UMMA TOKEN INVESTOR

Ahmedin Alemu paylaştı
7 ay Çeviri
Çeviri imkansız.

“የእናት ሀቅ.. መች ይለቅ! ”

(እውነተኛ)-ክፍል አንድ

ፀሀፊ✍፡አብዱልጀባር ፋሪስ

@finding_hubullah

ይህንን ታሪክ የምጽፍላችሁ በቅርቡ አያቴና እናቴ ካካፈሉኝ ነው። እውነተኛ እና እዚሁ ሀገራችን ውስጥ የተከሰተ ጉድ የሚያስብል ነው። በመጀመርያ ቻናሌን ሁሌም Unmute በማድረግና pin to top የሚለውን ተጭነው በቀላሉ መከታተል ይችላሉ። ቻናላችን ፍፁም ከCopy paste የፀዳ ነው። በዚህም አዳዲስ ፅሁፎችን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ወሬ ሳላበዛ ታሪኩን ልቀጥል..

ታሪኩ በቅርቡ ከአንድ ወይም ሁለት አመት በፊት የተከሰተ ነው። እናት ከልጆቿ ጋር ኑሮዋን መስርታ መኖር ከጀመረች ሰነባብታለች። የመጀመርያ ትሁን ባይነገረኝም ታላቅ ልጇ ትዳር መስርታ መኖር ጀምራለች። ታድያ ታናሹ ወጣት ልጅሆዬ እናቱ ላይ እንደ ልቡ ይደነፋል። በዚህ ስራው እናት ከልብ ትፈራዋለች። ፍራቻዋ የመነጨው እሱ ለሷ ከሚያሳያት ትዕቢት እንጂ ሌላ አይደለም። ይገርማል የሰው ነገር! ሽንቱን በእጇ ጠርጋ ያሳደገችው እናቱን ግልምጫው አንሶ ሊመታት ይቃጣዋል። ምን ዓይነት ጭንቅላት ነው ይህን ሚቀበለው!!

እናም ከእለታት በአንዱ ቀን ልጅ ለእናቱ የሞባይል ስልኩን ቻርጅ እንድታስደርግለት አስጠንቅቆ ይሰጣታል። ወቸው ጉድ! እናቱን ይልካል.. እናት በትዕዛዙ መሰረት ገበያ ስትወጣ ስልኩን በጡቶቿ መሃል ቋጥራ ከምትይዘው ብር ጋር አያይዛ ታስቀምጠዋለች። ግብይቷን እንደጨረሰችም የልጇን ስልክ ቻርጅ ለማስደረግ ብትመልከት ከቦታው አጣችው። በድንጋጤ በአካባቢዋ ፈለገች።

ስትባክን ውላ ምንም ልታገኝ ስላልቻለች በፍራቻ ወደ ታላቅ ልጇ ቤት አመራች። 9 ወር በሆዳ ተሸክማው፣ 2 ዓመት ያጠባችውና ተንከባክባ ቆንጥጣ ያሳደገችው ልጁን ትፈራዋለች። የሰው ነገርኮ ጉድ ነው ወዳጆቼ! ግና ልጇ ቤት ደርሳ ችግሩን ነገረቻት። ስልኩ ካስቀመጠችበት መጥፋቱንና ልጅየውም እንደሚገላት አስረድታ አብራት እንድትሄድ ተማፀነቻት። ልጅ ምንም ሳይመስላት “ኧረ እማዬ ምንም አያደርግሽም። ይልቅ እመጣለሁ። ሂጂ” ብላ ከነፍርሃቷ አሰናበተቻት። እናት ሁሉ ነገር ጠቦባታል። ቤት ስትደርስ አንዳች ክፋ ነገር እንደሚገጥማት ጠርጥራለች። ከዚህ ስሜት ጋር ቤት ደረሰች። ቤት ስትደርስ አንዳች ክፋ ነገር እንደሚገጥማት ጠርጥራለች። ማይደረስ የለምና ከዚህ ስሜት ጋር ቤቷ ደረሰች። ልጅየው ከሁለት ጓደኞቹ ጋር ሆኖ ቤት ተቀምጧል። እናት ከበሩ እንደገባች በጥያቄ ጀመራት። “ስልኬን ስጪኝ” ብሎ ከተቀመጠበት ወደሷ ተራመደ። አንዳች ነገር እንዳይደርስባት የሰጋችው እናት ተርበደበደች። ልጇ ከሚያደርስባት ክፋ ነገር ለማምለጥም እንዲህ ብላ የጠፋውን ስልክ እንደምትክሰው ለማሳመን ንግግር ጀመረች..

