UMMA TOKEN INVESTOR

mehbub awel shared a
Translation is not possible.

"ሡልጣን ሆይ! ሰላትህን በጀመዓ አትሰግድምና ምስክርነትህ ተቀባይነት የለውም..."

╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍╍

  አሁን የምንገኝው በሙስሊሞች ዋና ከተማ ቡርሳ ነው። በታላቁ መሪ በሱልጣን ባየዚድ ቢን ሙራድ ዘመነ መንግስት!

ቡልጋሪያን፣ ቡርሳንና አልባኒያን ድል አድርጎ የከፈተው የክፍለ ዘመኑ ኃያል መሪ ቃዲ ሸምሰ ድ-ዲን ዘንድ በአንድ ጉዳይ ላይ የምስክርነት ቃሉን ሊሰጥ ከፊታቸው ተጥዷል። እንደማንኛውም ምስክር እጆቹን አጣምሮ ከችሎቱ ፊት ቆሟል።

ዳኛው ዓይኑን አማትሮ ሡልጣኑን እየተመለከተ ከእግር እስከ ራሱ በትኩረት ቃኘ

  "ሡልጣን ሆይ!" አለ ዓይን ዓይኑን እያየ። ታዳሚው በዝምታ ተውጦ የዳኛውን ንግግር ለመስማት ጆሮውን ቀሰረ "ሡልጣን ሆይ! ሰላትህን በጀመዓ አትሰግድምና ምስክርነትህ ተቀባይነት የለውም። ሰላቱን በጀመዓ የማይሰግድ በምስክርነት ቃሉ ሊዋሽ ይችላልና አይታመንም ተብሎ ስለሚገመት ያንተን ምስክር አንቀበልህም ሂድ" አሉት።

  በፍርድ ቤቱ የተገኙ የዳኛውን ንግግር የሰሙ ታዳሚያን በድንጋጤ አይናቸውን ለጠጡ። ሡልጣን ባይዚድን በሰዎች ፊት ዝቅ ያደረገውን ዳኛ መጨረሻ ለማየት፣ ለዳኛው እየፈሩ ባሉበት ቦታ ተቀመጡ።

ችሎቱ ፀጥ ረጭ አለ። ሡልጣን ባየዚድ አንዲትም ቃል ከአፉ ሳያወጣ አንገቱን ከመሬቱ እንደደፋ በእርጋታ እየተራመደ ፍርድ ቤቱን ለቆ ወጣ። በዚያው ቀን ከቤተ መንግስቱ አጠገብ መስጂድ እንዲሰራ አዘዘ። ተገንብቶ እንዳለቀ ሰላቱን ሳያዛንፍ አምስቱንም አውቃት በጀመዓ የሚሰግድ የአላህ ባርያ ሆነ።

ይህ ፍትህ የንግስና መሰረት፣ የኢስላም ዳኞችና ዑለማኦች ከአላህ በቀር ማንንም በማይፈሩበት ወቅት የተገኘ አስገራሚ ታሪክ ነው::

Send as a message
Share on my page
Share in the group
mehbub awel shared a
Translation is not possible.

ዓጃኢብ የሆነ ታሪክ

November 26, 2022

አጃዒብ የሆነ ታሪክ ላካፍላችሁ‼

ዲኔ ላይ ደህና ነኝ፡፡ መልክ አለኝ ባይባልም አልከፋም፡፡ በባህሪዬ ጥሩ ነኝ ብዬ አስባለሁ፡፡ ከቤተሰብ ሳልርቅ ነው ያደግኩት፡፡ የልጅነት ጊዜዬ አልፎ ወጣትነት መጣ፡፡ እንደማንኛዋም ሴት ትዳር አሰብኩ፡፡ ግና በማላውቀው ምክንያት ድርሻዬ ዘገየብኝ፡፡ ለጋብቻ የሚጠይቀኝ ጠፋ፡፡ ከኔ በኋላ የተወለዱ የቤተሰብም፣ የዘመድም፣ የሰፈርም ልጆች አንድ በአንድ አገቡ፡፡ ወለዱ፡፡ ልጆቻቸውም አደጉ፡፡ ሳላስበው 34 ዓመት ሆነኝ፡፡ እድሜዬን ሳስታውሰው ደነገጥኩ፡፡ ብቻዬን ቆሜ የቀረሁ እስኪመስለኝ ድረስ ተሰማኝ፡፡

⊙ የሆነ ጊዜ ከቅርብ ዘመድ የሆነ አንድ ወጣት ለጋብቻ ጠየቀኝ፡፡ ፈቃደኝነቴን ገለፅኩ፡፡ ሁለት ዓመት ይበልጠኛል፡፡ ዲኑም ፀባዩም ቆንጆ ነው፡፡ ደስ አለኝ፡፡ ከሀሳቤ የተገላገልኩ መሰለኝ፡፡ ቤተሰብም ደስ አለው፡፡

≅ ኒካሕ ለማሰር ተዘጋጀን፡፡ አንዳንድ ጉዳዮችን ለመጨረስ ብሎ መታወቂያዬን ይዞ ሄደ፡፡ 

.

