የሚያሳክማቸው / የሚያስራቸው ዘመድ ያጡ ወሊዮች
~
ጀ^ዝ ^ባ የሚለው ቃል ከዐረብኛው جذبة የተወሰደ ነው። جَذْبَة ማለት ሱፊያዊ ወፈፌነት ማለት ነው። ስለዚህ ጀ^ዝ ^ባ እና መጅዙብ ማለት ንክ የሆነ ወይም ወፈፍ ያደረገው፣ ቀውስ ማለት ነው። ጀዝ *ባነት በሱፊያው ዓለም አንድ የወሊይነት ደረጃ ነው። በዚህ የተነሳ ነው ብዙ ቀ -ውስ ወሊዮች ያሉት። ያው በወሊይነት የሚያምኑባቸው ማለቴ ነው። አንዳንዶቹ ይህንን የወሊይነት ደረጃ ዝቅ ያለ እንደሆነ ሲገልፁ ሌሎች ደግሞ በጣም አግንነው ያስቀምጡታል። ለምሳሌ ያህል ሸህረስታኒይ እንዲህ ይላል፦
ادعت طائفة من الصوفية أن في أولياء الله تعالى من هو أفضل من جميع الأنبياء والرسل، وقالوا: من بلغ الغاية القصوى من الولاية سقطت عنه الشرائع كلها من الصلاة والصيام والزكاة وغير ذلك، وحلت له المحرمات كلها من الزنا والخمر وغير ذلك، واستباحوا بذلك نساء غيرهم
"ከሱፊያ ውስጥ የሆነው ክፍል ከአላሁ ተዓላ ወሊዮች ውስጥ ከሁሉም ነብያትና መልእክተኞች የሚበልጡ አሉ ብሎ የሞገተ አለ። እናም \'የወሊይነትን የመጨረሻ ጥግ የደረሰ ሰው ሶላት፣ ፆም፣ ዘካና ሌሎችም የሸሪዐ ድንጋጌዎች በሙሉ ይወድቁለታል፣ ዝሙት፣ አስካሪ መጠጥና ሌሎችም ሐራም ነገሮችም ይፈቀዱታል\' ይላሉ። በዚህ የተነሳ የሌሎች ሰዎችን ሚስቶች ለራሳቸው ሐላል አድርገዋል።" [አልሚለል ወኒሐል፡ 226]
ልብ በሉ! ምንጭ ጠቅሻለሁ። ሰውየው በሱፊያና አሽዐሪያው ዓለም የሚታመን ነው። በሃገራችንም በርካታ እንዲህ አይነት ጀ^ዝ ^ባ እና ባ-ለ -ጌ ወልዮች ነበሩ። ለነገሩ ዐቅሉን የሳተ ሰው ቢሰግድስ ምን ትርጉም አለው? ሲጀመር ጦሀራ የለው!
ታዋቂው ሱፊይ ዐብዱልወሃብ ሸዕራኒይ እንዲህ ይላል፦
المجاذيب: هم قوم سلب الله قلوبهم عن التعشق بشيء من الأكوان، وجعلها عاكفة في حضرته، لا يشهدون إلا إياه، فإن شاء الله تعالى ردهم إلى عقل التكليف، وان شاء خبأ عقولهم عنده
"ጀ^ዝ ^ባዎች ማለት ከፍጥረቶች ውስጥ የትኛውንም እንዳይወዱ አላህ ልቦናቸውን የነጠቃቸውና እሱ ዘንድ እንዲጣዱ ያደረጋቸው ሰዎች ናቸው። እሱን እንጂ አይመለከቱም። የላቀው አላህ ከሻ ኃላፊነትን መፈፀም ወደሚችሉበት አእምሮ ይመልሳቸዋል። ከፈለገ ደግሞ አእምሮዎቻቸውን እሱ ዘንድ ይደብቃል።"
ምን ሆነው ቀ -ወሱ የሚለውን ሸዕራኒይ ይጨነቅበት። ብቻ ሰዎቹ 0ቅል የላቸውም ያለበትን ያዙልኝ።
ሌላኛው ሱፊይ ነብሃን ደግሞ እንዲህ ብሏል፦
المجذوب له صفات ثلاث: عقله صغير، نفسه كبيرة، قلبه طاهر، وهو غير مكلف، المجاذيب لا يحملون سراً
"መጅ -ዙብ ሶስት መታወቂያዎች አሉት። ዐቅሉ ትንሽ ነው። ነፍሱ ትልቅ ነው። ልቡ ንፁህ ነው። እሱ ደግሞ ኃላፊነት (ዒባዳ) ግዴታ የሆነበት አይደለም። ቀ -ው -ሶች ሚስጥር መያዝ አይችሉም።"
አስተውሉ!
