Translation is not possible.

#moe

ትምህርት ሚኒስቴር ሁለት ሚኒስትር ዴኤታዎች ተሹመውለታል።

ወ/ሮ አየለች እሸቴ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም አቶ ኮራ ጡሹኔ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን ከጥቅምት 12/2016 ዓ.ም ጀምሮ ተሹመዋል፡፡

ወ/ሮ አየለች እሸቴ የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

አቶ ኩራ ጡሹኔ በጅማ ዩኒቨርሲቲ በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲሁም በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ለረጅም ዓመታት አገልግለዋል።

ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ እንዲሁም ፈንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ከጥቅምት 2014 ዓ.ም ጀምረው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወቃል።

ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸው ይታወሳል።

Via @tikvahuniversity

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group