UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
«እኔ ገና ነኝ…»
 
~በዲናችን ውስጥ «ተዋዱዕ» (መተናነስ) እጅግ የተወደደ እና የላቀ ምግባር ነው። ነቢዩ(ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) «ለአላህ ብሎ የተናነሰን ሰው አላህ ከፍ ያደርገዋል» ብለዋል። ነገር ግን በዘመናችን በአንዳንድ መድረኮች እና የዳዕዋ ፕሮግራሞች ላይ የምንታዘበው ነገር አለ። እርሱም መተናነስ የመሰለ ነገር ግን ሲደጋገምና ከልክ ሲያልፍ «እኔን አክብሩኝ» ወይም «እኔን ከፍ አድርጉኝ» የሚል ድብቅ መልዕክት ያለው የሚመስል አካሄድ ነው።
 
🎤 አንድ ወንድም ወይም ኡስታዝ መድረክ ላይ እንዲናገር ከተጋበዘ፣ አዘጋጆቹ በቦታው የመረጡት የሚናገረው ነገር ይጠቅማል ብለው አምነውበት ነው። ነገር ግን ተናጋሪው ማይኩን እንደጨበጠ፡- «እኔ ለዚህ ቦታ የምገባ አይደለሁም»፣ «እዚህ ጋ ሸይኽ እከሌ እያሉ እኔ መናገሬ ስህተት ነው»፣ «እኔ ገና ተማሪ ነኝ»፣ «መሃይሙ ወንድማችሁ»... እያለ ብዙ ደቂቃዎችን ይፈጃል።
 
ይህ አድማጭን ማሰልቸቱ ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ዋናው ቁምነገር ለመግባት እንቅፋት ይሆናል። ስለ ራስ መሃይምነት የሚወራው ወሬ ከዋናው ትምህርት ሲበልጥ ነገሩ ከአደብ ይወጣል። እውነተኛ አደብ የተሰጠንን አደራ በአግባቡ መወጣት እንጂ፣ ራስን በማራከስ ጊዜን ማቃጠል አይደለም።
 
✅️አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ራሳቸውን ዝቅ የሚያደርጉት፣ሌሎች ሰዎች እንዲያስተባብሉላቸው እና እንዲያሞግሷቸው ፈልገው ሊሆን ይችላል።ለምሳሌ አንድ ሰው «እኔ እኮ ደካማ ነኝ፣ ምንም እውቀት የለኝም»ሲል፣ አድማጮች በውስጣቸው ወይም በአደባባይ «ኧረ እንደውም አንተ እኮ ትልቅ አዋቂ ነህ፣ ማንም የማይችለውን ችለሃል»እንዲሉለት የሚፈልግበት ሁኔታ አለ።
 
📚ታላቁ ዓሊም ኢብኑ ረጀብ አል-ሀንበሊ (ረሂመሁላህ) “ዘም አል-ማል ወል-ጃህ” በተሰኘው ኪታባቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፡-
«وَمِنْهُمْ مَنْ يَذُمُّ نَفْسَهُ بَيْنَ النَّاسِ يُرِيدُ بِذَلِكَ أَنْ يَرَوْا تَوَاضُعَهُ، فَيَمْدَحُوهُ بِذَلِكَ، وَهَذَا مِنْ دَقَائِقِ أَبْوَابِ الرِّيَاءِ...»
 
«ከእነሱም (ከሰዎች) መካከል ሰዎች ትህትናውን ያዩለት ዘንድ በሰዎች ፊት ራሱን የሚወቅስ  አለ፤ በዚህም ተግባሩ እንዲያሞግሱት ይፈልጋል። ይህ (ተግባር) ረቂቅ ከሆነ የይዩልኝ (ሪያ) በር ነው።»
 
📚እንዲሁም ከሰለፎች አንዱ የሆነው ሙጠሪፍ ኢብኑ ዐብዲላህ እንዲህ ይላል፡-
«كفى بالمرءِ تزكيةً لنفسِه أن يذمَّها على الملأ»
«አንድ ሰው በአደባባይ (በሰዎች ፊት) ራሱን መውቀሱ፤ ራሱን ከማጥራት ይበቃዋል።»
 
ማለትም፡- ሰዎች «እንዴ! እሱ እኮ እንዴት ያለ ትሁት ነው» ብለው እንዲያወድሱት መንገድ እየጠረገላቸው ስለሆነ ነው።
 
✔️በሌላ አባባል፣ ሰውየው ራሱን ዝቅ የሚያደርገው ሰዎች ከፍ እንዲያደርጉት ነው። ይህ ልብን መፈተሸ የሚያስፈልገው አደገኛ በሽታ ነው።
 
