UMMA TOKEN INVESTOR

About me

ከየትኛውም ፖለቲካዊና ሀይማኖታዊ ተፅእኖ ነፃ በሆነ መልኩ ማንኛውንም አይነት ሃገራዊ ይዘት ያላቸው ትክክለኛ እና ወቅታዊ ዜናዎችን በየግዜው ለማግኘት በፌስቡክ፣በቴሌግራም፣በቲውተር እና በኡማላይፍ ገፆቻችን ይከታተሉን!ለሀሳብና አስተያትዎ በኢሜይል Ethio24NewsAgency@yahoo.com ይፃፉልን!

Followings
0
No followings
Translation is not possible.

#አማራ #ዋግኽምራ

" ሰው ሁሉ ግራ ተጋብቶ የሚበላውንም አጥቶ ነው ያለው፤ ታይቶም ተሰምቶ የማይታወቅ በጣም የሚዘገንን ድርቅ ነው ያጋጠመን  " - የዋግኽምራ ምሽሃ ቀበሌ ነዋሪ

በአማራ ክልል፣ ዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ፤ ሰሀላ ሰየትም ወረዳ ውስጥ ስላለው አስከፊ የድርቅ ሁኔታ በተደጋጋሚ መነገሩ ይታወሳል።

በአካባቢው ስለሚገኙ ዜጎች ሁኔታ ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ጉዳይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተደጋጋሚ መልዕክቶችን ማጋራቱም ይታወሳል።

አሁንም ችግሩ በከፋ ሁኔታ ላይ ሲሆን በርካታ ወገኖች በድርቁ ችግር ውስጥ ይገኛሉ። ወደ ሚሊዮን የሚጠጉ እንስሳትም መኖ ፍለጋ ወደ አጎራባች ወረዳዎች ተሰደዋል።

በዚሁ አካባቢ ስላለው አስከፊ የድርቅ ሁኔታ ከሰሞኑን ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የሰጡ ወገኖች " ቀጣይ ኑሯችን ተስፋም የለው " ብለዋል።

አርሶ አደር ደሴ ፈንቴ ፤ የምሸሃ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ ባለፈው ክረምት በቀበሌው ምንም አይነት ዝናብ ባለመጣሉ እርሳቸውም ሆኑ ከብቶቻቸው የሚበሉት እንደሌላቸው ተናግረዋል።

በድርቁ ምክንያት የጎረቤቶቻቸው ህይወት እንዳለፈም የገለፁት አርሶ አደሩ ፤ የቤት እንስሳቶቻቸው በመሞታቸው ቀጣይ ኑሯቸው ተስፋ እንደሌለው ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ሌላው የ01 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ነጋሽ ጎበዙ ፤ " 2015 ለ2016 ምንም አይነት ሳርም ሆነ ሌላ ነገር ያልበቀለበት ፤ ታይቶም ተሰምቶ የማይታወቅ በጣም የሚዘገንን ድርቅ ነው ያጋጠመን። ሰው ሁሉ ግራ ተጋብቶ የሚበላው አጥቶ እስሳቱንም ትቶ፣ ሰውም በየቦታው እየሞተ፣ እንስሳቱም እየሞቱ በጣም የከፋ ሁኔታ ላይ ነው ደርሰን ያለነው። በጣም በጣም አስከፊ ነው። " ብለዋል።

እሳቸው የነበራቸው በርካታ ከብቶች እና ፍየሎች በረሃብ ሞተውባቸው እንዳለቁ ተናግረው ፤ " የከብቱስ ይሁን እሳሳት ናቸውና እጅግ የሚያሳዝነው የሰዎች ህይወት እያለፈ መሆኑ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህ ሳምንት እሳቸው ባሉበት አካባቢ 2 ህፃናት እና 3 አዛውንቶች በአጠቃላይ 5 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ተናግረዋል።

ከሰሞኑን በዋግኽምራ ድርቅ ያስከተለውን ጉዳት ከመንግስታዊና 18 ከሚደርሱ መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት የተውጣጣ የባለሞያዎች ቡድን በአካል ተገኝቶ ጥናት ማድረጉ ተነግሯል።

በዚህም ጥናት በሰው እና እስሳት ሞት ላይ ዳሰሳ ተደርጓል።

ምንም እንኳን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ለድርቅ ተጎጂዎች በሚል የዕለት እርዳታ እንደላከ ቢያሳውቅም የዋግኽምራ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ድጋፉ በቂ እንዳልሆነ አሳውቋል።

