UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ግንኙነት ያልተፈፀመበት ኒካሕ

~

አንድ ሰው አንዲትን ሴት ኒካሕ አድርጎ ካገባ በኋላ ነገር ግን በመሃላቸው ግንኙነት ሳይፈፀም ከፈታት ፤ ለምሳሌ የተለያየ ሃገር እየኖሩ ኒካሕ ከታሰረ በኋላ ሳይገናኙ ፍቺ ቢፈፅም ዒዳ የለባትም። ምክንያቱም አላህ እንዲህ ብሏልና፦

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آَمَنُوا إِذَا نَكَحْتُمُ الْمُؤْمِنَاتِ ثُمَّ طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِنْ قَبْلِ أَنْ تَمَسُّوهُنَّ فَمَا لَكُمْ عَلَيْهِنَّ مِنْ عِدَّةٍ تَعْتَدُّونَهَا فَمَتِّعُوهُنَّ وَسَرِّحُوهُنَّ سَرَاحًا جَمِيلًا

{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ምእምናትን ባገባችሁና ከዚያም ሳትነኳቸው በፊት በፈታችኋቸው ጊዜ ለእናንተ በእነርሱ ላይ የምትቆጥሯት ዒዳ ምንም የላችሁም፡፡ አጣቅሟቸውም፤ (ጉርሻ ስጧቸው)፡፡ መልካም ማሰናበትንም አሰናብቷቸው፡፡} [አል አሕዛብ፡ 49]

* ይሄ ጉዳይ የዑለማእ ኢጅማዕ ያለበት ነው።

ማሳሰቢያ፦

* ዳግም ማግባት ከፈለገ መስፈርቱን ያሟላ አዲስ ኒካሕ ማሰር እንጂ እንዲሁ መልሻለሁ ብሎ መመለስ አይችልም።

* ለመመለስ ሌላ አግብታ መፈታቷ ሸርጥ አይደለም። ሌላ አግብታ የተፈታች ባይሆንም ማግባት ይችላል። ነገር ግን የባለፈው ፍቺ አንድ ተብሎ ይቆጠራል። ስለዚህ ሁለት ኒካሕ ነው የሚቀረው ማለት ነው።

.

በፍቺ ሳይሆን በሞት ከተለየ ግን የዒዳው ብይን ይለያል። ማለትም ኒካሕ ታስሮ ግንኙነት ሳይፈፀም በፊት ባል ከሞተ አራት ወር ከ 10 ቀን ዒዳ ትቆጥራለች። ከንብረቱም ትወርሳለች። ሙሉ መህሯንም ትወስዳለች። የመህሯ መጠን ቀድሞ ያልተወሰነ ከሆነ የአምሳያዎቿ መህር ታሰቦ ይሰጣታል።

=

የቴሌግራም ቻናል፡-

https://t.me/IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

كناشة ابن منور
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ከትዳር በፊት ፍቅር የለም ብዬ የኸዲጃን ፍቅር ገደል አልከተውም… ምክንያቱ ምንም ይሁን አፍቅራ እንዳገባቻቸው አልጠራጠርም… በሪራ በሚሏት ሰሓቢት ፍቅር ተለክፎ በመዲና መንገዶች ላይ ከኋላዋ እየተከተለ… የእንባ ቋንጣውን በመዲና አድማስ ሲወረውር የነበረውን ሰሓባው ሙጊስ … አፍቃሪ አልነበርክም ልለው አልችልም… ቀድመው ቢለያዩና ከዚያ በኋላ ባያገባትም “ሙጊስ ለበሪራ ባለው ፍቅር፣ በሪራ ደግሞ ለሙግስ ባላት ጥላቻ አልተገረምክም ወይ” የተባለለት አፍቃሪ ነው… ያውም በረሱል አንደበት።

አንድ ነገር ግን አምናለሁ… ፍቅር በስሙ የሚደረጉ ኃጥያቶችን እንደማያውቃቸውና የአፍቃሪ መድሀኒቱም ትዳር እንደሆነ… ማንነትህን ፣ እምነትህንና ጉዞህን የሚያመክንብህ ከሆነ በሽታ እንደሆነ… አምናለሁ። ነብይህ “ለተዋደዱ ሰዎች ከኒካህ ውጪ (አማራጭ) አላየሁም” ሲሉም… ከትዳር በፊት መዋደድ እንዳለና ኒካህ ካልታከለበት ግን የኪሳራ መንገድ ሊሆን እንደሚችል ነው… አፍቅርሃል? በበር በኩል ና በቃ … በፍቅር ስም ሙድ አትያዝ!!

t.me/abdu_rheman_aman

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እየተማማራችሁ»አስተምሪዉ አስተምራት

እንደኔ ግን በሁሉም ወንድ ልጅ ሲበልጥ ነዉ የሚል አቋም አለኝ\"በተለይ በዚህ ቁፅል እዉቀትና ኢማን በሆነበት ጊዜ,~~

ግንኮ ስንትና ስንት እንቁ ሴቶችም አልፈዋል!