“ይሃውልህ የኔ ልጅ! እኛ ቤት ያለችውን ላም ከነ ጥጃዋ ወስደህ መሸጥ ትችላለህ። በምታገኘው ብርም የጠፋብህን ስልክ ትተካለህ። ስልክህ ካስቀመጥኩበት ወድቆ ጠፍቷል” አንዳች ነገር እንዳይደርስባት ትንቀጠቀጣለች። ልጅ ይሄንን ንግግር እየጠበቀ ይመስል እናቱን ዘልሎ አንነቃት። ጎሮሮዋን ይዞ ትንፋሽ እስኪያጥራት አንጠራራት።

ውይይ የሰው ጭካኔ!! እናትን አንቆ ለመግደል ይቃጣል። ሊያውም በተልካሻ ምክንያት። ምናለ እንኳን ስልኩን ልጁን እንኳ ብትደግልበት ባይነካት። እኮ! እናት ናት። እሷ ባትወልደው ከየት አባቱ ይገኝና ነው?!! የጠፋበትን ስልክ ዋጋ እጥፍ የሚሆን ንብረትም "ተክተህ ውስድ" ብላ እየተማፀነችው፤ በእንቢተኝነቱ ፀና። እንዳነቃትም እዛው ገደላት። አዎ! እናቱን አንቆ ገደለ።

ያ አላህ! ለተራ ስልክ ብሎ እሱንም ስልኩንም እንዲገኝ የመጀመርያ ሰበብ የነበረችውን እናቱን ገደለ። በድርጊቱ በጣም ነበር ያዘንኩት። እናቴ ይህንን ስትሰማ በጣም ነበር ያለቀሰችው። የሞተችውን ባታውቃትም፤ ሰው ሊያውም እናት በልጇ ታንቃ ስትሞት መስማት ይዘገንናል። ታላቅ እህት ሮጣ ወደ ቤቱ ስትደርስ እናት መሬት ላይ ተዘርራለች። አይኗን ማመን አልቻለችም። ይሄኔ ኡኡታዋን አቀለጠችው...

ልጁ ምን እንደገጠመው በክፍል ሁለት(በመጨረሻው)ይቀጥላል... እባካችሁ ሼር!! በናንተ ምክንያት ብዙ ሰው የእናቱን ክብር ሊያውቅና ሊረዳ ይችላል። ታሪኩ በጣም አሳዛኝ ነው። በዚህ አላበቃም የልጁ ጉዳይ።

Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş
Ahmedin Alemu paylaştı
Çeviri imkansız.

መህዲ ማነው?

‹‹መህዲ›› በመጨረሻው ዘመን ከደጃልና ዒሳ መምጣት አስቀድሞ የሚነሳ ታላቅ ‹‹ኸሊፋ›› ነው። ‹‹መህዲ›› የማዕረግ ስሙ ሲሆን ‹‹ሁዳ›› ከሚለው ቃል የተገኘና ‹‹የተመራ ቅን ኸሊፋ›› ማለት ነው። መጠሪያ ሙሉ ስሙ ደግሞ ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ አል-መህዲ›› ነው።

ስለ መህዲ በቁርኣን የተነገረ ምንም ነገር አናገኝም። መረጃዎቹ በሙሉ ከሐዲስ የተገኙ ሲሆን ከሃያ በላይ የተረጋገጡ ዘገባዎች ይገኛሉ። ብዙ የሱንና ዑለማዎች ስለ መህዲ የፃፉ ሲሆን ቲርሚዚና አቡ-ዳውድ ራሱን የቻለ ምዕራፍ ሰጥተውታል።