ያለው ችግር የእንስሳት መኖ እጥረት፣ የሰዎች ሰብዓዊ ድጋፍ እጥረት ...ሌሎችም ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንደሆነ የገለፀው ፅ/ቤቱ " የክልሉ መንግስት 600 ኩንታል ስንዴ፣ ፌዴራል መንግስት 675 ኩንታል ስንዴ አቅርበዋል፣ ረጂ ድርጅቶች 42 ሚሊዮን ብር የሚሆን በካሽ የሚከፈል አቅርበዋል። አሁን ላይ ለአንድ ወር የሚሆን 25,834 አካባቢ ሰዎችን ሊያግዝ የሚችል ድጋፍ አግኝተናል ይህ ግን ካለው ችግር አንፃር በቂ አይደለም " ብሏል።

ተጨማሪ ድጋፍ ካልተደረገ ተጨማሪ ጥፋት ሊደርስ ይችላል ሲልም ፅ/ቤቱ መግለፁን ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

Via tikvahethiopia

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

#moe

ትምህርት ሚኒስቴር ሁለት ሚኒስትር ዴኤታዎች ተሹመውለታል።

ወ/ሮ አየለች እሸቴ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም አቶ ኮራ ጡሹኔ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ከጥቅምት 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ ተሹመዋል፡፡

ወ/ሮ አየለች እሸቴ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

አቶ ኩራ ጡሹኔ በጅማ ዩኒቨርሲቲ በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲሁም በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል።

ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም ፈንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ከጥቅምት 2014 ዓ.ም ጀምረው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወቃል።

ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸው ይታወሳል።

Via @tikvahuniversity

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሩሲያ የኑክሌር ሙከራ አደረገች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሩሲያ የክሩዝ እና ባላስቲክ ሚሳኤሎችን ያቀፈ የኑክሌር ልምምድ ማድረጓን ክሬምሊን አስታወቀ፡፡

ሙከራው የሞስኮን ወታደራዊ አመራር እና ስልታዊ የኑክሌር ሀይሎች ዝግጁነት ለመገምገም ያለመ ስለመሆኑ ተመላክቷል፡፡

ልምምዱ ሶስት ወታደራዊ ዘርፎችን ያከተተ ነው የተባለ ሲሆን ÷የአህጉር አቋራጭ ባላስቲክ ሚሳኤል ልምምድ፣ኑክሌር የታጠቁ የባህር ሰርጓጅ መርከቦች ልምምድ እና ስትራቴጂካዊ ቦምቦች የልምምዱ አካል ነበሩ ተብሏል፡፡

ልምምዱ በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል በሚገኘው እና ፕሌስክ ኮስሞድሮም በተባለው የሩሲያ አህጉር አቋራጭ ማስወንጨፊያ ማዕከል መከናወኑን ነው ክሬምሊን የገለፀው፡፡

በእለቱ የተሞከረው ሀገር አቋራች ሚሳኤሉ ከተተኮሰበት ቦታ ከ5 ሺህ 700 ኪሎ ሜትር በላይ ርቀት ላይ በሚገኘው የካምችካ ባህረ ገብ መሬት ላይ ኢላማውን መምታቱ ተገልፃል፡፡

ልምምዶቹን በሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና በሞስኮ የሚገኘው የሩሲያ ብሔራዊ የመከላከያ ኦፕሬሽን ሴንተር አስተባባሪነት የተካሄዱ መሆናቸውን አር ቲ ዘግቧል፡፡

FBC

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

116ኛው የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ቀን በምስል‼

image
image
image
image
image
image
+8
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል ስራ ለመጀመር የሚያስችለውን ውይይት በመቀሌ ከተማ አካሄደ፡፡

ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) የተመራውና ሌሎች አራት ኮሚሽነሮችን ያካተተው ቡድን በመቀሌ ከባለድርሻ አካላት ጋር መወያየቱ ተመላክቷል፡፡

ቡድኑ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ተወካዮች ጋር ተገናኝቶ የተወያየ ሲሆን በቀጣይ በክልሉ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶችን ለመተግበር የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ አሰራር ኮሚሽኑ መተግበር እንደሚገባ ከስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) ኮሚሽኑ እስካሁን ስላከናወናቸው ተግባራት ገላፃ አድርገው ከእነዚህ ባለድርሻ አካላት ሊደረግላቸው የሚገቡ ትብብሮችን ጠቅሰዋል፡፡

በቀጣይ ኮሚሽኑ በክልሉ የሚያከናውናቸውን ተግባራት ደረጃ በደረጃ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየት ማከናወን እንደሚገባ በውይይቱ የተመላከተ ሲሆን የክልሉ መንግስት ኮሚሽኑ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ድጋፍ እንደሚያደርግ መግለጹን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡

@Jeilu Tv

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group