🔻 የፕሬዝዳንት ባይደን ንግግር አጫጭር ነጥቦች እና ዓለም አቀፉ ምላሽ።
ያለፉት ጥቂት ወራት ለእስራኤላውያን እና ፍልስጤማውያን “አንጀት የሚበላ” ነበር ሲሉ ንግግራቸውን የጀመሩት ባይደን ሐማስ ኦክቶበር 7 በደቡብ እስራኤል ላይ ያደረሰውን ጥቃት በማውገዝ እስራኤል “ራሷን የመከላከል መብት አላት” በማለት የተለመደ ንግግራቸውን ደግመውታል። በመቀጠልም "እስራኤል ሃማስን የመፋለም መብት አላት" እንዲሁም የፍልስጤሙ ቡድን ትጥቁን በመፍታት እና ምርኮኞቹን በመመለስ የጋዛን ጦርነት ማስቆም ይችላል በማለት ቀልድ የሚመስል ንግግር ተናግሯል።
ላለፉት ወራት የጋዛ ጦና ሚኒስቴር መረጃን አላምንም ሲል ነበረው ባይደን በመጨረሻም “ከ30,000 በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል፣ አብዛኞቹ ሃማስ አይደሉም" በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሐን ሴቶች እና ሕፃናት፣ ልጃገረዶች እና ወንዶች ልጆች ወላጅ አልባ ሆነዋል በማለት የጋዛ ጤና ሚኒስቴር ያወጣውን መረጃ መቀበሉን የሚያሳይ ምስክርነት ሰጥቷል። ባይደን የአሜሪካ ወታደሮች በጋዛ ውጊያ ላይ እንደማይሳተፉ የተናገረ ሲሆን “ምግብ፣ ውሃ፣ መድሀኒት እና ጊዜያዊ መጠለያ የጫኑ ትላልቅ ጭነቶች መቀበል” የሚችል “ጊዜያዊ ወደብ” እንዲቋቋም ወታደራዊ መመሪያው እንደሰጠ ተናግሯል።
ባይደን ይህን ወደብ ለማዘጋጀት ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድ ምንም ያለው ነገር የለም፡፡ ፕሬዝዳንቱ የእስራኤል አመራር ለጋዛ የሚቀርበውን እርዳታ እንደ መደራደሪያ እንዳይጠቀም አስጠንቅቋል። “እስራኤል የበኩሏን ማድረግ አለባት። እስራኤል ተጨማሪ እርዳታ ወደ ጋዛ መፍቀድ አለባት፣ የሰብአዊ እርዳታ ሰራተኞች በተኩስ ውስጥ ሰለባ እንዳይሆኑ ማድረግ አለባት ብሏል። የእስራኤል ጦር በጋዛ ላይ ያካሄደው ጦርነት በኤጀንሲው ታሪክ ውስጥ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰራተኞች እጅግ ገዳይ ከሆኑት አንዱ ነው ብሏል ባይደን፡፡
የአልጀዚራ ከፍተኛ የፖለቲካ ተንታኝ ማርዋን ቢሻራ ባይደን በጋዛ ለዕርዳታ “ጊዜያዊ ወደብ ለመገንባት” ማወጁ ዋሽንግተን ለእስራኤል የምታደርገውን ቀጣይ ድጋፍ የሚያደናቅፍ ነው ብለዋል። "እኔ እንደማስበው እንደዚህ ያለ መግለጫ በጋዛ ውስጥ ያለውን ስቃይ ለማብቃት ከሚደረገ ልባዊ ሙከራ ይልቅ, ትወና እና በይበልጥ የህዝብ ግንኙነት ስራ ነው…" ሲል ማርዋን ቢሻራ ሃሳቡን ተችቷል፡፡
የአሜሪካ-ኢስላማዊ ግንኙነት ምክር ቤት (The Council on American-Islamic Relations CAIR) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በጋዛ የተኩስ አቁምን እንዲደረግ የዋሽንግተንን አቅም መጠቀም አለባቸው ብሏል። "ፕሬዚዳንት ባይደን በጋዛ ጭፍጨፋ ላይ ነዳጅ እየቸመሩ እሳቱን በማባባስ እና እሳት አደጋውን ለማጥፋት የሚሞክ ሰው ሚናን ለመጫወት መሞከር ማቆም አለባቸው" ሲል ምክር ቤቱ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ አስፍሯል ።