~~

የሰዒድ ኢብኒል ሙሰየብ ሴት ልጅ ከአባቷ የያዘቺው ጥሩ የሚባል ዒልም ነበራትና

ያገባችውም ከአባቷ ሰኢድ ኢብኒል ሙሰየብ ደረሶች ውስጥ አንዱን ነበር በተጋቡም ከተወሰኑ ቀናቶች በኋላ ደረሳ ባልዋ ኩታውን ደርቦ ከቤት ሊወጣ ሲል ሚስት ወደት ልትሄድ ነው? ብላ ትጠይቀዋለች እርሱም ወደ አባትሽ የቂርዓት ቦታ በሚል መለሰላት\"

እሷም አትሂድ\"ተቀመጥ እኔ አባቴ የሚያስተምርህን ዒልም አስተምርሃለው በማለት አስቀረችዉ!!

[مصدر من الكتاب المدخل لابن الحاج ١/٢١٥]

https://t.me/+JILwkIarUT40YjFk

Telegram: Join Group Chat

Telegram: Join Group Chat

https://t.me/+JILwkIarUT40YjFk كُن نافعاً ولو بِالنية فإن الله إذا رأى فيك خيراً ، يسّرك للخير تَمَسَّكْ بِحَبْلِ اللهِ وَاتَّبِعِ الهُدَى ....
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

\" ፍቅር \"\"\"\"

-------

በመሰረቱ \" ማፍቀር \" ለጤነኛና ሰናይ ህሊና ባለቤቶች የተቸረ ታላቅና ውብ ፀጋ ነው ፡፡

በመብላት በመጠጣት እንዲሁም ሌሎች \" መዝናኛ \" ብለን የምንቆጥራቸውን ተግባራት ለአመታት በመፈፀማችን የማናገኘውን ደስታ የሰከንዶች እድሜ በሌለው የፍቅር ስሜት መሸመት እንችላለን ፡፡

ፍቅር ከአላህ ዘንድ የሆነ ታላቅ ተዐምርም ነው ፡፡ ይህንንም \" ወዱዱ \" ጌታችን በመጠቀው ቃሉ እንዲህ ሲል ገልፆታል።

■ وَمِنْ آَيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُمْ مِنْ أَنْفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُمْ مَوَدَّةً وَرَحْمَةً إِنَّ فِي ذَلِكَ لَآَيَاتٍ لِقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ [ الروم : 21 ] ■

ለእናንተ ከነፍሶቻችሁ ሚስቶችን ትረኩ ዘንድ መፍጠሩ ፥ በመካከላችሁም ፍቅርንና እዝነት ማድረጉ ከአስደናቂ ምልክቶቹ ናቸው፡፡ ■ [ ሱ - ሩም 21 ]

ፍቅር እጅግ በጣም የነፃ ውብ መሃረብ ( ጨርቅ ) ነው ፡፡ ይህን ነጭ ጨርቅ በአደፈ ( በቆሸሸ ) እጃችን ለመያዝ ከሞከርን የጨርቁን ውበትና ንፅህና እናጎድፈዋለን !

በተመሳሳይ ንፁህ ልብና ቅን ህሊናን ሳይዪዙ ወደ ፍቅር ዐለም ሰተት ማለት የተዋበውን ፍቅርን ልክ እንደ ነጩ ጨርቅ ማደክርት ይሆናል ፡፡

ምክንያቱም ፍቅርን \" በፍቅር \" መያዝና ተንከባክበው ማቆየት የሚቻላቸው የንፁህ ልብና የብሩህ ህሊና ባለቤቶች ብቻ ናቸው ፡፡ ስለዚህም ወደዚህ ድንቅና ውብ አለም ( ወደ ፍቅር ) ከመግባታችን በፊት ልባችንና ህሊናችንን ልናፀዳ የግድ ይላል ፡፡

ሌላው ደግሞ ፍቅር ውድ ነውና ተልካሻና ርካሽ ቦታ ሊቀመጥ አይገባውም ፡፡ፍቅር በዘላቂነት እንዲቆይልን ብሎም ትክክለኛ ጣዕሙንና ጥፍጥናውን ይቸረን ዘንዳ \" ያማረ ማስቀመጫ \" ይፈልጋል ፡፡

ምን ማለት ነው

ፍቅርን ሳይበላሽ ማቆየት የሚችለውና ባማረና በጣፈጠ መልኩ ማቅረብ የሚችለው .... \" ሀላል የሆነ ኒካህ \"..... ብቻ ነው ! ከዚህ ውጪ በሆነ መልኩ የሚጠነሰስ የፍቅር እንቅስቃሴ ጣፋጭ መሳይ ነገር ግን እጅግ ጎምዛዛና ዘለቄታም የሌለው ስለሆነ ህሊና ላይ የማይሽር ጠባሳንም አሳርፎ ያልፋልና .... \" እራቁት \"...... !

ወንድሞችና እህቶች ጊዜያዊ ጣፋጭ መሳይ መራራ ገፈትን ...\" በሀራም ፍቅር \".... መቀማመሱን ትታችሁ መሰላቸት የሌለበትንና ዘላቂነትን የተላበሰውን ....\" ሀላሉን ፍቅር ጠብቁት ፤ ስታገኙትም አንቃችሁ 👀ያዙት \".....

