UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

አሜሪካ በሶሪያ ያሉ ወታደሮቿን ባጠቁ አካላት ላይ የአየር ላይ ጥቃት መፈጸማን ገለጸች

October 27, 2023

በሶሪያ እና ኢራቅ ባሉ የአሜሪካ ወታደሮች ላይ የድሮን ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ተገልጿል

አሜሪካ በሶሪያ ያሉ ወታደሮቿን ባጠቁ አካላት ላይ የአየር ላይ ጥቃት መፈጸማን ገለጸች።

ከ20 ቀናት በፊት ለፍስልጤም ነጻነት እታገላለሁ የሚለው ሐማስ በእስራኤል ላይ ያልታሰበ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ በአካባቢው ጦርነት ተቀስቅሷል፡፡

ይዚህ ጦርነት አሁንም መቀጠሉን ተከትሎ የዓለም ሀገራት ለእስራኤል እና ፍልስጤም የቀጥታ እና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ ላይ ናቸው።

አሜሪካ ለእስራኤል የቀጥታ ድጋፍ ካደረጉ ሀገራት መካከል ዋነኛዋ ስትሆን ኢራን እና ሌሎች ሀገራት እና ቡድኖች ጎራ ለይተው ድጋፍ በማድረግ ላይ ናቸው።

የየመን አማጺያንን ጨምሮ በሶሪያ እና ኢራቅ ያሉ ቡድኖች አሜሪካ በእስራኤል-ሐማስ ጦርነት ጣልቃ እንዳትገባም ሲያስጠነቅቁ ቆይተዋል።

ይሁንና አሜሪካ ለእስራኤል የጦር መሳሪያ በቀጥታ ድጋፍ ማድረጓን ተከትሎ በሶሪያ እና ኢራቅ ባለው ወታደራዊ የጦር መንደሮቿ ላይ የድሮን ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ተገልጿል።

ዋሽንግተን በሁለቱ ሀገራት በደረሰባት የድሮን ጥቃት የአጸፋ እርምጃ መውሰዷን አስታውቃለች።

አሜሪካ እንዳለችው በሶሪያ እና ኢራቅ ባለው የጦር መንደሮች ላይ ጥቃት የፈጸሙት በኢራን የሚደገፉ ቡድኖች ናቸው።

አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ተጨማሪ የጦር መሳሪያዎችን ያሰማራች ሲሆን 900 ተጨማሪ ወታደሮችን ደግሞ በቅርቡ ወደ አካባቢው እንደምትልክ አስታውቃለች።

የእስራኤል-ሐማስ ወይም ፍልስጤም ጦርነት አሁንም የቀጠለ ሲሆን ኢራን እና ቱርክ ጦርነቱ ካልቆመ ወደ ጎረቤት ሀገራት ሊዛመት እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሃማስ ለእስራኤል የምድር ጦር ወረራ ምለሽ ለመስጠት ዝግጁ ነኝ አለ

ሃማስ እስራኤል በጋዛ ለምታካሂደው የምድር ወረራ ተገቢውን ምለሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን አስታውቋል።

የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ዛሬ ማምሻውን በሰጠት መግለጫ፤ የምድር ኃይላችን በጋዛ የሚያደርገውን ዘመቻ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ አስፋፍቶ ያካሂዳል ብለዋል።

የህንን ተከትሎ ሃማስ እስራኤልወረራ ከፈጸመች ዝግጁ ነኝ ማለቱን አጃንስ ፍራንስ ፕሬዝ ዝግቧል።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ሩሲያ የሀማስን ልኡካን ቡድን መጋበዟ ተገቢ መሆኑን ገለጸች

October 27, 2023

ፔስኮ እንደገለጹት የሀማስ ልኡካን ቡድን አባላት በሩሲያ ቆይታቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተወካዮች ጋር ተገናኝተዋል

ሩሲያ የሀማስን ልኡካን ቡድን መጋበዟ ተገቢ መሆኑን ገለጸች።

ሩሲያ የሀማስን የልኡካን ቡድን ወደ ሞስኮ ለመጋበዝ ያሳለፈችውን ውሳኔ ትክክል ነው ተከላክላለች።

ይህ የሩሲያ ውሳኔ እስራኤልን አስቆጥቷታል።

የእስራኤል ጦር የምድር ኃይል የጋዛ ሰርጥ ዘመቻን ከዛሬ ጀምሮ በስፋት እንደሚያከናውን ገለጸ

የሩሲያ ቤተ መንግስት ክሬሚሊን ቃል አቀባይ ዲሜትሪ ፔስኮቭ ሩሲያ "በእስራኤል- ፍልስጤም ግጭት ውስጥ ያሉ ሀሉንም አካላት ማነጋገር አስፈላጊ ነው ብላ ታምናለች" ብለዋል።

ፔስኮ እንደገለጹት የሀማስ ልኡካን ቡድን አባላት በሩሲያ ቆይታቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተወካዮች ጋር ተገናኝተዋል።

የስራኤል እና ሀማስ ግጭት ከተቀሰቀሰ ከሶስት ሳምንት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን እና የሀማስ ተወካዮች በሞስኮ መገናኘታቸውን የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በትናንትናው እለት አስታውቋል።

ነገርግን ሚኒስቴሩ የውይይቱ ይዘት ምን እንደሆነ አልገለጹም።

በድርጊቱ የተቆጣችው እስራኤል ሩሲያ ሞስኮን እየጎበኙ ያሉትን የሀማስ የልኡካን ቡድን አባላትን እንድታባርር ጠይቃ ነበር።

ሩሲያ ከሀማስ ጋር የቆየ ግንኙት ያላት በመሆኑ እንደ አሜሪካ እና አውሮፖ ሽብርተኛ ድርጅት ብላ አልፈረጀችውም።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ለእስራኤል ፖሊስ መለዮ ያቀርብ የነበረው ኩባንያ ውሉን አቋረጠ

የህንዱ ማርያን ጨርቃ ጨርቅ ኩባንያ ለእስራኤል ፖሊስ መለዮ በማቅረብ ላይ የነበረ ሲሆን ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ውሉን ማቋረጡን አስታውቋል።

ኩባንያው ውሉን ያቋረጠው የእስራኤል ፖሊስ የሙያ ስነ ምግባሩን ጠብቆ እየሰራ አይደለም በሚል እንደሆነ ኢንዲያን ታየምስ ዘግቧል።

የኩባንያው ስራ አስኪያጅ ቶማስ አሊካል እንዳሉት የእስራኤል ጦር በተለይም በጋዛ በሚገኘው አል አህሊ ሆስፒታል ላይ የፈጸመው ጥቃት ውሉን እንዲያቆም ዋነኛው ምክንያት ነው።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
bereket zeinu Сhanged his profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group