ከሁለት ቀን በኋላ ስልክ ተደወለልኝ፡፡ እናቱ ነበረች፡፡ እንደምትፈልገኝ ነገረችኝ፡፡ ምን ይሆን ብዬ እየበረርኩ ሄደኩኝ፡፡ ቤታቸው ገባሁ፡፡ ጥቂት ካወራን በኋላ መታወቂያዬን እያሳየችኝ እዚህ ላይ የተጠቀሰው የትውልድ ቀኔ ትክክል ስለመሆኑ ጠየቀችኝ፡፡ “አዎን! ትክክል ነው” አልኳት፡፡ 

“እንግዲያውስ አንች አርባ ተጠግተሻል መውለድ አትችይም” አለችኝ፡፡ “34 ዓመቴኮ ነው እንዴት አልችልም” አልኳት፡፡ 

“አይ … አንች ሰላሳ አልፎሻል እኔ ደግሞ ልጅ አይደለም ገና የልጅ ልጅ ማየት እፈልጋለሁ” አለች፡፡ ጋብቻው እንዲሰረዝ ሞገተች፡፡ ልጇንም አሳመነች። ለቤተሰቤ ምን እንደምላቸው እያሰላሰልኩ ተስፋ ቆርጬ ወደቤቴ ተመለስኩ፡፡

≅ ቀናት አለፉ፡፡ ድፍን ስድስት ወራትን በሐዘን አሳለፍኩ፡፡ ረጃጅም ቀንና ሌሊቶችን ስብሰለሰል ከረምኩ፡፡ በር በሩን ባይ እኔን ብሎ የሚመጣ ለኔ የተፃፈ ባል ጠፋ፡፡ ብቸኝነት፣ ባይተዋርነት፣ አጥንት ድረስ ዘልቆ ተሰማኝ፡፡ 

አባቴ ሁኔታዬን ይከታተላል፡፡ ስለኔ አብዝቶ ተጨነቀ፡፡ በመጨረሻም ከወንድሜ ጋር ለዑምራ እንድሄድ መከረኝ፡፡ “ሂጂና በተከበረው የአላህ ቤት አጠገብ ብሶትሽን ተናገሪ፤ የውስጥሽን የውስጥ አዋቂ ለሆነ ጌታ ተንፍሺ” አለኝ፡፡ 

ዑምራ ሄድኩኝ፡፡ የአላህ ቤት ከዕባ ፊት ቁጭ ብዬ ረጅም ዱዓ አደረግኩ፡፡ ለርሱ የውስጥ ስሜቴን ሁሉ አንሾካሸኩ፡፡ አለቀስኩ፤ ፈረጄን ያቀርብልኝ ዘንድ ተማፀንኩት፡፡

≅ የሆነ ቀን ሱንና ከሰገድኩ በኋላ ጥቂት ቁጭ አልኩ፡፡ ከኋላዬ አንዲት ሴት ባማረ ድምጽ ቁርኣንን ታነባለች። “የአላህ ችሮታ ብዙ ነው።” የሚል ትርጉም ያለውን የቁርኣን አንቀጽ ስታነብ ቀልቤ በተለየ መልኩ ወደዚያ ተሳበ፡፡ በቁርኣን ውስጥ የዚህ ዓይነት አንቀፅ ስለመኖሩ ገረመኝ፡፡ አላህ በችሮታው ያስበኝ ዘንድ ተማፀንኩት፡፡ 

ሴትዮዋ አየችኝ፡፡ ምን እንደሆንኩ ጠየቀችኝ፡፡ ሁኔታዬን ነገርኳት፡፡ “አብሽሪ” አለችኝ “አብሽሪ አላህም ያሰብሽውን ይሰጥሻል፤ ኢን ሻኣላህ ደስም ይልሻል” አለችኝ፡፡

