UMMA TOKEN INVESTOR

معلومات عني

የፈለከውን ያክል ኑር ሟች ነህ የፈለግከውን ስራ የስራህን ዋጋ ታገኛለህ የፈለግከውን ውደድ ከእሱ ትለያያለህ»

Fuad Abatemam Abagisa قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

በቁርኣን አንዱ በሌላው ድምፅን ከፍ ማድረግ

~

ሶላት ስንሰግድ አጠገባችን ሌላ ሰጋጅ ካለ እንዳንወሰውስ ድምፃችንን ዝቅ ልናደርግ ይገባል። ልክ እንዲሁ መስጂድ ውስጥ - ለምሳሌ ጁሙዐ ቀን ሊሆን ይችላል - ቁርኣን ስንቀራ ሌሎችን በሚረብሽ መጠን ድምፃችንከፍ ያለ መሆን የለበትም። ነብያችን ﷺ በአንድ ወቅት ኢዕቲካፍ ላይ ነበሩ። ሰዎች ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እየቀሩ ሰሟቸው። መጋረጃቸውን ገለጥ አድርገው እንዲህ አሉ፦

أَلَا إِنَّ كُلَّكُمْ مُنَاجٍ رَبَّهُ، فَلَا يُؤْذِيَنَّ بَعْضُكُمْ بَعْضًا، وَلَا يَرْفَعْ بَعْضُكُمْ عَلَى بَعْضٍ فِي الْقِرَاءَةِ ، أَوْ قَالَ: فِي الصَّلَاةِ

"ንቁ! እያንዳንዳችሁ ከጌታው ጋር ነው እየተንሾካሾከ ያለው። ስለዚህ አንዳችሁ ሌላውን አያስቸግር። ከፊላችሁ በከፊሉ ላይ በቂራኣ - ወይም በሶላት - አይጩህ። [አቡ ዳውድ፡ 1332]

በሌላ ዘገባ ላይ ደግሞ እንዲህ ብለዋል፦

أما إن أحدكم إذا قام في الصلاة، فإنه يناجي ربه، فليعلم أحدكم ما يناجي ربه، ولا يجهر بعضكم على بعض بالقراءة في الصلاة

"አንዳችሁ ለሶላት ሲቆም ከጌታው ጋር ነው የሚንሾካሾከው። ስለሆነም ከጌታው ጋር የሚንሾካሾክበትን ይወቅ። ከፊላችሁ በከፊሉ ላይ በሶላት ውስጥ በቁርኣን አይጩህ።" [ሙስነድ አሕመድ፡ 11896]

ስለዚህ ሌሎች ሰጋጆች ባሉበት ጀማዐ ሶላት ላይ ያለፈንን ስንመልስ፣ ወይም ካጠገባችን ሌሎች ቁርኣን የሚቀሩ ሲኖሩ ድምፃችንን ዝቅ በማድረግ ልንቀራ ይገባል። ጁሙዐን እየጠበቁ በድምፅ ማጉያ ቁርኣንን ከመስጂድ መክፈትም እንዲሁ ተገቢ አይደለም።

ልክ እንዲሁ በየቤታችን ሆነን ሶላት የሚሰግድ ባለበት እየተንጫጩ ማውራትም የተለመደ ነው። ይህም መታረም ያለበት ነው። በቁርኣን አንዱ በሌላው ላይ እንዲጮህ ካልተፈቀደ በሌላ ወሬ፣ ያውም ሶላት ላይ ያለን አካል መወስወስ ግልፅ የሆነ ጥፋት ነው። ለሶላት ክብር ሊኖረን ይገባል። ልጆቻችንንም እንዲሁ አደብ ማስተማር አለብን።

Ibnu Munewor

=

* የቴሌግራም ቻናል

https://t.me/IbnuMunewor

* የዋትሳፕ ቻናል፦

https://whatsapp.com/channel/0....029VaA3X1e5kg7BlsJbo

* ፌስቡክ

https://www.facebook.com/Ibnu.....Munewor?mibextid=ZbW

image
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
لا يمكن الترجمة

ስራህን ከሺርክ ጠብቅ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إنَّ أخوَفَ ما أخافُ عليكم الشِّركُ الأصغرُ، قالوا: وما الشِّركُ الأصغرُ؟ قال الرِّياءُ،﴾

“በእናንተ ላይ የምፈራላችሁ ትንሹን ሺርክ ነው። ትንሹ ሺርክ የሚባለው የቱ ነው? ሲባሉ ለ‘እዩልኝ’ የሚሰራ ስራ ነው በማለት መለሱ።”

📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 951

ጆይን፦ https://t.me/BuhariMuslimAmharic

image
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
لا يمكن الترجمة

አንተ አማኝ ነህ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إذا سَرَّتْكَ حَسَنَتُكَ، وساءَتْكَ سَيِّئَتُكَ، فَأنتَ مُؤْمِنٌ﴾

“መልካም ስራህ ካስደሰተህ፣ መጥፎ ስራህ ካስከፋህ አንተ አማኝ ነህ።”

📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 551

﴿جاء رجلٌ إلى حذيفة، فقال: يا أبا عَبْد

الله، إني أخشى أن أكون منافقًا، قال: تُصَلِّي

إذا خلَوتَ، وتستغفرُ إذا أذنبـت؟ قال: نعم،

قال: اذهب، فما جعلك الله منافقا﴾

“አንድ ሰው ወደ ሁዘይፋ መጣና እንዲህ አላቸው፦ አንቱ የአብደላህ አባት ሆይ! እኔ ሙናፊቅ እንዳልሆን እፈራለሁ ሲላቸው። አሉት፦ ብቻህን ስትሆን ሶላት ትሰግዳለህ ወንጀልስ ሰርተህ ምህረት ትጠይቃለህ? አዎ! አለ። አሉት፦ ሂድ በቃ አላህ ሙናፊቅ አላደረገህም።”