ከሁሉም ታዋቂው ሐዲስ አቡ-ዳውድ የዘገቡት ሲሆን ነቢዩ (ዐሰወ) እንዲህ ብለዋል፡-

‹‹ትንሳኤ ሊቆም አንድ ቀን ቢቀረው እንኳን አላህ ከቤተሰቤ የሆነን፤ ስሙ ከእኔና ከአባቴ ጋር የሚመሳሰል መሪን ሳያስነሳና በበደል የተዋጠችውን ምድር በፍትህ ሳይሞላት አይተዋትም።››

(አቡ-ዳውድ 4282)

ከዚህ ሐዲስ እንደምንረዳው መህዲ የነቢዩ (ዐሰወ) ቤተሰብ ነው። ስሙም የነቢዩን (ዐሰወ) እና አባታቸውን የያዘ ሲሆን ‹‹ሙሐመድ ኢብን አብዱላህ›› ወይም ‹‹አህመድ ኢብን አብዱላህ›› ነው። የሚመጣውም ዓለም በዙልም በተዋጠችበት በመጨረሻው ዘመን ሲሆን የአላህን ቃል ከፍ በማድረግ ፍትህን ያነግሳል።

ኡሙ ሰላማ (ረዐ) እንደተናገረችው ነቢዩ (ዐሰወ) ‹‹መህዲ በፋጡማ በኩል የሚገኝ ቤተሰቤ ነው።›› ብለዋል። ኢብኑል ቀይም ይሄንን ሐዲስ ሲያብራሩ ‹‹መህዲ የሐሰን ዘር ሲሆን አል-ሐሰን ለሙስሊሙ አንድነት ሲሉ ኸሊፋነታቸውን አሳልፈው በመስጠታቸው ምክንያት አላህም በመጨረሻው ዘመን ከቤተሰባቸው ታላቅ ኸሊፋ በማስነሳት ክሷቸዋል።›› ሲሉ ፅፈዋል።

(አቡ-ዳወድ 11/373)

አቡ-ሰዓድ አልኩድሪ በዘገቡት ሐዲስ ነቢዩ (ዐሰወ) ስለ መህዲ ገፅታ ሲናገሩ ‹‹ቁመቱ ረጂም፣ ትከሻው ሰፊ፣ አፍንጫው አጠፍ ያለ ነው።›› ብለዋል።

(አቡ-ዳውድ 4265)

መህዲ የሚነሳበትን ቦታ በተመለከተ የተለያዩ ዘገባዎች አሉ። ከፊሎቹ ከሻም ከፊሉ ከኹራሳን ሌላው ደግሞ ከመዲና እንደሆነ ይናገራሉ። ኢብን ከሲር የሁሉንም ሐዲሶች ጥቅል ሀሳብ ሲያስቀምጡ ‹‹የሚነሳው ከምስራቅ ነው። ከዚያም ወደ መካ ይሄዳል። ሰዎችም በከዓባ ዙሪያ ቃልኪዳን ይገቡለታል።›› ብለዋል። እንዲሁም በሌላ መጽሐፋቸው ‹‹በሐዲስ በተጠቀሰው መሰረት ባንዲራው ጥቁር ነው።›› በማለት አብራርተዋል።

(አልቢዳያህ ወልኒያህ 19/63፤ አልፊታን ወልመላሂም 1/49)

ኢማም አህመድ እንደዘገቡት መህዲ መሪነት ሲመረጥ ፍላጎቱም ክህሎቱም አልነበረውም። እናም ‹‹አላህ በአንድ ሌሊት ይመራዋል።›› ብለዋል (ዐሰወ)። ኢብን ከሲር ሐዲሱን ሲያብራሩ፡- ‹‹ይህ ማለት አላህ ይረዳዋል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረውን ችሎታም ይሰጠዋል ማለት ነው።›› ብለዋል።

(አህመድ 2/58/ አልፊታን ወልመላሂም 1/29)