≅ ዑምራውን አጠናቅቄ ተመለስኩ፡፡ ድንገት የረጅም ጊዜ ጓደኛዬንና ባሏን በአይሮፕላን ማረፊያው አገኘኋቸው፡፡ የባሏን ጓደኛ ለመቀበል እየጠበቁ ነበር፡፡ ሰላምታ አቅርቤላቸው ትንሽ እንዳወጋን ጓደኛቸው ደረሰና ተሰነባበትን፡፡ ወዲያው አባቴ ደርሶ ተቀበለኝ፡፡

ጥቂት ቀናት አለፉ፡፡ አሁን ከበፊቱ በተሻለ ልቤ በመጠኑ ሰክኗል፡፡ ዱዓዬን አላቋረጥኩም፡፡

የሆነ ቀን ያች ጓደኛዬ ደወለችልኝ ያን ቀን ያየኝ የባሏ ጓደኛ ለትዳር እንዳሰበኝ ነገረችኝ፡፡ በአንድ ቀን እይታ እንዴት ሊሆን ይችላል ብዬ ተገረምኩ፡፡ ግና ለአላህ ምን ይሳነዋል!!፡፡ 

በእውነቱ የማይታሰብ ነገር ሆነብኝ፤ ማመን አቃተኝ፡፡ እሱ ግን የምሩን ነበር፡፡ ስለኔ ሁሉን ነገር ከጓደኛዬ ከሰማ በኋላ አላንገራገረም፡፡ ወደ ቤተሰቦቼ ሽማግሌ ላከ፡፡ ደስ አለኝ፡፡ ተስፋዬ ለመለመ፡፡ ወዜ ተመለሰ፡፡ ስሜቴ ታደሰ፡፡

በመጨረሻም አገባሁ። ጥሩ አፍቃሪ፣ መልካምና ደጋፊ፣ አዛኝና አሳቢ ባል … አላህ ሰጠኝ። ለኔም ለወላጆቹም ጥሩ ሰው ነበር፡፡

ካገባሁ ቀናት ሄዱ፣ ሁለትና ሶስት ወራት ተተኩ፡፡ ሌላ ሀሳብ አስጨነቀኝ፡፡ የእርግዝና ምልክት ናፈቀኝ፡፡ ግና እስካሁን ምንም አላስተዋልኩም፡፡ ሲበዛ አሳሰበኝ፡፡ እንቅልፍ አጣሁ፡፡

መመርመር እንደምፈልግ ለባሌ ነገርኩት፡፡ ወደ ሀኪም ቤት ሄድን፡፡ ጥቂት ቆይተን ለውጤቱ ተጠራን፡፡ ልቤ መምታቱን ጨመረ፡፡ ገና እንደገባሁ “መዳም መብሩክ!” አለችኝ ሀኪሟ፡፡

አርግዤ ነበር፡፡ ሱብሐነላህ! ለዚህ ብስራት ነበር እንዴ አላህ እዚህ ድረስ ያመጣኝ አልኩ፡፡

የእርግዝና ጊዜዬ ሰላማዊ ነበር፡፡ ግና የእድሜዬ መግፋት መጠነኛ ተጽእኖ ነበረው፡፡ ሆዴ እያደገ ሲመጣ ሰውነቴ ከበደኝ፡፡ እንደምንም የድካሙ ወራት አለፈ፡፡ የምጡ ቀን ደረሰ፡፡ በቀዶ ጥገና ነበር የወለድኩት፡፡ ከተሰጠኝ ሰመመን ስነቃ ቤተሰቦቼና ባለቤቴ ዙርያዬ ተሰብስበዋል፡፡ ይስቃሉ፣ ይጫወታሉ፡፡

“ምን ወለድኩ?” አልኳቸው ያለሁበትን ሁኔታ እያስታወስኩ፡፡

የተመካከሩ ነበር የሚመስለው፡፡ አንድ ላይ ሆነው ነበር ሰርፕራይዝ ያደረጉኝ “ወንድ እና ሴት!” አሉኝ፡፡ መንታ!!፡፡ የኔን መንቃት ሲጠብቅ የነበረው ባሌ በደስታ ተፍነከነከ፡፡ እኔንም ሀሴት የምሆነውን አሳጣኝ፡፡ ብችል ተነስቼ በዘለልኩ፡፡ ቁስሌ ገና እርጥብ ነው፡፡ ሱጁድም ራቀኝ፡፡ በተኛሁበት እንባዬ በሁለቱም ጉንጮቼ በኩል ዝም ብሎ ሲፈስ ይታወቀኛል፡፡ በትኩስ እንባ ፊቴ ታጠበ፡፡ ምስጋናዬን ያወጣሁበት ቃል እሱ ነበር፡፡ 