የእስራኤልን እገዳ ለማለፍና አሜሪካ ሰብአዊ እርዳታ ለማድረስ በጋዛ ላይ ወደብ መገንባት ወይም በጋዛ ላይ በአውሮፕላን ምግብ መጣል አያስፈልጋትም ይልቁንም በሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ቦምቦችን እና በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ወደ እስራኤል መንግስት መላክ የለባትም ብሏል ምክር ቤቱ።
በጋዛ ጦርነት ወቅት እስራኤልን በመደገፍ ላሳየው ተባባሪነት ባይደን ላይ ጫና ለመፍጠር ታስቦ በሚኒሶታ በተመሰረተው የ"ምንም ምርጫ" (“no preference”) ዘመቻ አስተባባሪ አስማ መሀመድ የባይደን ንግግር “እንዳስቆጣት” ተናግራለች። አስማ ለአልጀዚራ እንደተናገረችው “ፕሬዚዳንቱ ጭፍጨፋውን ባላየ እንዳለፉ ሲያስቡ የነበሩ መራጮችን የበለጠ ያገለለ ይመስለኛል ባይደን ለፍልስጤማውያን ባለው ሀዘኔታ ዙሪያ “የሚያምሩ ቃላት” ቢጠቀምም የአሜሪካን ፖሊሲ እንደገና መገምገም አልቻለም ስትል ተችታለች።
ኦማር በዳር አሜሪካ ለጋዛ የእርዳታ ወደብ እንደምታቋቁም መገለፁ የበይደን አስተዳደር እስራኤልን መደገፏን እና ማስታጠቋን ሊሸፍን እንደማይችል በመግለጽ ውድቅ አድርገውታል።
በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት @ethmohammedia ገፅን ፎሎው ያድርጉ
🔻 የፕሬዝዳንት ባይደን ንግግር አጫጭር ነጥቦች እና ዓለም አቀፉ ምላሽ።
ያለፉት ጥቂት ወራት ለእስራኤላውያን እና ፍልስጤማውያን “አንጀት የሚበላ” ነበር ሲሉ ንግግራቸውን የጀመሩት ባይደን ሐማስ ኦክቶበር 7 በደቡብ እስራኤል ላይ ያደረሰውን ጥቃት በማውገዝ እስራኤል “ራሷን የመከላከል መብት አላት” በማለት የተለመደ ንግግራቸውን ደግመውታል። በመቀጠልም "እስራኤል ሃማስን የመፋለም መብት አላት" እንዲሁም የፍልስጤሙ ቡድን ትጥቁን በመፍታት እና ምርኮኞቹን በመመለስ የጋዛን ጦርነት ማስቆም ይችላል በማለት ቀልድ የሚመስል ንግግር ተናግሯል።
ላለፉት ወራት የጋዛ ጦና ሚኒስቴር መረጃን አላምንም ሲል ነበረው ባይደን በመጨረሻም “ከ30,000 በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል፣ አብዛኞቹ ሃማስ አይደሉም" በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሐን ሴቶች እና ሕፃናት፣ ልጃገረዶች እና ወንዶች ልጆች ወላጅ አልባ ሆነዋል በማለት የጋዛ ጤና ሚኒስቴር ያወጣውን መረጃ መቀበሉን የሚያሳይ ምስክርነት ሰጥቷል። ባይደን የአሜሪካ ወታደሮች በጋዛ ውጊያ ላይ እንደማይሳተፉ የተናገረ ሲሆን “ምግብ፣ ውሃ፣ መድሀኒት እና ጊዜያዊ መጠለያ የጫኑ ትላልቅ ጭነቶች መቀበል” የሚችል “ጊዜያዊ ወደብ” እንዲቋቋም ወታደራዊ መመሪያው እንደሰጠ ተናግሯል።