-

በተረፈ .....,

ፍቅር ጣፋጭ ነው = አጣጥሙት

ፍቅር ህይወት ነው = ኑሩት

ፍቅር መስወዐትነት ነው = ሙቱለት 44.

በቃ ባካችሁ ፍቅር ፍቅር ነው = አፍቅሩት

_\"\"\"\"\"\"\"\"\"\"ካነበብኩት!!

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ልጅህን አባት ያለው የቲም አታድርገው!

~

ልጆች ከአላህ የተሰጡ አማናዎች ናቸው። አማናን ባግባቡ አለመጠበቅ ነውር ነው። ዘመኑ እንደምናየው ከባድ ነው። የልጆችን ህይወት የሚያበላሹ ነገሮች በጣም በዝተዋል። የአደጋ ስጋት ሲጨምር ጥንቃቄያችን መጨመር ነበረበት። እኛ ግን ይበልጥ እየተዘናጋን ነው። በገዛ ገንዘብህ፣ እጅህ ላይ ባለው ሞባይል፣ ቤትህ ውስጥ ባለው ቴሌቪዥን ልጆችህን እያጠፋሃቸው እንዳይሆን ተጠንቀቅ። ልጅህ ልጅ ነው። የነገ ህይወቱን ሳይሆን የዛሬ ደስታውን ነው የሚያየው። ቅፅበታዊ ኩርፊያውን ፈርተህ፣ የእለት ደስታውን ብቻ እያየህ የጠየቀውን ሁሉ አትስጥ። የሚያስፈልገውን እንጂ የሚፈልገውን ሁሉ አታድርግ።

ትንፋሽ እስከሚያጣ አስጨንቀው እያልኩህ አይደለም። ግን ዛሬ ቁርኣን ካልቀራ፣ ዲኑን ካላወቀ፣ ትምህርት ካልተማረ መቼ ሊማር ነው? አባትነት ልጆችን ቆፍጠን ብሎ በስርአት ለማሳደግ ካልሆነ ምን የረባ ትርጉም አለው? አኺራውንም ይሁን ዱንያውን በተመለከተ ስለ ነገ ህይወቱ አንተ ካልተጨነቅክለት ማን ይጨነቅለት? አባትነትህ ለዚህ ካልሆነ ለምን ይሁን?

ስለ ልጅህ ስታስብ ልብሱና ጉርሱ ላይ አትቁም። ነጣ ገረጣ፣ ከሳ ኮሰሰ፣ ሳቀ አኮረፈ ላይ ብቻ አታተኩር። \"ለነገ ምን ይዟል?\" በል። ለሃላፊነት አዘጋጀው። ህይወት ከባድ ትምህርት ቤት ናት። ብዙ መውጣት መውረድ አላት። ነገ ምን እንደሚገጥመው አታውቅም። ሁሌ አብረኸው አትሆንም። ብትሆንም አቅምህ ውስን ናት። ጥገኝነትን አታለማምደው። ካንተ የተሻለ እንጂ ያነሰ እንዲሆን አትተወው። ከመስመር ወጥቶ ከሆነ በጊዜ ወደ ቦዩ መልሰው።

ይጫወት ፋታ ስጠው። ግና ቁም ነገረኝነትን አስተምረው። ያለበለዚያ አካሉ ቢያድግም ከልጅነት ስነ ልቦና አይወጣም። በሰላሳ አመቱም የሰው እጅ የሚጠብቅ ጥገኛ ይሆናል። ሌሎችን በሚጦርበት እድሜው ተዘፍዝፎ በአዛውንቶች ይጦራል። ከእህቱ እየነጠቀ ሱስ የሚያሳድድ ጅል ፈጥረት ይሆናል።

ባጭሩ ለልጅህ የእውነት አባት ሁነው። ከልብ አንፀው። መኖርህ በልጅህ አስተዳደግ ላይ ትርጉም ያለው ልዩነት ይኑረው። ልጅህን በአደብ፣ በእውቀት ተከትኩቶ እንዲያድግ ካላገዝከው በህይወት እያለህ የቲም አድርገኸዋል። የአባትን መኖር ትርጉም ነፍገኸዋል። የምታሳድገው ልጅ የቤተሰብ ማፈሪያ፣ የማህበረሰብ እዳ፣ የሃገር ሸክም ከሆነ በሃገርም በወገንም ላይ ትልቅ በደል ነው የፈፀምከው። ይሄ ህዝብ ጀርባውን ያጎበጠው ብዙ ሸክም አለበት። ሌላ ሸክም አትጨምርበት። ለራስህም ቢሆን ነገ በፀፀት እጅህን ከመንከስህ በፊት ዛሬ ሃላፊነትህን ባግባቡ ተወጣ። አባት ሁን። አባት!

=

የቴሌግራም ቻናል፡-

https://t.me/IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

كناشة ابن منور
Send as a message
Share on my page
Share in the group