  የሚለውን የቁርኣን አንቀጽ አስታወስኩ፡፡ ስለ አላህ አሰብኩና በሀሳብ ርቄ ሄድኩ፡፡ የሱ ሥራ አብዝቶ ገረመኝ፡፡ እኛ ተስፋ እንቆርጣለን እንጂ እሱ ያዘጋጀልን ነገር አለ፡፡ እኛው ሁለት ልብ ሆነን ተቸገርን እንጂ በርግጠኝነት በአንድ ሆነን ልብ ይሰጠናል ብለን ብንለምነው ይሰጠናል፡፡ 

እኛው እንቸኩላለን እንጂ እሱ ለሁሉም ነገር መላና መፍትሄ አለው፤ ለሁሉም ነገር ምክንያትና ጊዜ አለው፡፡ ለአላህ ውሳኔ መታገስና ፈረጃውን መጠበቅ ትልቅ ዒባዳ ነው፡፡ 

እንኳን እኛ ነቢዩ ዘከርያም በልጅ እጦት ተፈትነዋል፡፡ “ጌታዬ ሆይ ብቻዬን አትተወኝ!!” ሲሉ ነበር ዱዓ ያደረጉት፡፡ 

ኢን ሻኣላህ ፈጣሪሽ ያሰብሽውን ይሰጥሻል፤ አንቺም አንድ ቀን ደስ ይልሻል፡፡

📚 “ቂሶሱን ሚነል ዋቂዕ” ከተሰኘ መጽሐፍ የተወሰደ፡፡ 

☑️ ተስፋ የቆረጡ ተስፋቸው ይለመልም ዘንድ እባክዎ ሼር ያድርጉ።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
mehbub awel shared a
Translation is not possible.

ሮም በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፊት ለፊት የተሰቀለውን የወራሪዋን ባንዲራ እንዲህ በጥሶ ጥሎታል አንድ ጀግና ።

11 views
1 view
Send as a message
Share on my page
Share in the group
mehbub awel shared a
Translation is not possible.

Sheikh Dr. Salih Fewzan Al-Fewzan

ሸይኽ ዶ/ር ሷሊሕ ፈውዛን አላህ ይጠብቃቸውና የአይሁዶች በፈለስጢን አካባቢ መሰባሰብ የቂያም ቀን አንዱ ምልክት ነው ይላሉ።

አላህ እነዚህን ካፊሮች ከነ አጋሮቻቸው ከምድረ ገፅ ያጥፋቸው።

5 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
mehbub awel shared a
Translation is not possible.

ገደልነው ሲሉ ህያው ሞተ ሲሉም እየዳነ ዛሬም ድረስ በህይወት ያለ ተንቀሳቃሹ ሰማዕት። ተራማጁ ሸሂድ። የማይነጥፍ የወንድነት ባህር! የፍልስጤማዊያን ኩራት! የዘመኑ አብሪ ኮከብ! የጦር ሊቅ! የኬምስትሪ ደቂቅ። ፍፁም ትሁት አስተዋይና ለስላሳ ቁጥብነትን የተላበሰ ጀግና። መልካም ልብ፣ ደግ ማንነትን የታደለ ወንድ።

ጌታዬ ሆይ!

ብዕሬን እንደ ኻሊድ ኢብኑልወሊድ ሠይፍ የሰላ አድርግልኝ

Mahi Mahisho

አሰልጥኖ የሚያሰማራቸው ወታደሮች፣ አብላልቶ የሚተኩሳቸው ሮኬቶች የወራሪዋን ራዳር ጥሰው ሰማዩን እየሰነጣጠቁ ጠላትን ማሸበር ከጀመሩ እነሆ 23 አመታት ተቆጠሩ። የእስራኤል የስለላ ተቋም ሮኬቶቹ ሲሰሩ እንኳ አያቅም። ተምዘግዛጊ ሮኬቶችን እንደታጠቁ ያወቁት በ2001 አየሩን ሰንጥቀው ከተማቸው ውስጥ ሲያርፉ ነው።

ከእነዚህ ሮኬቶች ጀርባ አንድ የኬምስትሪ ምሩቅ አለ። ለዚህ ብሎ የተማረ። ብረትን ከፖታሺየም ናይትሬትና የወዳደቁ እቃዎችን ከማዳበሪያ ጋር ቀምሞ በቆርቆሮ ሲሊንደር አብላልቶ ሮኬቶቹን የሚያዘጋጅ ታንክን በዲንጋይ የገጠመ ፍፁም ለአላህ ያደረ ዓቢድ። ባመሸበት ቦታ የማያድር ባረፈደበት መንደር የማይውል። በእናቱ ቀብር ላይ እንኳ ያልተገኘ ፍፁም ጥንቁቅ።

