የሚጥል ህመም ያለበት ሰው ፆም
~
አንድ ፆመኛ በቀኑ ክፍለ ጊዜ ውስጥ የሆነ ያክል ሰዓት ራስን መሳት ቢያጋጥመው ፆሙ ላይ ችግር የለውም፣ ይቆጠራል። ሙሉ ቀን ራሱን ሳያውቅ ካሳለፈ ግን ፆሙ አይቆጠርም። የላቀው አላህ ፆመኛን እንዲህ ሲል ነው የገለፀው:-
يَتْرُكُ طَعَامَهُ وَشَرَابَهُ وَشَهْوَتَهُ مِنْ أَجْلِي
"ምግቡንም፣ መጠጡንም፣ ስሜቱንም ለኔ ሲል ይተዋል።" [አልቡኻሪይ፡ 1894] [ሙስሊም፡ 1151
ሙሉ ቀን ራሱን የማያውቅ ሰው እዚህ ኒያ ውስጥ የለም።
ስለዚህ ሲሻለው ሌላ ጊዜ ቀዷእ ያወጣል። ማስረጃው አላህ እንዲህ ማለቱ ነው:-
{فَمَن كَانَ مِنكُم مَّرِیضًا أَوۡ عَلَىٰ سَفَرࣲ فَعِدَّةࣱ مِّنۡ أَیَّامٍ أُخَرَۚ}
"ከእናንተም ውሰጥ ህመምተኛ ወይም በጉዞ ላይ የሆነ ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን መፆም አለበት።" [አልበቀረህ: 184]
የሚጥል በሽታ ያለበት አካል በፆሙ ክፍለ ጊዜ መድሃኒት የሚወስድ ከሆነ እንዴት ያድርግ? በሰሑር እና ፊጥራ ሰዓት ላይ አመቻችቶ መድሃኒቱን የሚወስድበት አማራጭ ካለው መፆም ግዴታው ነው። በየ 12 ሰዓቱ የሚወሰደውን መድሃኒት በዚህ መልኩ የሚወስዱ አሉ። መጀመሪያ ሰሞን ከሚሰማ ስሜት ውጭ ከቆይታ በኋላ `ኖርማል' ይሆናል ይላሉ። ሰዓቱን በትክክል ጠብቆ ባይወስድ ጉዳት የሚኖረው ከሆነ ግን ማፍጠር ይገባል። ምክንያቱም አላህ እንዲህ ይላል፦
{فَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ مَا ٱسۡتَطَعۡتُمۡ}
"አላህንም የቻላችሁትን ያክል ፍሩት።" [አተጋቡን: 16]
ስለዚህ ከውሳኔ በፊት ታማኝና ብቁ ሃኪም ማማከርና ምክረ ሃሳቡን መውሰድ ይገባል።
በመድሃኒቱ ሰበብ ያፈጠረ ሰው ህክምናውን ሲያጠናቅቅ ቀዷእ ያወጣል። ህመሙ ቋሚ ከሆነ ወይም ቀዷእ ለማውጣት በሚከብድ መጠን ብዙ አመታትን የሚወስድ ከሆነ ለእያንዳንዱ ቀን አንዳንድ ምስኪን ማብላት ይችላል። ወሏሁ አዕለም።
=
ቴሌግራም:-
https://t.me/IbnuMunewor
የሚጥል ህመም ያለበት ሰው ፆም
~
አንድ ፆመኛ በቀኑ ክፍለ ጊዜ ውስጥ የሆነ ያክል ሰዓት ራስን መሳት ቢያጋጥመው ፆሙ ላይ ችግር የለውም፣ ይቆጠራል። ሙሉ ቀን ራሱን ሳያውቅ ካሳለፈ ግን ፆሙ አይቆጠርም። የላቀው አላህ ፆመኛን እንዲህ ሲል ነው የገለፀው:-
يَتْرُكُ طَعَامَهُ وَشَرَابَهُ وَشَهْوَتَهُ مِنْ أَجْلِي
"ምግቡንም፣ መጠጡንም፣ ስሜቱንም ለኔ ሲል ይተዋል።" [አልቡኻሪይ፡ 1894] [ሙስሊም፡ 1151
ሙሉ ቀን ራሱን የማያውቅ ሰው እዚህ ኒያ ውስጥ የለም።
ስለዚህ ሲሻለው ሌላ ጊዜ ቀዷእ ያወጣል። ማስረጃው አላህ እንዲህ ማለቱ ነው:-
{فَمَن كَانَ مِنكُم مَّرِیضًا أَوۡ عَلَىٰ سَفَرࣲ فَعِدَّةࣱ مِّنۡ أَیَّامٍ أُخَرَۚ}
"ከእናንተም ውሰጥ ህመምተኛ ወይም በጉዞ ላይ የሆነ ሰው ከሌሎች ቀኖች ቁጥሮችን መፆም አለበት።" [አልበቀረህ: 184]
የሚጥል በሽታ ያለበት አካል በፆሙ ክፍለ ጊዜ መድሃኒት የሚወስድ ከሆነ እንዴት ያድርግ? በሰሑር እና ፊጥራ ሰዓት ላይ አመቻችቶ መድሃኒቱን የሚወስድበት አማራጭ ካለው መፆም ግዴታው ነው። በየ 12 ሰዓቱ የሚወሰደውን መድሃኒት በዚህ መልኩ የሚወስዱ አሉ። መጀመሪያ ሰሞን ከሚሰማ ስሜት ውጭ ከቆይታ በኋላ `ኖርማል' ይሆናል ይላሉ። ሰዓቱን በትክክል ጠብቆ ባይወስድ ጉዳት የሚኖረው ከሆነ ግን ማፍጠር ይገባል። ምክንያቱም አላህ እንዲህ ይላል፦
{فَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ مَا ٱسۡتَطَعۡتُمۡ}
"አላህንም የቻላችሁትን ያክል ፍሩት።" [አተጋቡን: 16]
ስለዚህ ከውሳኔ በፊት ታማኝና ብቁ ሃኪም ማማከርና ምክረ ሃሳቡን መውሰድ ይገባል።
በመድሃኒቱ ሰበብ ያፈጠረ ሰው ህክምናውን ሲያጠናቅቅ ቀዷእ ያወጣል። ህመሙ ቋሚ ከሆነ ወይም ቀዷእ ለማውጣት በሚከብድ መጠን ብዙ አመታትን የሚወስድ ከሆነ ለእያንዳንዱ ቀን አንዳንድ ምስኪን ማብላት ይችላል። ወሏሁ አዕለም።
=
ቴሌግራም:-
https://t.me/IbnuMunewor