1 week Translate
Translation is not possible.
#አላህን_መፍራት
ክፍል_2
አላህ እንዲህ ብሏል፦
"አላህም ነፍሱን (ቁጣውን) ያስጠነቅቃችኋል።" (አል_ዒምራን፡ 28)
#ሐዲሥ 50/398
ኢብኑ መስዑድ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ "ጀሀነም በመጭው ዓለም ሰባ ሺህ ልጓም ያላት ሆናና እያንዳንዱን ልጓም ሰባ ሺህ መላኢክት ይዞት፥ እየተጎተተች ትቀርባለች፡፡" (ሙስሊም ዘግበውታል)
ከሐዲሡ የምንማረው ቁምነገር
፨ ገለጻው እውነተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ የጀሀነምን ታላቅነትና አስፈሪነት ለመግለጽ የቀረበ ምሳሌያዊ አነጋገር ሊሆንም ይችላል። ዞሮ ዞሮ የተፈለገው የሰው ልጅ በመጭው ዓለም የሚጠብቀው እጣ ፈንታ ሊያስፈራው እንደሚገባ ማስታወስ ነው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group