UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
ሁድሁድ፡ ተአምረኛው ወፍ!
~
ነብዩ ሱለይማን ብኑ ዳውድ ﷺ እጅግ አስደናቂ በሆነ መልኩ አላህ ሁሉን ነገር የገራላቸው ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡ ከቁርኣን ጥቂት ቀንጨብ ላድርግማ፡-
وَلَقَدْ آتَيْنَا دَاوُودَ وَسُلَيْمَانَ عِلْمًا ۖ وَقَالَا الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي فَضَّلَنَا عَلَىٰ كَثِيرٍ مِنْ عِبَادِهِ الْمُؤْمِنِينَ
{ለዳውድና ለሱለይማንም እውቀትን በእርግጥ ሰጠናቸው፡፡ አሉም፡- “ምስጋና ለአላህ ይገባው፡፡ ለዚያ ከምእምናን ባሮቹ በብዙዎቹ ላይ ላበለጠን፡፡”}
وَوَرِثَ سُلَيْمَانُ دَاوُودَ ۖ وَقَالَ يَا أَيُّهَا النَّاسُ عُلِّمْنَا مَنْطِقَ الطَّيْرِ وَأُوتِينَا مِنْ كُلِّ شَيْءٍ ۖ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْفَضْلُ الْمُبِينُ
{ሱለይማንም ዳውድን ወረሰ፡፡ አለም፡ “ሰዎች ሆይ! የወፍን ቋንቋ ተስተማርን፡፡ ከነገሩ ሁሉም ተሰጠን፡፡ ይህ እርሱ በእርግጥ ግልጽ የሆነ ችሮታ ነው!”}
وَحُشِرَ لِسُلَيْمَانَ جُنُودُهُ مِنَ الْجِنِّ وَالْإِنْسِ وَالطَّيْرِ فَهُمْ يُوزَعُونَ
{ለሱለይማንም ሰራዊቶቹ ከጂን፣ ከሰውም፣ ከወፍም የሆኑት ተሰበሰቡ፡፡ እነሱም በስርኣት ይደራጃሉ፡፡}
حَتَّىٰ إِذَا أَتَوْا عَلَىٰ وَادِ النَّمْلِ قَالَتْ نَمْلَةٌ يَا أَيُّهَا النَّمْلُ ادْخُلُوا مَسَاكِنَكُمْ لَا يَحْطِمَنَّكُمْ سُلَيْمَانُ وَجُنُودُهُ وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ
{በጉንዳንም ሸለቆ በመጡ ጊዜ አንዲት ጉንዳን “እናንተ ጉንዳኖች ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ፡፡ ሱለይማንና ሰራዊቱ እነርሱ የማያውቁ ሲሆኑ እንዳይሰባብሩዋችሁ” አለች፡፡}
فَتَبَسَّمَ ضَاحِكًا مِنْ قَوْلِهَا وَقَالَ رَبِّ أَوْزِعْنِي أَنْ أَشْكُرَ نِعْمَتَكَ الَّتِي أَنْعَمْتَ عَلَيَّ وَعَلَىٰ وَالِدَيَّ وَأَنْ أَعْمَلَ صَالِحًا تَرْضَاهُ وَأَدْخِلْنِي بِرَحْمَتِكَ فِي عِبَادِكَ الصَّالِحِينَ
{(ሱለይማን) ከንግግርዋም እየሳቀ ፈገግ አለ፡፡ “ጌታዬ ሆይ! ያቺን በእኔና በወላጆቼ ላይ የለገስካትን ጸጋህን እንዳመሰግን፣ የምትወደውንም በጎ ሥራ እንድሰራ ምራኝ፡፡ በችሮታህም በመልካሞቹ ባሮችህ ውስጥ አግባኝ” አለ፡፡}
وَتَفَقَّدَ الطَّيْرَ فَقَالَ مَا لِيَ لَا أَرَى الْهُدْهُدَ أَمْ كَانَ مِنَ الْغَائِبِينَ
{ወፎቹንም ተመለከተ፤ አለም፡ “ምነው ሁድሁድን አላየውም?! ወይስ (በቦታው) ከሌሉት ሆኗልን?”}
لَأُعَذِّبَنَّهُ عَذَابًا شَدِيدًا أَوْ لَأَذْبَحَنَّهُ أَوْ لَيَأْتِيَنِّي بِسُلْطَانٍ مُبِينٍ
{“በእርግጥ ብርቱ ቅጣትን እቀጣዋለሁ፡፡ ወይም በእርግጥ አርደዋለሁ!! ወይም (ለመጥፋቱ አሳማኝ የሆነ) ግልፅ የሆነን ማስረጃ ያመጣልኛል” (አለ፡፡)}
فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍ فَقَالَ أَحَطْتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِ وَجِئْتُكَ مِنْ سَبَإٍ بِنَبَإٍ يَقِينٍ
{(ሁድሁድ ግን) ሩቅ ያልሆነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም፡ “ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ፡፡”}
