#የሰዎችን #ውጫዊ #እንቅስቃሴና #ተግባር (#አምኖ) #መቀበልና #ውስጣቸውን #ለአላህ #መተው
#ክፍል_4
#ሐዲሥ 49 / 394
ኡሳማ ኢብኑ ዘይድ (ረ.ዐ) ተከታዩን አስተላልፈዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) የጁሀይና ጐሣ አባል ወደ ሆነው ጁሀይና ወደ ተባለ ጦር አዘመቱን። ሰዎችን በጧት መጣንባቸው (ማልደን ዘመትንባቸው)። እኔና አንድ የአንሷር ሰው ከነርሱ ከሆነ አንድ ሰው ጋር (ፍልሚያ) ተገናኘን። ስንከበው “ከአላህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም” አለ። የአንሷሩ ሰው እጁን ሰበሰበ። እኔ ግን በጦር ወግቼ ገደልኩት፡፡ መዲና ስንገባ ይህ (ድርጊቴ) ለነቢዩ (ﷺ) ተነገራቸው። “ኡሳማ ሆይ! ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት እኮ ከግድያችን ለመጠበቅ ነው” አልኳቸው። “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ በድጋሜ። ከዚያን ቀን በፊት ባልሰለምኩ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን ጥያቄ) ደጋገሙት፡፡ (ቡኻሪና ሙስሊም)
በሌላ ዘገባ ደግሞ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ)፦ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት ሰይፍ ፈርቶ ነው” አልኳቸው። “የተናገራት ከአንጀቱ ይሁን ከአንገቱ ልቡን ከፍተህ አይተኸዋልን?” አሉ። የሰለምኩት የዚያኑ ቀን በሆነ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን አባባል) ደጋገሙት፡፡
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ አንድ ሰው መስለሙን ለመቀበል ግልጽ ቃል ወይም ተግባር ማየቱ በቂ ነው። ውስጥን መፈላፈል አግባብ አይደለም። ይህ ሸሪዓዊ ድንጋጌ “ውስጡ አልሰለመም ይሆናል” በሚል ሰበብ ብቀላ ለሚሹ ወገኖች መንገድ ለመዝጋት ነው።
2/ የአላህ መልዕክተኛ በኡሳማ ላይ የሞት ብይን (ቂሷስ) ያላስተላለፉት ነገሩ ግልጽ ስላልሆነለት (ሹብሃ ስለነበረበት) ነው። የሞት ቅጣት በእንዲህ ዓይነት ሹብሃዎች ይቀራል። ይሁንና የደም ካሳ (ዲያህ) አይቀርም።
3/ ታላቅ ወንጀል የሠራ “ከዚያ በፊት ባልሰለምኩ” ብሎ መመኘት አይፈቀድለትም። ኡሳማ ይህን ያለው _ የሚፈቀድ ሆኖ ሳይሆን _ ከነቢዩ ጠንካራ ውግዘት የተነሳ ልቡ በፍርሃት ስለራደና ስለተጨነቀ ነው።
Umma Life
https://ummalife.com/MuslimEthio
ቴሌግራም/ telegram/
https://t.me/ethiomuslim_1
ኡሳማ ኢብኑ ዘይድ (ረ.ዐ) ተከታዩን አስተላልፈዋል፦ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) የጁሀይና ጐሣ አባል ወደ ሆነው ጁሀይና ወደ ተባለ ጦር አዘመቱን። ሰዎችን በጧት መጣንባቸው (ማልደን ዘመትንባቸው)። እኔና አንድ የአንሷር ሰው ከነርሱ ከሆነ አንድ ሰው ጋር (ፍልሚያ) ተገናኘን። ስንከበው “ከአላህ ውጭ ሌላ አምላክ የለም” አለ። የአንሷሩ ሰው እጁን ሰበሰበ። እኔ ግን በጦር ወግቼ ገደልኩት፡፡ መዲና ስንገባ ይህ (ድርጊቴ) ለነቢዩ (ﷺ) ተነገራቸው። “ኡሳማ ሆይ! ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት እኮ ከግድያችን ለመጠበቅ ነው” አልኳቸው። “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ በድጋሜ። ከዚያን ቀን በፊት ባልሰለምኩ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን ጥያቄ) ደጋገሙት፡፡ (ቡኻሪና ሙስሊም)
በሌላ ዘገባ ደግሞ የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ)፦ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ካለ በኋላ ገደልከውን?” አሉኝ። “የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ያላት ሰይፍ ፈርቶ ነው” አልኳቸው። “የተናገራት ከአንጀቱ ይሁን ከአንገቱ ልቡን ከፍተህ አይተኸዋልን?” አሉ። የሰለምኩት የዚያኑ ቀን በሆነ ብዬ እስክመኝ ድረስ (ይህን አባባል) ደጋገሙት፡፡
ከሐዲሡ የምንማራቸው ቁምነገሮች
1/ አንድ ሰው መስለሙን ለመቀበል ግልጽ ቃል ወይም ተግባር ማየቱ በቂ ነው። ውስጥን መፈላፈል አግባብ አይደለም። ይህ ሸሪዓዊ ድንጋጌ “ውስጡ አልሰለመም ይሆናል” በሚል ሰበብ ብቀላ ለሚሹ ወገኖች መንገድ ለመዝጋት ነው።
2/ የአላህ መልዕክተኛ በኡሳማ ላይ የሞት ብይን (ቂሷስ) ያላስተላለፉት ነገሩ ግልጽ ስላልሆነለት (ሹብሃ ስለነበረበት) ነው። የሞት ቅጣት በእንዲህ ዓይነት ሹብሃዎች ይቀራል። ይሁንና የደም ካሳ (ዲያህ) አይቀርም።
3/ ታላቅ ወንጀል የሠራ “ከዚያ በፊት ባልሰለምኩ” ብሎ መመኘት አይፈቀድለትም። ኡሳማ ይህን ያለው _ የሚፈቀድ ሆኖ ሳይሆን _ ከነቢዩ ጠንካራ ውግዘት የተነሳ ልቡ በፍርሃት ስለራደና ስለተጨነቀ ነው።
Umma Life
ቴሌግራም/ telegram/