UMMA TOKEN INVESTOR

About me

الحَمْدُ ِلله for everything ©የነገ ሟች የዛሬን ሟች ይሸኛል ربنا اتنا فى الدنيا حسنةً وفي الاخرة حسنةً وقنا عذاب النار

Mesut10ibro shared a
Translation is not possible.

የእስራኤል ጦር በጋዛ የመሬት ኦፕሬሽን ላይ የጦር ወንጀል እየፈፀመ ነው። ሂትለር ያደረጋቸውን በትክክል እየፈጸሙ ነው። እባካችሁ በዚህ ኡማ ፔጅ ላይ በፊት ሼር በማድረግ ለማህበረሰቡ በማዳረስ ምድራዊ ግፋቸዉን እናጋልጥ። ፈስ ቡክ ላይ ግን አትሞክሩት ሸር አድርገ በደቂቃዎች ዉስቸጥ አዉርዶ አካዉንተንም ዘግተዉብኛልና አሁን።

5 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እዚህ የትምህርት አመቱ ተጠናቋል

ሁሉም ተማሪዎች አላህን ተገናንኝተዋል

ይህ ጋዛ ነዉ የሸሂዶች መንደር

😪😪😪

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Mesut10ibro shared a
Translation is not possible.

ፎሎወር እንዲበዛለት የሚፈልግ እነዚን ያድርግ    

1.ይሄንን አካውንት follow ያድርግ   

2. ኮሜንት ላይ 1 የራሱን ሊንክ ይፃፍ                

3. ሊንክ ያስቀመጡ 5 ሰው ፎሎው ያድርግ    

  ፎሎው የተደረጋቹ follow back መልሱ    

ልብ ይበሉ  

ይህ የሚሰራው ፎሎው የተደረጋቹ follow back ስትመልሱ ነው   

            ·ኢንሻአላህ አብረን እናድጋለን·

   

        ቢስሚላህ አሁን እንጀምረው

#በተጨማሪም ይህ ፖስት ከቆየ እየጠፋ ስለሚሄድ ሼር ሼር በማድረግ አቆዩት ለሌሎችም እንዲዳረስ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Mesut10ibro shared a
Translation is not possible.

ከቀሳም ሙጃሂዶች ቃል አቀባይ ከአቡዑበይዳ ለዐረብ መሪዎች የተላለፈ መልዕክት:-

  "የጋዛን ከበባና ፍልሚያ በስክሪን ላይ የምትመለከቱ የአረብ መሪዎች ሆይ! ሰራዊታችሁን ልካችሁ ለመስጂደል አቅሳ ክብር እንድትከላከሉ ጦራችሁን ሰብቃችሁ ስለ ወንድሞቻችሁ አፀፋዊ ምላሽ እንድትወስዱ አንጠይቃችሁም።

ሐቢቢ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሠለም) በመሰደባቸው እንድትቆጡ፣ ወደ ሰማይ ኢስራዕ ያደረጉበት ክቡር ስፍራ በደም ሲጨቀይና ሲረክስ ሰይፍ ይዛችሁ እንድትወጡ አንጠይቃችሁም። ይህንን ለኛ ተውት። ስለ መስጂደል አቅሳ ስለ ኢስላምና ስለሀገራችን ከወዳደቁ ነገሮች በእጃችን በሰራነው መሳርያ በአቅማችን ለመታገል እኛ ወስነን በመንገዱ ላይ ነን።

ነገር ግን ከፈንና ምግብ የጫኑ ተሽከርካሪዎችን ለወንድሞቻችሁ እንዴት መላክ አቃታችሁ?! ሰብአዊ እርዳታዎችን ወደ ኢስላማዊቷ ምድር ማጓጓዝ ከቶ እንዴት ተሳናችሁ?! ይህ ልንረዳው ብንሞክር ያቃተን ተፍሲር ብንፈልግለትም ያጣንለት ጉዳይ ሆኗል"

አቡ ኡበይዳ በእርግጥም እውነት ተናገረ። በጦርነት ወቅት የሴቶች ስራ ስንቅ ማቀበልና ቁስለኛ ማከም ነውና የአረብ መሪዎችን ውሃና መድኃኒት መጠየቁ ልክ ነበር።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Mesut10ibro shared a
Translation is not possible.

🔔「 በደንብ የሰሙት 」📈

▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬▭▬

✅¹:የሰሙትማ ግዴታዎቻቸውን በአግባቡ ተወጥተዋል፡፡ ሱንናዎችን ጠራርገው ሰርተዋል፡፡ አላህ ሱብሃነሁ ወተዐላ በሚወዳቸው ነገሮች ላይ ፈጥነው ተገኝተዋል፡፡ ለዚህ ዲን የቻሉትን ያህል አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡ በደንብ የሰሙት እነ ቢላል ፣ እነ ሱመያ፣ እነ ያሲር ፣ እነ ኸባብ ናቸው፡፡ በብርቱ ቅጣት በአላህ መንገድ ተፈትነውዝንፍ አላለም ከአቋማቸው፡፡በደንብ የሰሙት ለዚህ ዲን ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ታስረዋል፣ ተርበዋል ፣ ተሠደዋል ፣ ተንገላተዋል ፣ ደህይተዋል ፣ ታመዋል ፣ ቆስለዋል ፣ ደምተዋል ፣  ሙሉ ንብረታቸውን ለአላህ መንገድ ሠጥተዋል፡፡ የሚወዷትን ነፍስ ሰውተዋል፡፡