إِنِّي وَجَدْتُ امْرَأَةً تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِنْ كُلِّ شَيْءٍ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌ
{“እኔ የምትገዛቸው (ሰዎች ያሏት) የሆነችን፣ ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችን ሴት አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡}
وَجَدْتُهَا وَقَوْمَهَا يَسْجُدُونَ لِلشَّمْسِ مِنْ دُونِ اللَّهِ وَزَيَّنَ لَهُمُ الشَّيْطَانُ أَعْمَالَهُمْ فَصَدَّهُمْ عَنِ السَّبِيلِ فَهُمْ لَا يَهْتَدُونَ
{“እርሷንም ሕዝቦችዋንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም፡፡”}
أَلَّا يَسْجُدُوا لِلَّهِ الَّذِي يُخْرِجُ الْخَبْءَ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَيَعْلَمُ مَا تُخْفُونَ وَمَا تُعْلِنُونَ
{“ለዚያ በሰማያትና በምድር የተደበቀውን ለሚያወጣው፣ የምትሸሽጉትንና የምትገልፁትንም ሁሉ ለሚያውቀው አላህ እንዳይሰግዱ (ሰይጣን አግዷቸዋል)፡፡”}
اللَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ رَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ
{“አላህ ከርሱ ሌላ (የእውነት) አምላክ የለም፡፡ የታላቁ ዐርሽ (ዙፋን) ጌታ ነው፡፡”}
قَالَ سَنَنْظُرُ أَصَدَقْتَ أَمْ كُنْتَ مِنَ الْكَاذِبِينَ
{(ሱለይማንም) አለ፡- “እውነት እንደ ተናገርክ ወይም ከውሸታሞቹ እንደ ሆንክ ወደፊት እናያለን፡፡”}
اذْهَبْ بِكِتَابِي هَٰذَا فَأَلْقِهْ إِلَيْهِمْ ثُمَّ تَوَلَّ عَنْهُمْ فَانْظُرْ مَاذَا يَرْجِعُونَ
{“ይህንን ደብዳቤዬን ይዘህ ሂድ፡፡ ወደ እነርሱም ጣለው፡፡ ከዚያም ከእነሱ ዘወር በል፡፡ ምን አንደሚመልሱም ተመልከት፡፡”}
ሁድሁድ የታዘዘውን ፈፀመ፡፡ ደብዳቤውንም ከሱለይማን ወስዶ የመን ደርሶ የሰበእ (ሳባ) ንግስት ከምትገኝበት ስፍራ ጣለው፡፡ ተልእኮው ግቡን መቷል፡፡ ደብዳቤው ከንግስቲቷ እጅ ገባ፡፡ ይህኔም፡
قَالَتْ يَا أَيُّهَا الْمَلَأُ إِنِّي أُلْقِيَ إِلَيَّ كِتَابٌ كَرِيمٌ
{አለች፡ “እናንተ መማክርቶች ሆይ! እኔ የተከበረ ደብዳቤ ወደኔ ተጣለ፡፡”}
إِنَّهُ مِنْ سُلَيْمَانَ وَإِنَّهُ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
{“እነሆ እርሱ ከሱለይማን ነው፡፡ እርሱም በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” (የሚል መክፈቻ አለው፡፡)}
أَلَّا تَعْلُوا عَلَيَّ وَأْتُونِي مُسْلِمِينَ
{“በእኔ ላይ አትኩሩ፡፡ ታዛዦችም ሆናችሁ ወደኔ ኑ” (የሚል ነው)፡፡} [አነምል፡ 15 - 31]
ይህን ልብ አንጠልጣይ ታሪክ መጨረስ የፈለገ ጥሩ የሆነ ተፍሲር ይዞ እስከመጨረሻው መከታተል ይችላል፡፡ እኔ ግን አንድ ጥያቄ ጠይቄ ፅሁፌን ልቋጭ፡፡ ሁድሁድ፡ ንግስተ-ሳባ የታደለችውን ሀብትና ድሎት ከገለፀ በኋላ ፀሀይ አምላኪ የሆኑትን ንግስቷን እና ህዝቦቿን ከእውነተኛው የተውሒድ መስመር ያፈነገጡ እንደሆኑ በሚደንቅ ሁኔታ እንዲህ ሲል ገልፁዋቸዋል፡-
“እርሷንም ሕዝቦቿንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም!”
አላሁ አክበር! ዛሬም ልክ እንዲሁ ሸይጧን ጥፋታቸውን አስውቦላቸው በአላህ ላይ ማጋራታቸውን እንደ ተውሒድ፣ እንደ ፅድቅ የሚቆጥሩት ስንትና ስንት ናቸው?! ህሊና ያላችሁ አስተውሉ! ሁድሁድ ቀጠለ፣ የሰዎቹ ምግባር ማስተዋሉን ላልተነፈገ ከህሊና ጋር የሚጋጭ እንደሆነ እንዲህ ገለፀው፡-
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
2 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ለውዴታቸው መመዘኛው ውልደታቸውን አስቦ መፈንጠዝ ቢሆን በመወለዳቸው ከአቡለሀብ በላይ ማን ፈነጠዘ እና?