መህዲ ኸሊፋነትን ከተረከበ በኋላ ሙስሊም አገራትን በአንድ በማፅናት በቀደመው ኢስላማዊ አስተዳደር ስር ያስገባቸዋል። ከዚያም በቡኻሪ እና ሙስሊም (2897) እንደተዘገበው ከሮማውያን ጋር የመጨረሻው ታላቁ ጦርነት ‹‹አል-መልሃማ አል-ኩብራ›› ይካሄዳል። ሙስሊሞችም ዳቢቅ ላይ ድል ደርጋሉ። ከዚህ በፊት ያልተከፈቱ አገራትንም ይከፍታሉ። ከዚያ በኋላ ሙስሊሞች በየትኛውም ኃይል አይሸነፉም። አላህ አማኞችን ከፍተኛ የሀብት መትረፍረፍ ይባርካቸዋል።

ሸይህ ዑመር ሱለይማን አል-አሽቀር ሐዲሱን መሰረት በማድረግ እንደተናገሩት ‹‹ይህ ጦርነት ከባድ ውድመትን ስለሚያስከትል ዓለም አሁን ካለችው ስልጣኔ ወደኋላ በመመለስ እንደ ጥንቱ በጦር በጋሻ በፈረስ መጠቀም ይጀምራሉ።›› ብለዋል።

(አል-ቂያማህ አስ-ሱግራ 275)

መህዲ ታላቅ ጦርነት አድርጎ ሙስሊሞችን የበላይ ቢያደርግም ጊዜው የቂያማህ ቀን መቃረቢያ በመሆኑ ከባባዶቹ ፊትናዎች ይከሰታሉ። ከእነዚህም መካከል ቀዳሚው የደጃል መነሳት ነው። እሱን ተከትለው የዕጁጅና መዕጁጆች ከጉድጓዳቸው ይወጣሉ። በዚህ ጊዜ አላህ ዒሳን (ዐሰ) ለእርዳታ ይልከዋል።

በሐዲስ እንደተጠቀሰው ዒሳ (ዐሰ) ወደ ምድር የሚወርደው በፈጅር ሰላት ወቅት ነው። ነቢዩ (ዐሰወ) ስናገሩ ‹‹መህዲ ዒሳን አሰግደን ይለዋል። ዒሳም እናንተ መሪዎች መሆናችሁ ከቂያማህ ምልክቱ ነውና አንተ አሰግደን ይለዋል። ዒሳም ከመህዲ ኋላ ተከትሎ ይሰግዳል።›› ብለዋል።

(ሙስሊም 225)

ከዚያ በኋላ ዒሳ ከሙስሊሞች ጋር በመሆን የዕጁጆችንና ደጃልን በመጋደል በአላህ ዕርዳታ ያጠፋቸዋል። ነቢዩ (ዐሰወ) እንደተናገሩት ‹‹ሙስሊሞች ለሰባት ዓመታት ያህል የየዕጁጆችን አጥንት ቀስትና ጋሻ ለማገዶነት ይጠቀሙበታል።

መህዲ በኸሊፋነት የሚቆይባቸው ዓመታት ‹‹ሰባት›› እንደሆኑ አብዛኛዎቹ የሐዲስ ምሁራን ይናገራሉ። ከእነሱ መካከል አንዱ የኢብኑ ማጃህ ሲሆኑ ነቢዩ (ዐሰወ) ‹‹መህዲ ሰባት አጭር ጊዜያትን ይቆያል።›› ማለታቸውን ዘግበዋል።

(ኢብን ማጃህ 4039)

አል-መህዲ እስኪመጣ ሙስሊሙ ጂሐድን በመተው መጠበቅ ይኖርበታል? ለሚለው ጥያቄ ሸይህ ሙሐመድ ሷሊህ አል-ሙነጂድ በፈትዋ ገፃቸው እንዲህ ብለዋል፡-

‹‹ከጂሐድ መዘንጋት ከከባባድ ወንጀሎች አንዱ ነው። አላህ ያዘዘው ሁሉም የራሱን ግዴታ እንዲሞላ ነው። መህዲ የራሱ ጂሐድ አለው። ይሄም ህዝብ የራሱን ጂሐድ ማድረግ ግዴታው ነው። አላህ በቁርኣኑ እንዲህ ብሏል፡-