ሞሳዶች አስማተኛው ሰይጣን ይሉታል። ከጠቅላይ ሚኒስቴር ሽሞን ፔሬዝ እስከ ቢኒያሚን ኔታንያሆ በሰማይ በምድር የሚፈለግ ረብጣ ዶላር መድበው ደህንነቶቻቸውን አሰማርተው የዛሬሀያ ስምንት ዓመት እንዲገደል ትዕዛዝ ያስተላለፉበት የጋዛው ኮማንደር።

በማለዳ ተነስተው ከስክስ ጫማቸውን አጥልቀው ተራራውን ሮጠው ያላገኙት፣ የጥይት አሩር እየተኮሱ ቦንብ ከአውሮፕላን ቢያዘንቡ ፍፁም ሊገሉት ያልቻሉት የፍልስጤማዊያን ቁልፍ ሰው።

በእግሮቹ የሚራመድ ሸሂድ ቢሉት አትገረሙ። በእርግጥም ልክ ናቸው። ብዙ ጊዜ ከሞት ድኗል። የሞሳድ ደህንነቶች ከጓደኞቹ በአንዱ የእጅ ስልክ ላይ የተጠመደውን ፈንጂ ተኩሰው ሲገድሏቸው፣ መኪናው በድሮን ተደብድባ ሁለት ጠባቂዎቹና አንድ ረዳቱ ሲገደሉ እርሱ ተርፏል። የተማረበትን ዩንቨርስቲ ሊጎበኝ በሄደበት F1 የጦር ጀቶች ዩንቨርስቲውን ዶግ አመድ ሲያደርጉት በህይወት ድኗል። የእስራኤል አየር ኃይል ጋዛ በሚገኘው መኖርያ ቤቱ ላይ ድብደባ ፈፅሞ ሚስቱና ሁለት እንቦቃቅላ ልጆቹን ገድሎ የሙጃሂዶቹን አከርካሪ አጥንት ሰበርነው አዎ አስወገድነው ገደልነው ብለው በደስታ ውስኪ ሲራጩ ነፍሱ አዛኙንና ኃያሉን አላህ ለመገናኘት አልተፈቀደላትም ነበርና አለሁ ብሎ ብቅ ብሏል።

ሙሐመድ ዲያብ ኢብራሒም ይሰኛል። ፍልስጤማዊያን ደይፍ ይሉታል እንግዳ እንደማለት ነው። በእርግጥም እርሱ በወራሪዋ ደህንነቶች ታድኖ ሊገደል፣ ተጠፍሮም ሊያዝ ያልቻለ አሳዳጆቹ እጅ ሳይገባ ሀያ ስምንት አመታቶችን ያስቆጠረ ሁሌም እንግዳ ሰው ነው።

የሙስሊሞች ለቅሶ የእናቶች እሪታ፣ የልጆች ስቅስቅታ በጆሮው ሲንቆረቆር ለበይክ ብሎ በለጋ ዕድሜው የተነሳ ወጣትነቱን በትግል ያሳለፈ ትንታግ ነው። ወንድሞቹ ሲሞሻለቁ፣ እህቶቹ በድምፅ አልባ መሳሪያ ሲወቁ ትከሻም ልቡም ለመሸከም አልፈቀዱለትም፡፡ ድንቡሽቡሽ ፊት ያላቸው እንቦቃቅላ ልጆቹን ትቶ፣ የእናቱን የእጅ ደበሳ ርቆ በጂሃድ ሜዳ ላይ ተሰየመ፡፡

የብሩህ አዕምሮ ባለቤት የመሐፈዝ አቅሙ ከፍተኛ የሰማውን ቀብ፣ ያየውን ልቅም አድርጎ የሚይዝ ፈጣን ነው። በየትኛውም ቴሌቪዥን ታይቶ አይታወቅም። ምንም አይነት ቴክኖሎጂ የማይጠቀም ባለ ዊልቸሩ የጦር መሪ።

አባቱ ልብስ እየሰፉ በአነስተኛ የዶሮ እርባታ እንቁላል እየሸጡ ያሳደጉት ልጅ ዛሬ ስሙን እንጂ ማንነቱን ለማወቅ ከብዷል። አላህ ረጅም ሐያት ከሙሉ አፊያ ጋር!

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group