✅²:በደንብ የሰሙት ምድርን ሳይለቁ እዚሁ እያሉ የጀነት እንደሆኑ ተበስረዋል፡፡ ሥራቸው አላህ ሱብሃነሁ ወተዐላ ተቀባይነት እንዳገኘ ተነግሮአቸዋል፡፡ አላህ ወዷቸዋል፡፡ እነርሱም ባገኙት ምንዳ ተደስተዋል፡፡ በደንብ የሰሙት እነ አቡበክር፣ እነ ዑመር፣ እነ ዑስማን፣ እነ ዐሊ፣ እነ ዐብዱረህማን፣ እነ ዙበይር፣ እነ ሠዕድ፣ እነ ሰዒድ፣ እነ ዙበይር፣ እነ ጦለሃ ናቸው፡፡  

✅³:በደንብ የሰሙት ሶሃቦች ወደ ፍልሚያ ሜዳ ሲሮጡ በእጃቸው የያዙትን የተምር ፍሬ እንኳ ለመጨረስ አልታገሱም፡፡ ‹ቆስለናል፣ ደምተናልና እረፍት ያስፈልገናል፡፡ አላሉም፡፡ ‹ወቅቱ ሀሩር ነውና ዘመቻው ለሌላ ጊዜ ይተላለፍልን፡፡› ብለው አልተከራከሩም፡፡ የሰሙ ሰዎች ትእዛዙ እስኪደገምላቸው አልጠበቁም፡፡ ቁሙ ሲባሉ ቆሙ ተነሱ ሲባሉ ተነሱ፡፡ ሥሩ ሲባሉ ሰሩ፡፡ ተው ሲባሉ ተው፡፡

✅⁴:በደንብ የሰሙት ሶሃቦች ኢስላምን ለመከላከል ከፊት ነበሩ፡፡ በድር ላይ የሐምዛ ተጋድሎ ይነገራል፡፡ ኡሑድ ላይ የጦለሃ ተወርዋሪነት ይተረካል፡፡ አል አሕዛብ ላይ የዐሊ ደጀንነት ይወሣል፡፡ ሙእታ ላይ የጀዕፈር ትንግርት ይዘከራል፡፡ የርሙክ ላይ የአል ኸንሣእ ልጆች ውሎ ይተረካል፡፡

🚨እነርሱ በርግጥም በደንብ ሰምተዋል። አድርጉ የተባሉትን አድርገዋል። ተከልከሉ የተባሉትን ተከልክለዋል።

📏📏📏📏✨📏📏📏📏

➡️ሙስሊም በሰማው እና በታዘዘው ልክ ነው ስኬቱ፡፡ በደንብ የሰሙት ሁሌም ስኬት አላቸው፡፡ በሁለቱም ዓለም የበላይ ናቸው።ሰምተው የታዘዙት ጀነት ናቸው፡፡ ሰምተናል አንበል አልሠማንም፡፡ እስቲ ለአፍታም ቢሆን ቁርኣን የሚለውን በደንብ እንስማ፡፡ መልእክተኛ ﷺ የሚሉትን በደንብ እናደምጥ፡፡ ስንጠራ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ስንባል ጆሮ እንስጥ፡፡ እናዳምጥ፡፡ እናትኩር፡፡ አላህ ሱብሃነሁ ወተዐላ ምን ይላል መሠላችሁ፡፡

🔘يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَطِيعُوا اللَّهَ وَرَسُولَهُ وَلَا تَوَلَّوْا عَنْهُ وَأَنتُمْ تَسْمَعُونَ]وَلَا تَكُونُوا كَالَّذِينَ قَالُوا سَمِعْنَا وَهُمْ لَا يَسْمَعُونَ [٨:٢١]

🔴‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህንና መልክተኛውን ታዘዙ፡፡ እናንተም የምትሰሙ ስትኾኑ ከርሱ አትሽሹ፡፡ እንደነዚያም እነሱ የማይሰሙ ሲኾኑ ሰማን እንዳሉት አትሁኑ፡፡› (አል አንፋል፡ 20-21)

🔘يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اسْتَجِيبُوا لِلَّهِ وَلِلرَّسُولِ إِذَا دَعَاكُمْ لِمَا يُحْيِيكُمْ ۖ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ يَحُولُ بَيْنَ الْمَرْءِ وَقَلْبِهِ وَأَنَّهُ إِلَيْهِ تُحْشَرُونَ

🔴‹ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! (መልክተኛው) ሕያው ወደሚያደርጋችሁ እምነት በጠራችሁ ጊዜ ለአላህና ለመልክተኛው ታዘዙ፡፡ አላህም በሰውየውና በልቡ መካከል የሚጋርድ መኾኑን ወደርሱም የምትሰበሰቡ መኾናችሁን እወቁ፡፡› (አል አንፋል፡ 24)

/ አላህ ቀልብ ይስጠን /

┊  ┊  ┊  ┊

┊  ┊  ┊  ✿

┊  ┊  ❀ 📚

┊  ✿ 📌

❀ሼር አድርጉት በጥሞና ይነበብ በቻልነዉ ያህል እንስራበት الله መልካም ስራዎች አብዝተዉ እንዲሰሩ ከተወፈቁ ባሮቹ ያድርገን

https://ummalife.com/umma1698085195

kamil yemer | UmmaLife

kamil yemer | UmmaLife

kamil yemer: kamil yemer. Nikname: @umma1698085195 | One Ummah — One Network - was created as a response to the Internet technology needs of Muslims and all adherents of traditional value
Send as a message
Share on my page
Share in the group