ምክንያቱም ራስን በአደባባይ ማራከስ፣ «እዩኝ እኔ እኮ ምን ያህል ትሁት (ሙተዋዲዕ) ነኝ» ብሎ እንደመናገር ስለሚቆጠር ነው።
 
☑እና ውድ ወንድሞቼ…
ትህትና ማለት ራስን መካድ ወይም ያለመቻልን መስበክ ማለት አይደለም። ትህትና ማለት ከአንተ በታች ካለ ሰውም ቢሆን እውነት ሲመጣ መቀበል ነው።ሰዎችን አለመናቅ። ሌሎችን ከራስ በታች አድርጎ አለማየት ነው።
 
🎤ስለዚህ ሁሌ በመድረክ ላይ ስንወጣ«እኔ ደካማ ነኝ»እያሉ ከማውራት ይልቅ፣ በልብ ወደ አላህ በመተማመን «አላህ ሆይ አንደበቴን ፍታ፣ እውቀትን ጨምርልኝ» ብሎ በዱዓ መጀመር።ከዛም በቀጥታ ወደ ተጠሩበት ርዕስ መግባት። አድማጩ የመጣው መልዕክት ሊሰማ እንጂ የተናጋሪውን የትህትና ደረጃ ለመለካት አይደለም።
 
✅️እውነትም ታላላቅ ዑለማዎች ባሉበት መድረክ ላይ የመናገር እድል ከተሰጠ፣ «እርሶ እያሉ መናገሬ ባይገባም፣ ባዘዙኝ መሰረት…»ብሎ በአጭሩ ማለፍ እንጂ፣ የረጅም ደቂቃ «እኔኮ አይገባኝም» ንግግር አያስፈልግም።በመድረክ ላይ የሚደረግ የተጋነነ ራስን ዝቅ የማድረግ ዘመቻ፣ ከትህትና ይልቅ ለሰይጣን መግቢያ ቀዳዳ ሊሆን ስለሚችል መጠንቀቁ ይበጃል።
t.me/AbuSufiyan_Albenan
t.me/AbuSufiyan_Albenan
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
«እኔ ገና ነኝ…»
 
~በዲናችን ውስጥ «ተዋዱዕ» (መተናነስ) እጅግ የተወደደ እና የላቀ ምግባር ነው። ነቢዩ(ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) «ለአላህ ብሎ የተናነሰን ሰው አላህ ከፍ ያደርገዋል» ብለዋል። ነገር ግን በዘመናችን በአንዳንድ መድረኮች እና የዳዕዋ ፕሮግራሞች ላይ የምንታዘበው ነገር አለ። እርሱም መተናነስ የመሰለ ነገር ግን ሲደጋገምና ከልክ ሲያልፍ «እኔን አክብሩኝ» ወይም «እኔን ከፍ አድርጉኝ» የሚል ድብቅ መልዕክት ያለው የሚመስል አካሄድ ነው።
 
🎤 አንድ ወንድም ወይም ኡስታዝ መድረክ ላይ እንዲናገር ከተጋበዘ፣ አዘጋጆቹ በቦታው የመረጡት የሚናገረው ነገር ይጠቅማል ብለው አምነውበት ነው። ነገር ግን ተናጋሪው ማይኩን እንደጨበጠ፡- «እኔ ለዚህ ቦታ የምገባ አይደለሁም»፣ «እዚህ ጋ ሸይኽ እከሌ እያሉ እኔ መናገሬ ስህተት ነው»፣ «እኔ ገና ተማሪ ነኝ»፣ «መሃይሙ ወንድማችሁ»... እያለ ብዙ ደቂቃዎችን ይፈጃል።
 
ይህ አድማጭን ማሰልቸቱ ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ዋናው ቁምነገር ለመግባት እንቅፋት ይሆናል። ስለ ራስ መሃይምነት የሚወራው ወሬ ከዋናው ትምህርት ሲበልጥ ነገሩ ከአደብ ይወጣል። እውነተኛ አደብ የተሰጠንን አደራ በአግባቡ መወጣት እንጂ፣ ራስን በማራከስ ጊዜን ማቃጠል አይደለም።
 
✅️አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ራሳቸውን ዝቅ የሚያደርጉት፣ሌሎች ሰዎች እንዲያስተባብሉላቸው እና እንዲያሞግሷቸው ፈልገው ሊሆን ይችላል።ለምሳሌ አንድ ሰው «እኔ እኮ ደካማ ነኝ፣ ምንም እውቀት የለኝም»ሲል፣ አድማጮች በውስጣቸው ወይም በአደባባይ «ኧረ እንደውም አንተ እኮ ትልቅ አዋቂ ነህ፣ ማንም የማይችለውን ችለሃል»እንዲሉለት የሚፈልግበት ሁኔታ አለ።
 