መውደድ ትርጉም ሚሰጠው.... ተወዳጁ አካል እንድትወደው በሚፈልገው መንገድ ስትወደው ነው። ለራሱ ክፉ ደጉን ያለየ ነው ብለህ እስካልጠረጠርክ በቀር። አሽረፈል ኸልቅ ደሞ ከዚህ የጠሩ እንዴት ቢወደዱ እንደሚገባቸው ያወቁ፣ መለኮታዊው ትእዛዝም በዚህ ላይ ሚመራቸው ናቸው።
ለዚህም ስል እንድወዳቸው በፈለጉት መልክ ለመውደድ በማረገው ሙከራዬ ምክንያት መውሊዳቸውን አላከብርም🙌
አክባሪ እና ብቸኛ ወዳጃቸው ነኝ ባዩንም... እንቢተኛ ሁነህባቸዋል ብዬ በሳቸው ጠላትነት ልፈረጀው ሳልዳፈር እኔን በታዛዥነቴ ምክንያት ጠላት ለሚለኝ ቂል አልረበሽም😊
ምክንያቱም "መወለዳቸውን ጠልታ ነው" ባለኝ ጭፍን ሎጂኩ አምሳያ ሄጄ "በመሞታቸው ተደስተህ ነው" በዛሬ ቀን ምደልቀው ብሎ መበሻሸቅ አብሮ ቂል ከመሆን የዘለለ ምጥቀት ስለማይጠይቅ።
ብቻ ግን ልክ በእንደዛሬ በረቢዕ 12 በ 11 ኛወ አመተ ሂጅራ ሞቅ ባለው ንጋት ረሱላችን اللَّهُمَّ الرفيق الأعلى ብለው ወደ ምርጫዊ የተሻለ የህይወት ጉዟቸው ተሸጋግረዋል። ለእኛ ከየትኛውም ጉድለት በላይ ይህ ክስተት አጉድሎብናል።
ምድር የመደምደሚያ ነብይዋን በሞት ከመሸኘትዋ በላይ ምንም ፅልመት አይኖርባትም😥
ከረሱል ሞት ተያይዞ ምን ክስተት ይበልጥ ልባችሁን ይነካዋል?
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
~ኢላሂ!… የልቤን ምሥጢር አንተው ታውቃለህ። በሰዎች ዘንድ አስመስል ይሆናል እንጂ አንተ ዘንድ ፈፅሞ አይቻለኝም። እንደማትከለክለኝ ባውቅም ልጠይቅህ አፍራለሁ። የምታውቀው እኔነቴን ላንተ አላስረዳም። አንተን ብቻ ግን እከጅላለሁ። ከእንግዲህ ላንተ ካልሆነ በቀር አንዲትም እንባ እንዳላፈስ እርዳኝ።
• ከ አሁን በፊት ብዙ ነገር ፈልግያለሁ። በፍላጎቴ ውስጥ ግን አንተ አልነበርክምና አንዱም ያገኘሁት አላስደሰተኝም።ኢላሂ… አንተን ብቻ እፈልጋለሁ። መቼ እንደተሰበርኩ፣ ምን እንደሰበረኝ፣ እንዴት እያሳለፍኩ እንደሆነ ካንተ በቀር ማንም አያውቅም። አንተ ካልሆንክ በቀር ማንም አይረዳኝም። ያረሂም… የደካማ ደካማ የሆንኩት ባርያህ ነኝና ውደደኝ። በልቤ ከምከጅለው ነገር ሁሉ አንተ ቅደም።
ያ ረሒም!…ሁሌም መንገድ እስታለሁ። ርቄህ ተውከኝ እያልኩ አንተን እወቅሳለሁ። ደግሞ ሁሉንም አካልዬ መንገድ እንደሌለኝ ሳውቅ መልሼ ወዳንተው እመጣለሁ።ረቢ… ሁለንተናዬን ሁሉ ወዳንተ አድርግልኝ።  መረን ካጣች ነፍሴ እየታገልኩ አንተን እናፍቃለሁ። ፀዳሁ እያልኩ እመነችካለሁ። አፅዳኝ። የተገዛሁህ እየመሰለኝ እጅግ አምፅሀለው። እኔን ለእኔ አትተወኝ። ያረቢ ፍፃሜዬ ከጅማሬዬ ይበልጥ የተዋበ አድርግልኝ። ሞቴን ከህይወቴ ይበልጥ አሳምርልኝ። እዝነትህን ከመልካም ስራዬና ከዱዓዬ አስቀድምልኝ። እየተወኩህ አልተውከኝምና እኔን ለእኔ አትተወኝ። ያረቢ አንዳንዴ ብቻ አይደለም ሁሌም አንተን ብቻ የምከጅል አድርገኝ።…
=t.me/AbuSufiyan_Albenan
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
وَإِذْ قَالَ إِبْرَاهِيمُ رَبِّ اجْعَلْ هَٰذَا بَلَدًا آمِنًا
ኢብራሂም ባለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ <<ጌታዬ ሆይ! ይህንን ጸጥተኛ አገር አድርግ>>፡፡
አዎ ሰላምሽ ይብዛ የሁለቱ ሀረሞች ምድር
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group