‹‹ሁከትም እስከማትገኝ ሃይማኖትም ሁሉ ለአላህ ብቻ እስከሚሆን ድረስ ተጋደሏቸው። ቢከለከሉም አላህ የሚሰሩትን ሁሉ ተመልካች ነው።››

(አንፋል፡ 39)

Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş
7 ay Çeviri
Çeviri imkansız.

subhanelah

#ሸይኽ ኢብን ባዝ ተጠየቁ ፡ ሙቅ ውሃን በምናፈስበት ጊዜ

ቢስሚላህ እንላለንን፣ ይህም ጂን ቦታው ላይ ይኖራል ብሎ

በመፍራት ነው

መልስ፡

"አዎን! ቢስሚላህ ይበል ምን አልባት ቦታው ላይ ጂን ካለ

እንዲነቃ ለማድረግ ነው" ከዛም ሽይኹ እንዲህ አሉ" በርግጥም

በአንድ ወቅት አንድን ሰው ጂን ይዞት በሚቀራበት ቦታ ተገኝቼ

ነበር

#ሩቃ የሚያደርገው ሰው በሰውየው ላይ ለተደበቀው ጂኒ "ለምን

ያዝከው "አለው

#ጂንውም "የሞቀ ውሃ በአንዱ ልጄ ላይ ደፋና ገደለው "አለ

#የሚቀራዉ ሰውዬ ደግሞ "እሱ ልጅህ በቦታው መኖሩን

ስላላወቀ ነው" አለው

#ጂኒው ደግሞ "ለምን ቢስሚላህ አይልም ነበር እንዲያሳውቀው

(እንዲያነቃው)"

#ሽይኽ ዘይድ አል መድኸሊ ረሂምሁሏህ እንዲህ አሉ ፡

"ለማንኛውም የሞቀ ውሃ በፍሳሽ ትቦዎችም ይሁን በመሬት ላይ

አይደፋም ምክኛቱም መሬት በነዋሪዎች የተሞላች ነች

ምናልባትም በጂኖች አለም ወይም በትንንሽ ፍጡሮች ላይ ያርፋል

በዚህም ለበቀል ይነሳሱና ይይዙታል።ስለዚህ አንድ ሰው የሞቀን

ውሃ መድፋት ከፈለገ በቀዝቃዛ ውሃ ቅዝቃዘው የማያስቸግር

እስኪሆን ያብርደውከዛም ከፈለገ የፍሳሽ ትቦዎች ውስጥ ከፈለገ

መሬት ላይ ያፍሠው" ንግግራቸው እዚህ ጋር አለቀ ረሂመሁሏህ.

፟፟=========================

#ጉዳዩ አደገኛ ነው ሙስሊሞች ሆይ ነቃ በሉ ለወንድሞቻችሁ

ለእህቶቻችሁ ለእናቶቻችሁ አድርሱላቸው ስንትና ስንት እህቶች

በዚህ ሰበብ ችግር ውስት ይገባሉ ፓስታ የቀቀሉበትን ውሃ

አውጥተው በመድፋት ስንቱ ተለክፎዋል ስለዚህ አድርሱላቸው!

image
Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş
Çeviri imkansız.

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮችን ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የክብር ዶ/ር ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የአውሮፓ ኡለሞች ህብረት ዋና ፀሀፊ ጋር በቢሯቸው ተወያዩ!

...

(ሀሩን ሚዲያ፦ጥቅምት 14/2016)

...

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮችን ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የክብር ዶ/ር ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የአውሮፓ ኡለሞች ህብረት ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ፋይድ ሙሀመድ ሰኢድ ጋር በቢሯቸው ተወያይተዋል።

...

የአውሮፓ ኡለማዎች ህብረት ዋና ፀሀፊ ለስራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት እና ከፍተኛ አመራሮች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

...

በውይይታቸውም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ያለበት ሁኔታ እና ሁለቱ ተቋማት በጋራ ስለሚሰሩባቸው መንገዶች መነጋገራቸው ተገልጿል።

...

©ሀሩን ሚዲያ

image
image
Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş
Ahmedin Alemu Profil resmini değiştirdi
7 ay
Çeviri imkansız.

image
Mesaj olarak gönder
Sayfamda paylaş
Grupta paylaş