📚 ኢብኑ አካሲር ታሪኹ ዲመሽቅ ላይ ዘግበውታል: 1/251

ጆይን፦ https://t.me/BuhariMuslimAmharic

image
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
لا يمكن الترجمة

አንተ አማኝ ነህ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿إذا سَرَّتْكَ حَسَنَتُكَ، وساءَتْكَ سَيِّئَتُكَ، فَأنتَ مُؤْمِنٌ﴾

“መልካም ስራህ ካስደሰተህ፣ መጥፎ ስራህ ካስከፋህ አንተ አማኝ ነህ።”

📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 551

﴿جاء رجلٌ إلى حذيفة، فقال: يا أبا عَبْد

الله، إني أخشى أن أكون منافقًا، قال: تُصَلِّي

إذا خلَوتَ، وتستغفرُ إذا أذنبـت؟ قال: نعم،

قال: اذهب، فما جعلك الله منافقا﴾

“አንድ ሰው ወደ ሁዘይፋ መጣና እንዲህ አላቸው፦ አንቱ የአብደላህ አባት ሆይ! እኔ ሙናፊቅ እንዳልሆን እፈራለሁ ሲላቸው። አሉት፦ ብቻህን ስትሆን ሶላት ትሰግዳለህ ወንጀልስ ሰርተህ ምህረት ትጠይቃለህ? አዎ! አለ። አሉት፦ ሂድ በቃ አላህ ሙናፊቅ አላደረገህም።”

📚 ኢብኑ አካሲር ታሪኹ ዲመሽቅ ላይ ዘግበውታል: 1/251

ጆይን፦ https://t.me/BuhariMuslimAmharic

Telegram: Contact @BuhariMuslimAmharic

Telegram: Contact @BuhariMuslimAmharic

በቡኻሪና ሙስሊም ሳይገደብ በሌሎች የሐዲስ ሊቃውንቶች የተዘገቡ ነቢያዊ ሀዲሶችም ይቀርቡበታል።
أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة
Fuad Abatemam Abagisa قام بمشاركة
لا يمكن الترجمة

ሚዛን!

~

የትኛውንም ብሄር በሆኑ አባላቱ ጥፋት በጅምላ አትወርፍ። እራስህ ላይ ቢሆን የማትፈልገውን ነገር ሌሎች ላይ አትለጥፍ። በራስህ ሞኞች ሰበብ ዘርህ እንዲሰደብ እንደማትፈልገው ድፍን ብሄርን ባልዋለበት አትፈርጅ፤ በሌለበት አትክሰስ። በወቅታዊ የፖለቲካ ግለት ተነሳስተህ በጅምላ ሰዎችን አታጥቃ። መጠቃታቸውንም አትደግፍ። ባንተ ብሄር ላይ ቢቀለድ የምትከፋ ሆነህ ሳለ በሌሎች ላይ አትቀልድ፣ አታሰራጭ።

የሆኑ ነውረኞች ዘርህን ስለ ሰደቡ የነሱን ዘር አትሳደብ። ከረከሱ ጋር ከምትረክስ በማስተዋልህ ከፍ በልና ከነሱ ተሽለህ ተገኝ። ስትወድም፣ ስትጠላም፣ ሲከፋህም፣ ሲደላህም፣ በራስህም ይሁን በሌሎች ብሄር ጉዳይ ላይ ሚዛን አትሳት፣ ፍትህ አትልቀቅ። والانصاف خير الأوصاف

በየትኛውም ጉዳይ ላይ በማንኛውም ሁኔታ ሃይማኖትህን አስቀድም። ኢስላም የማይቀበለውን ነገር ለመጋፈጥ የብሄርና የፖለቲካ አሰላለፍ አትመልከት። ሌሎች ሲፈፅሙት ጥፋት የሆነ ተግባር ያንተ ብሄር ሰዎች ሲፈፅሙት ፅድቅ አይሆንም። ሌላ ብሄር ውስጥ ያሉ ሰዎች የፈፀሙትን ጥፋት እያብጠለጠልክ ያንተ ብሄር ሰዎች ሲፈፅሙት ለመከላከል አትነሳ። እፍረት ይኑርህ እንጂ። ህሊናህን አክብር እንጂ። ደግሞም እወቅ! ሌሎች ላይ የምታየውን ጥፋት ለመኮነን ዘራቸውን አትነካካ።

ደግሞም ንቃ! ለየትኛውም የፖለቲካ ኃይል ደጋፊ ብትሆን የእምነትህን እሴቶች እስከ መዋጋት፣ ወይም እምነትህን ለሚያራክሱ አካላት እስከመወገን ድረስ አትውረድ። "ሞኝ አህያ ጅብ ይሸኛል" ይላል ብሂሉ። ለሞኝነትህ ለከት አብጅለት።

የፖለቲካ ጥላቻና ውግንና አቅልህን አያስትህ። የ'ውር ድንብር ጥላቻና ውዴታ ውስጥ አይክተትህ። ኋላ ትጎዳለህ። ድንገት ያስተዋልክ እለት ታፍራለህ። ምናልባት ካስተዋልክ!

Ibnu Munewor

=

* ቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor

* ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/Ibnu.....Munewor?mibextid=ZbW

* ዋትሳፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0....029VaA3X1e5kg7BlsJbo

* ኡማ ላይፍ፦ https://ummalife.com/IbnuMunewor

أرسل كرسالة
شارك على صفحتي
شارك في المجموعة