#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_6
#ሐዲሥ 49 / 396
ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ በማለት ዐብደላህ ኢብኑ ዑትባህ ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ)፥ አስተላልፈዋል፦ “በነቢዩ (ﷺ) የሕይወት ዘመን የሰዎች (እውነተኛ) ማንነት በራዕይ (ወሕይ) ይገለጽ ነበር። ራዕዩ (ወሕዩ) ተቋርጧል። ስለዚህም አሁን ማንነታችሁን የምንወስነው በገሃድ በምናየው ሥራችሁ ነው። መልካም (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን እናምነዋለን። እናቀርበዋለን። ውስጡን የመፈተሽ መብት አልተሰጠንም። ውስጡን አላህ ይፈትሸዋል። ክፉ (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን ደግሞ አናምነውም። እውነት ብለን አንቀበለውም። ውስጡ መልካም እንደሆነ ቢናገረም። (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሰዎችን በግልጽ ከሚያሳዩት ባሕሪና ሥራ አንጻር ብቻ እስልምናቸውን መቀበል ግድ ነው። ውስጥን መፈተሽ የሰዎች መብት አይደለም።
2/ መልካም ኒይያ (ልበ-ውሳኔ) ከሸሪዓዊ ቅጣት አያድንም።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረ.ዐ) ተከታዩን ሲናገሩ አድምጫለሁ በማለት ዐብደላህ ኢብኑ ዑትባህ ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ)፥ አስተላልፈዋል፦ “በነቢዩ (ﷺ) የሕይወት ዘመን የሰዎች (እውነተኛ) ማንነት በራዕይ (ወሕይ) ይገለጽ ነበር። ራዕዩ (ወሕዩ) ተቋርጧል። ስለዚህም አሁን ማንነታችሁን የምንወስነው በገሃድ በምናየው ሥራችሁ ነው። መልካም (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን እናምነዋለን። እናቀርበዋለን። ውስጡን የመፈተሽ መብት አልተሰጠንም። ውስጡን አላህ ይፈትሸዋል። ክፉ (ባሕሪና ተግባር) ያሳየንን ደግሞ አናምነውም። እውነት ብለን አንቀበለውም። ውስጡ መልካም እንደሆነ ቢናገረም። (ቡኻሪ ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ ሰዎችን በግልጽ ከሚያሳዩት ባሕሪና ሥራ አንጻር ብቻ እስልምናቸውን መቀበል ግድ ነው። ውስጥን መፈተሽ የሰዎች መብት አይደለም።
2/ መልካም ኒይያ (ልበ-ውሳኔ) ከሸሪዓዊ ቅጣት አያድንም።
Umma Life
ቴሌግራም/ telegram/