1ኛ፦ ዐቅሉ ትንሽ ናት ሲል ያው ጤና ስለሚጎድለው የሚሰራውን አያውቅም ማለቱ ነው። ይህንን ዐቅለ ቢስ ወሊይ አስቡ እንግዲህ። በዚህ የተነሳ እንደ በደዊይ መስጂድ ውስጥ ሽንቱን ሊሸና ይችላል። ውሸት ከመሰለህ የሰኻዊይን አዶውኡ ላሚዕ ኪታብ 9ኛ ቅፅ ገፅ፡ 150 ተመልከት።
2ኛ፦ ሚስጥር አይዝም ብሏል። ዐቅል የሌለው ሰው ምን ሚስጥር ያውቃል?!
3ኛ፦ "ሙከለፍ አይደለም" ማለትም ኃላፊነት (ዒባዳ) ግዴታ የሆነበት አይደለም የሚለው ምክንያቱ ግልፅ ነው። የትኛውም ዒባዳ በእ -ብ-ድ ላይ ግዴታ እንዳልሆነ በሐዲሥ የተረጋገጠ ሐቅ ነው። ችግሩ ግን ብዙ የሱፊያ ወሊዮች አውቆ አበ -ድ ናቸው። ከተክሊፍ (ከተጠያቂነት) ነፃ የሚኮንበት የወሊይነት ደረጃ ደርሰናል በማለት አውቀው ሶላትና ፆም ይተዋሉ። አስካሪ መጠጥ ሊጠጡና ብል -ግና ሊፈፅሙ ይችላሉ።
በአለማቀፍ ደረጃ ስማቸው ከገነኑ የሱፊያ ወልዮች ውስጥ አንዱ አሕመደል በደዊይ ነው። በደዊይ በያመቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ቀብሩን ይጎበኛል። ምን አይነት ሰው ነበር? መጅዙብ ነበር፣ የቀወ -ሰ። ምንጭ ልጥቀስ፡
ዐብዱሶመድ ዘይኑዲን አልአሕመዲይ ስለ በደዊይ እንዲህ ይላል፦
وأقام على سطح الدار لا يفارقه ليلًا ولا نهارًا، وإذا عرض له الحال يصيح صياحًا متصلًا، وتزيَّى أحمد البدوي بزي المجاذيب، وظل ضاربًا اللثامين على وجهه، وكان إذا لبس ثوبًا أو عمامة لا يخلعها لغسل حتى تذوب، فيبدلونها بغيرها
" በቤቱ ጣራ ላይ ኑሮውን አደረገ። ሌትም ቀንም ከሱ አይለይም። ሓሉ ሲነሳበት ረጅም ጩኸት ይጮሃል። አሕመደል በደዊይ የወፈ -ፌዎችን ገፅታ የተላበሰ ነበር። ፊቱ ላይ መከናነቢያ እንዳደረገ ነበር የሚቆየው። ቀሚስ ወይም ጥምጣም ሲለብስ ላዩ ላይ (ቆሻሻው) እስከሚቀልጥ ድረስ አያወልቅም ነበር። ሰዎች ናቸው በሌላ የሚቀይሩለት።" [አሰዪዱል በደዊይ ዲራሳህ ነቕዲያህ፡ 15]
وكان يمكث طوال نهاره وليله قائمًا شاخصًا ببصره إلى السماء، وقد انقلب سواد عينيه بحمرة تتوقد كالجمر، وكان يمكث الأربعين يومًا وأكثر لا يأكل ولا يشرب ولا ينام
"ቀንና ሌቱን ሙሉ አይኑን ወደ ሰማይ አፍጥጦ ነበር የሚቆየው። የአይኑ ጥቁሩ ክፍል እንደ ፍም የሚንቀለቀል ቀይ ሆኖ ተቀይሮ ነበር። አርባ ቀን ሳይበላ፣ ሳይጣጣ፣ ሳይተኛ ይቆያል።" [ዳኢረቱል መዓሪፊል ኢስላሚያህ: 2/476]
ኢንሷፍ!
