Zebiba Mohammed Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Табасаранан алхьа кха дац.

ለእስራኤል ፖሊስ መለዮ ያቀርብ የነበረው ኩባንያ ውሉን አቋረጠ

የህንዱ ማርያን የጨርቃ ጨርቅ ኩባንያ ለእስራኤል ፖሊስ መለዮ በማቅረብ ላይ ነበር

አል-ዐይን

 2023/10/21 12:59 GMT

ኩባንያው ውሉን ያቆመው የእስራኤል ፖሊስ የስነ ምግባር ጥሰት ፈጽሟል በሚል ነው

ለእስራኤል ፖሊስ ዩኒፎርም ያቀርብ የነበረው ኩባንያ ውሉን አቋረጠ።

የእስራኤል-ሀማስ/ፍልስጤም ጦርነት ከተጀመረ ሁለት ሳምንት ያለፈው ሲሆን እስካሁን ከስድስት ሺህ በላይ ዜጎች ከሁለቱም ወገን ተገድለዋል።

የዓለምን ትኩረት የሳበው ይህ ጦርነት ከብዙ ጉዳዮች ጋር የተገናኘ ሲሆን ለእስራኤል ፖሊስ አባላት መለዮ ሲያቀርብ የነበረው ኩባንያ ውሌን አቋርጫለሁ ብሏል።

የህንዱ ማርያን ጨርቃ ጨርቅ ኩባንያ ለእስራኤል ፖሊስ መለዮ በማቅረብ ላይ የነበረ ሲሆን ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ውሉን ማቋረጡን አስታውቋል።

ኩባንያው ውሉን ያቋረጠው የእስራኤል ፖሊስ የሙያ ስነ ምግባሩን ጠብቆ እየሰራ አይደለም በሚል እንደሆነ ኢንዲያን ታየምስ ዘግቧል።

የኩባንያው ስራ አስኪያጅ ቶማስ አሊካል እንዳሉት የእስራኤል ጦር በተለይም በጋዛ በሚገኘው አል አህሊ ሆስፒታል ላይ የፈጸመው ጥቃት ውሉን እንዲያቆም ዋነኛው ምክንያት ነው።

በመሆኑም እስራኤል ከፍልስጥኤማውያን ጋር ሰላም እስኪያወርዱ ድረስም አዲስ ትዕዛዝ ከእስራኤል ፖሊስ እንደማይቀበል ኩባንያው ገልጿል።

ይሁንና ከዚህ በፊት የእስራኤል ፖሊስ ከኩባንያው ጋር የገባቸውን ስምምነቶች እንደሚያከብር ተጠቅሷል።

የእስራኤል ጦር ጥቃት ሀማስን ኢላማ ያደረገ ነው ቢባልም ንጹሀን ዜጎች የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል ተብሏል።

አሜሪካ በቀጥታ ለእስራኤል የጦር መሳሪያ እና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ ላይ ስትሆን የእስራኤልን ድርጊት በርካቶች ራስን ከመከላከል ያለፈ እንደሆነ እየገለጹ ይገኛሉ።

ጦርነቱ በሚቆምበት ሁኔታ እና ለፍልስጤማዊያን ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረግ ያለመ ውይይት በግብፅ አስተናግጅነት የበርካታ ሀገራት መሪዎች ውይይት በማድረግ ላይ ናቸው።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Табасаранан алхьа кха дац.

በለንደን በተካሄደ የፍልስጤም ድጋፍ ሰልፍ 100ሺ ሰዎች መሳተፋቸው ተገለጸ

የአረብ ሀገራት እስራኤል ተኩስ እንድታቆም ያደረጉት ጥረትም አልተሳካም

ቀዳሚ ገፅ

ዜና

አስተያየት

ፖለቲካ

ኢኮኖሚ

ማህበራዊ

ልዩልዩ

ስፖርት

የመረጃ ሳጥን

ተመልከት

ፖለቲካ

በለንደን በተካሄደ የፍልስጤም ድጋፍ ሰልፍ 100ሺ ሰዎች መሳተፋቸው ተገለጸ

የአረብ ሀገራት እስራኤል ተኩስ እንድታቆም ያደረጉት ጥረትም አልተሳካም

አል-ዐይን

 2023/10/22 8:19 GMT

ሰልፈኞቹ በዳውኒንግ ጎዳና ከመሰባሰባቸው በፊት "ነጻ ፍልስጤም" የሚል መፈክር ከፍ አድርገው አሰምተዋል

በእንግሊዝ ለንደን ከተማ በተካሄድ የፍልስጤም የድጋፍ ሰልፍ ላይ ወደ 100ሺ የሚጠጉ ሰልፈኞች ተሳትፈዋል።l

ሰልፈኞቹ እስራኤል ሀማስ የሰነዘረባትን ጥቃት ተከትሎ የምታደርገውን ጥቃት እንድታቆም መጠየቃቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ሰልፈኞቹ በእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ መኖሪያ በሆነው በዳውኒንግ ጎዳና ከመሰባሰባቸው በፊት "ነጻ ፍልስጤም" የሚል መፈክር ከፍ አድርገው አሰምተዋል።

'በፍልስጤም አጋርነት ዘመቻ' በተጠራው ሰልፍ 100ሺ ሰዎች መሳተፋቸውን ፖሊስ ግምቱን አስቀምጧል።

 በጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ በተለይም በሙስሊም ሀገራት ቁጣ ተቀስቅሷል፣ የአጋርነት ሰልፎችም ተካሂደዋል።

የፍልስጤሙ ታጣቂ ቡድን ሀማስ በጥብቅ የሚጠበቀውን የእስራኤል ድንበር ጥሶ በመግባት ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ እስራኤል እየወሰደች ያለችውን ጥቃት አጠናክራ ቀጥላለች።

ሀማስ ከምድረ ገጽ መጥፋት አለበት የምትለው እስራኤል 1.1 ሚሊዮን የሚሆኑ የሰሜን ጋዛ ነዋሪዎች እንዲወጡ ማስጠንቀቋም ይታወሳል።

እስራኤል ከአየር ድብደባ ጎን ለጎን ጋዛን በእግረኛ ወታደር ለማጥቃት በድንበር አካባቢ ወታደሮቿን አከማችታለች።

የአረብ ሀገራት እስራኤል ተኩስ እንድታቆም ያደረጉት ጥረትም አልተሳከም።

ምዕራባውያንም ቢሆን ስለተፈጠረው ሰብአዊ ቀውስ እንጂ የተኩስ መቆም ጉዳይ አላስጨነቃቸውም።ሰልፈኞቹ በእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ መኖሪያ በሆነው በዳውኒንግ ጎዳና ከመሰባሰባቸው በፊት "ነጻ ፍልስጤም" የሚል መፈክር ከፍ አድርገው አሰምተዋል።

ሰልፈኞቹ በእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ መኖሪያ በሆነው በዳውኒንግ ጎዳና ከመሰባሰባቸው በፊት "ነጻ ፍልስጤም" የሚል መፈክር ከፍ አድርገው አሰምተዋል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group