ባይደን ይህን ወደብ ለማዘጋጀት ምን ያህል ጊዜ እንደሚወስድ ምንም ያለው ነገር የለም፡፡ ፕሬዝዳንቱ የእስራኤል አመራር ለጋዛ የሚቀርበውን እርዳታ እንደ መደራደሪያ እንዳይጠቀም አስጠንቅቋል። “እስራኤል የበኩሏን ማድረግ አለባት። እስራኤል ተጨማሪ እርዳታ ወደ ጋዛ መፍቀድ አለባት፣ የሰብአዊ እርዳታ ሰራተኞች በተኩስ ውስጥ ሰለባ እንዳይሆኑ ማድረግ አለባት ብሏል። የእስራኤል ጦር በጋዛ ላይ ያካሄደው ጦርነት በኤጀንሲው ታሪክ ውስጥ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰራተኞች እጅግ ገዳይ ከሆኑት አንዱ ነው ብሏል ባይደን፡፡
የአልጀዚራ ከፍተኛ የፖለቲካ ተንታኝ ማርዋን ቢሻራ ባይደን በጋዛ ለዕርዳታ “ጊዜያዊ ወደብ ለመገንባት” ማወጁ ዋሽንግተን ለእስራኤል የምታደርገውን ቀጣይ ድጋፍ የሚያደናቅፍ ነው ብለዋል። "እኔ እንደማስበው እንደዚህ ያለ መግለጫ በጋዛ ውስጥ ያለውን ስቃይ ለማብቃት ከሚደረገ ልባዊ ሙከራ ይልቅ, ትወና እና በይበልጥ የህዝብ ግንኙነት ስራ ነው…" ሲል ማርዋን ቢሻራ ሃሳቡን ተችቷል፡፡
የአሜሪካ-ኢስላማዊ ግንኙነት ምክር ቤት (The Council on American-Islamic Relations CAIR) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት በጋዛ የተኩስ አቁምን እንዲደረግ የዋሽንግተንን አቅም መጠቀም አለባቸው ብሏል። "ፕሬዚዳንት ባይደን በጋዛ ጭፍጨፋ ላይ ነዳጅ እየቸመሩ እሳቱን በማባባስ እና እሳት አደጋውን ለማጥፋት የሚሞክ ሰው ሚናን ለመጫወት መሞከር ማቆም አለባቸው" ሲል ምክር ቤቱ በማህበራዊ ሚዲያው ላይ አስፍሯል ።
የእስራኤልን እገዳ ለማለፍና አሜሪካ ሰብአዊ እርዳታ ለማድረስ በጋዛ ላይ ወደብ መገንባት ወይም በጋዛ ላይ በአውሮፕላን ምግብ መጣል አያስፈልጋትም ይልቁንም በሺዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ቦምቦችን እና በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ወደ እስራኤል መንግስት መላክ የለባትም ብሏል ምክር ቤቱ።
በጋዛ ጦርነት ወቅት እስራኤልን በመደገፍ ላሳየው ተባባሪነት ባይደን ላይ ጫና ለመፍጠር ታስቦ በሚኒሶታ በተመሰረተው የ"ምንም ምርጫ" (“no preference”) ዘመቻ አስተባባሪ አስማ መሀመድ የባይደን ንግግር “እንዳስቆጣት” ተናግራለች። አስማ ለአልጀዚራ እንደተናገረችው “ፕሬዚዳንቱ ጭፍጨፋውን ባላየ እንዳለፉ ሲያስቡ የነበሩ መራጮችን የበለጠ ያገለለ ይመስለኛል ባይደን ለፍልስጤማውያን ባለው ሀዘኔታ ዙሪያ “የሚያምሩ ቃላት” ቢጠቀምም የአሜሪካን ፖሊሲ እንደገና መገምገም አልቻለም ስትል ተችታለች።
ኦማር በዳር አሜሪካ ለጋዛ የእርዳታ ወደብ እንደምታቋቁም መገለፁ የበይደን አስተዳደር እስራኤልን መደገፏን እና ማስታጠቋን ሊሸፍን እንደማይችል በመግለጽ ውድቅ አድርገውታል።
በሙስሊሙ ዓለም የተፈጠሩ ሁሉንም አዳዲስ መረጃዎች በተለይም በወቅታዊ የፍልስጤም ጉዳይ እውነተኛ እና ሚዛናዊ መረጃ ለማግኘት የሙሐመድ ትውልድ ገፅን ፎሎው ያድርጉ