ሁሉም ሱፊዮች እንዲህ ናቸው ማለቴ አይደለም። ነገር ግን በተለይ በዚህ ዘመን ያሉ ሱፊዮች እንዳለ እነዚህን ጀ *ዝ -ባዎች በደፈናው ካልሆነ በስተቀር አያወግዙም። አብዛኞቹ እነ አቡ የዚድ አልቢስጧሚን፣ እነ ሐላጅን፣ ኢብኑ ሰብዒንን፣ ኢብኑ ዐረቢን፣ ኢብኑ ፋሪድን፣ በደዊይን፣ ቁነዊይን፣ ቲልሚሳኒይን፣ ሻዚሊይን፣ ጀላሉዲን ሩሚን፣ ሪፋዒይን፣ ... ሲያወድሱ ነው የሚታወቁት። ማረጋገጥ ከፈለግክ የሙሐመድ አወልን መንዙማ ማዳመጥ ትችላለህ። የዚህን ሰው ኮተት የሚያደንቁትንም እዚሁ ውስጥ አስባቸው። ሺርክ የማይጎረብጣቸው ፍጡሮች ናቸው።
.
"እስራኤላዊው" የሁዲ ሃጋይ ኤርሊች "ለኢትዮጵያ የሚያስፈልገው እስልምና አሕ. ባሽ ነው" ሲል እንዲህ አይነቱን የጀዝ * ባዎች መንገድ ማለቱ ነው። እነ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ዘመድኩን በቀለ፣ አባይነህ ካሴ፣ ...ለአሕ * ባሽ የሚወግኑት ያለ ምክንያት አይምሰልህ።
* "በምስሉ ላይ ያለው ሰው ምን እየሰራ ነው?" እንዳትሉ! "ምነው አይባልም የወልይ ነገርi"
=
( Ibnu Munewor ፣ ሸዋል 18/1444 (ሚያዚያ 30/ 2015 ))
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
የሚያሳክማቸው / የሚያስራቸው ዘመድ ያጡ ወሊዮች
~
ጀ^ዝ ^ባ የሚለው ቃል ከዐረብኛው جذبة የተወሰደ ነው። جَذْبَة ማለት ሱፊያዊ ወፈፌነት ማለት ነው። ስለዚህ ጀ^ዝ ^ባ እና መጅዙብ ማለት ንክ የሆነ ወይም ወፈፍ ያደረገው፣ ቀውስ ማለት ነው። ጀዝ *ባነት በሱፊያው ዓለም አንድ የወሊይነት ደረጃ ነው። በዚህ የተነሳ ነው ብዙ ቀ -ውስ ወሊዮች ያሉት። ያው በወሊይነት የሚያምኑባቸው ማለቴ ነው። አንዳንዶቹ ይህንን የወሊይነት ደረጃ ዝቅ ያለ እንደሆነ ሲገልፁ ሌሎች ደግሞ በጣም አግንነው ያስቀምጡታል። ለምሳሌ ያህል ሸህረስታኒይ እንዲህ ይላል፦
ادعت طائفة من الصوفية أن في أولياء الله تعالى من هو أفضل من جميع الأنبياء والرسل، وقالوا: من بلغ الغاية القصوى من الولاية سقطت عنه الشرائع كلها من الصلاة والصيام والزكاة وغير ذلك، وحلت له المحرمات كلها من الزنا والخمر وغير ذلك، واستباحوا بذلك نساء غيرهم
"ከሱፊያ ውስጥ የሆነው ክፍል ከአላሁ ተዓላ ወሊዮች ውስጥ ከሁሉም ነብያትና መልእክተኞች የሚበልጡ አሉ ብሎ የሞገተ አለ። እናም 'የወሊይነትን የመጨረሻ ጥግ የደረሰ ሰው ሶላት፣ ፆም፣ ዘካና ሌሎችም የሸሪዐ ድንጋጌዎች በሙሉ ይወድቁለታል፣ ዝሙት፣ አስካሪ መጠጥና ሌሎችም ሐራም ነገሮችም ይፈቀዱታል' ይላሉ። በዚህ የተነሳ የሌሎች ሰዎችን ሚስቶች ለራሳቸው ሐላል አድርገዋል።" [አልሚለል ወኒሐል፡ 226]
ልብ በሉ! ምንጭ ጠቅሻለሁ። ሰውየው በሱፊያና አሽዐሪያው ዓለም የሚታመን ነው። በሃገራችንም በርካታ እንዲህ አይነት ጀ^ዝ ^ባ እና ባ-ለ -ጌ ወልዮች ነበሩ። ለነገሩ ዐቅሉን የሳተ ሰው ቢሰግድስ ምን ትርጉም አለው? ሲጀመር ጦሀራ የለው!
