነው።

ከዱዓእ ውጭ አቅም የለንምና ሁሌም ወንድሞቻችንን እናስታውሳቸው።

||

t.me/MuradTadesse

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ترجمہ ممکن نہیں

አይሁዶችን እና ደጋፊዎቻቸውን ከምንዋጋበት መንገድ አንዱ Facebookን ባለመጠቀም ነው። ወገን ይህን ፕላትፎርም በደምብ ማስተዋወቅ ይኖርብናል።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
ابو امار Сhanged his profile picture
7 month
ترجمہ ممکن نہیں

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group