ታዋቂው ሱፊይ ዐብዱልወሃብ ሸዕራኒይ እንዲህ ይላል፦
المجاذيب: هم قوم سلب الله قلوبهم عن التعشق بشيء من الأكوان، وجعلها عاكفة في حضرته، لا يشهدون إلا إياه، فإن شاء الله تعالى ردهم إلى عقل التكليف، وان شاء خبأ عقولهم عنده
"ጀ^ዝ ^ባዎች ማለት ከፍጥረቶች ውስጥ የትኛውንም እንዳይወዱ አላህ ልቦናቸውን የነጠቃቸውና እሱ ዘንድ እንዲጣዱ ያደረጋቸው ሰዎች ናቸው። እሱን እንጂ አይመለከቱም። የላቀው አላህ ከሻ ኃላፊነትን መፈፀም ወደሚችሉበት አእምሮ ይመልሳቸዋል። ከፈለገ ደግሞ አእምሮዎቻቸውን እሱ ዘንድ ይደብቃል።"
ምን ሆነው ቀ -ወሱ የሚለውን ሸዕራኒይ ይጨነቅበት። ብቻ ሰዎቹ 0ቅል የላቸውም ያለበትን ያዙልኝ።
ሌላኛው ሱፊይ ነብሃን ደግሞ እንዲህ ብሏል፦
المجذوب له صفات ثلاث: عقله صغير، نفسه كبيرة، قلبه طاهر، وهو غير مكلف، المجاذيب لا يحملون سراً
"መጅ -ዙብ ሶስት መታወቂያዎች አሉት። ዐቅሉ ትንሽ ነው። ነፍሱ ትልቅ ነው። ልቡ ንፁህ ነው። እሱ ደግሞ ኃላፊነት (ዒባዳ) ግዴታ የሆነበት አይደለም። ቀ -ው -ሶች ሚስጥር መያዝ አይችሉም።"
አስተውሉ!
1ኛ፦ ዐቅሉ ትንሽ ናት ሲል ያው ጤና ስለሚጎድለው የሚሰራውን አያውቅም ማለቱ ነው። ይህንን ዐቅለ ቢስ ወሊይ አስቡ እንግዲህ። በዚህ የተነሳ እንደ በደዊይ መስጂድ ውስጥ ሽንቱን ሊሸና ይችላል። ውሸት ከመሰለህ የሰኻዊይን አዶውኡ ላሚዕ ኪታብ 9ኛ ቅፅ ገፅ፡ 150 ተመልከት።
2ኛ፦ ሚስጥር አይዝም ብሏል። ዐቅል የሌለው ሰው ምን ሚስጥር ያውቃል?!
3ኛ፦ "ሙከለፍ አይደለም" ማለትም ኃላፊነት (ዒባዳ) ግዴታ የሆነበት አይደለም የሚለው ምክንያቱ ግልፅ ነው። የትኛውም ዒባዳ በእ -ብ-ድ ላይ ግዴታ እንዳልሆነ በሐዲሥ የተረጋገጠ ሐቅ ነው። ችግሩ ግን ብዙ የሱፊያ ወሊዮች አውቆ አበ -ድ ናቸው። ከተክሊፍ (ከተጠያቂነት) ነፃ የሚኮንበት የወሊይነት ደረጃ ደርሰናል በማለት አውቀው ሶላትና ፆም ይተዋሉ። አስካሪ መጠጥ ሊጠጡና ብል -ግና ሊፈፅሙ ይችላሉ።
በአለማቀፍ ደረጃ ስማቸው ከገነኑ የሱፊያ ወልዮች ውስጥ አንዱ አሕመደል በደዊይ ነው። በደዊይ በያመቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ቀብሩን ይጎበኛል። ምን አይነት ሰው ነበር? መጅዙብ ነበር፣ የቀወ -ሰ። ምንጭ ልጥቀስ፡
ዐብዱሶመድ ዘይኑዲን አልአሕመዲይ ስለ በደዊይ እንዲህ ይላል፦
وأقام على سطح الدار لا يفارقه ليلًا ولا نهارًا، وإذا عرض له الحال يصيح صياحًا متصلًا، وتزيَّى أحمد البدوي بزي المجاذيب، وظل ضاربًا اللثامين على وجهه، وكان إذا لبس ثوبًا أو عمامة لا يخلعها لغسل حتى تذوب، فيبدلونها بغيرها
" በቤቱ ጣራ ላይ ኑሮውን አደረገ። ሌትም ቀንም ከሱ አይለይም። ሓሉ ሲነሳበት ረጅም ጩኸት ይጮሃል። አሕመደል በደዊይ የወፈ -ፌዎችን ገፅታ የተላበሰ ነበር። ፊቱ ላይ መከናነቢያ እንዳደረገ ነበር የሚቆየው። ቀሚስ ወይም ጥምጣም ሲለብስ ላዩ ላይ (ቆሻሻው) እስከሚቀልጥ ድረስ አያወልቅም ነበር። ሰዎች ናቸው በሌላ የሚቀይሩለት።" [አሰዪዱል በደዊይ ዲራሳህ ነቕዲያህ፡ 15]
وكان يمكث طوال نهاره وليله قائمًا شاخصًا ببصره إلى السماء، وقد انقلب سواد عينيه بحمرة تتوقد كالجمر، وكان يمكث الأربعين يومًا وأكثر لا يأكل ولا يشرب ولا ينام
"ቀንና ሌቱን ሙሉ አይኑን ወደ ሰማይ አፍጥጦ ነበር የሚቆየው። የአይኑ ጥቁሩ ክፍል እንደ ፍም የሚንቀለቀል ቀይ ሆኖ ተቀይሮ ነበር። አርባ ቀን ሳይበላ፣ ሳይጣጣ፣ ሳይተኛ ይቆያል።" [ዳኢረቱል መዓሪፊል ኢስላሚያህ: 2/476]
ኢንሷፍ!
ሁሉም ሱፊዮች እንዲህ ናቸው ማለቴ አይደለም። ነገር ግን በተለይ በዚህ ዘመን ያሉ ሱፊዮች እንዳለ እነዚህን ጀ *ዝ -ባዎች በደፈናው ካልሆነ በስተቀር አያወግዙም። አብዛኞቹ እነ አቡ የዚድ አልቢስጧሚን፣ እነ ሐላጅን፣ ኢብኑ ሰብዒንን፣ ኢብኑ ዐረቢን፣ ኢብኑ ፋሪድን፣ በደዊይን፣ ቁነዊይን፣ ቲልሚሳኒይን፣ ሻዚሊይን፣ ጀላሉዲን ሩሚን፣ ሪፋዒይን፣ ... ሲያወድሱ ነው የሚታወቁት። ማረጋገጥ ከፈለግክ የሙሐመድ አወልን መንዙማ ማዳመጥ ትችላለህ። የዚህን ሰው ኮተት የሚያደንቁትንም እዚሁ ውስጥ አስባቸው። ሺርክ የማይጎረብጣቸው ፍጡሮች ናቸው።
.
"እስራኤላዊው" የሁዲ ሃጋይ ኤርሊች "ለኢትዮጵያ የሚያስፈልገው እስልምና አሕ. ባሽ ነው" ሲል እንዲህ አይነቱን የጀዝ * ባዎች መንገድ ማለቱ ነው። እነ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ዘመድኩን በቀለ፣ አባይነህ ካሴ፣ ...ለአሕ * ባሽ የሚወግኑት ያለ ምክንያት አይምሰልህ።
* "በምስሉ ላይ ያለው ሰው ምን እየሰራ ነው?" እንዳትሉ! "ምነው አይባልም የወልይ ነገርi"
=
( Ibnu Munewor ፣ ሸዋል 18/1444 (ሚያዚያ 30/ 2015 ))
የቴሌግራም ቻናል፡-
Comment
Share
Send as a message
Share on my page
Share in the group