📚ታላቁ ዓሊም ኢብኑ ረጀብ አል-ሀንበሊ (ረሂመሁላህ) “ዘም አል-ማል ወል-ጃህ” በተሰኘው ኪታባቸው ላይ እንዲህ ይላሉ፡-
«وَمِنْهُمْ مَنْ يَذُمُّ نَفْسَهُ بَيْنَ النَّاسِ يُرِيدُ بِذَلِكَ أَنْ يَرَوْا تَوَاضُعَهُ، فَيَمْدَحُوهُ بِذَلِكَ، وَهَذَا مِنْ دَقَائِقِ أَبْوَابِ الرِّيَاءِ...»
 
«ከእነሱም (ከሰዎች) መካከል ሰዎች ትህትናውን ያዩለት ዘንድ በሰዎች ፊት ራሱን የሚወቅስ  አለ፤ በዚህም ተግባሩ እንዲያሞግሱት ይፈልጋል። ይህ (ተግባር) ረቂቅ ከሆነ የይዩልኝ (ሪያ) በር ነው።»
 
📚እንዲሁም ከሰለፎች አንዱ የሆነው ሙጠሪፍ ኢብኑ ዐብዲላህ እንዲህ ይላል፡-
«كفى بالمرءِ تزكيةً لنفسِه أن يذمَّها على الملأ»
«አንድ ሰው በአደባባይ (በሰዎች ፊት) ራሱን መውቀሱ፤ ራሱን ከማጥራት ይበቃዋል።»
 
ማለትም፡- ሰዎች «እንዴ! እሱ እኮ እንዴት ያለ ትሁት ነው» ብለው እንዲያወድሱት መንገድ እየጠረገላቸው ስለሆነ ነው።
 
✔️በሌላ አባባል፣ ሰውየው ራሱን ዝቅ የሚያደርገው ሰዎች ከፍ እንዲያደርጉት ነው። ይህ ልብን መፈተሸ የሚያስፈልገው አደገኛ በሽታ ነው።
 
ምክንያቱም ራስን በአደባባይ ማራከስ፣ «እዩኝ እኔ እኮ ምን ያህል ትሁት (ሙተዋዲዕ) ነኝ» ብሎ እንደመናገር ስለሚቆጠር ነው።
 
☑እና ውድ ወንድሞቼ…
ትህትና ማለት ራስን መካድ ወይም ያለመቻልን መስበክ ማለት አይደለም። ትህትና ማለት ከአንተ በታች ካለ ሰውም ቢሆን እውነት ሲመጣ መቀበል ነው።ሰዎችን አለመናቅ። ሌሎችን ከራስ በታች አድርጎ አለማየት ነው።
 
🎤ስለዚህ ሁሌ በመድረክ ላይ ስንወጣ«እኔ ደካማ ነኝ»እያሉ ከማውራት ይልቅ፣ በልብ ወደ አላህ በመተማመን «አላህ ሆይ አንደበቴን ፍታ፣ እውቀትን ጨምርልኝ» ብሎ በዱዓ መጀመር።ከዛም በቀጥታ ወደ ተጠሩበት ርዕስ መግባት። አድማጩ የመጣው መልዕክት ሊሰማ እንጂ የተናጋሪውን የትህትና ደረጃ ለመለካት አይደለም።
 
✅️እውነትም ታላላቅ ዑለማዎች ባሉበት መድረክ ላይ የመናገር እድል ከተሰጠ፣ «እርሶ እያሉ መናገሬ ባይገባም፣ ባዘዙኝ መሰረት…»ብሎ በአጭሩ ማለፍ እንጂ፣ የረጅም ደቂቃ «እኔኮ አይገባኝም» ንግግር አያስፈልግም።በመድረክ ላይ የሚደረግ የተጋነነ ራስን ዝቅ የማድረግ ዘመቻ፣ ከትህትና ይልቅ ለሰይጣን መግቢያ ቀዳዳ ሊሆን ስለሚችል መጠንቀቁ ይበጃል።
t.me/AbuSufiyan_Albenan
t.me/AbuSufiyan_Albenan
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
كم تحزن عندما ترى في الساحة الدعوية في الحبشة طلاب علم لا يتجاوز عمرهم في الطلب عدد أصابع اليد الواحد ولا يتقنون أبجديات العلم وأصوله ثم يحشرون أنفسهم في أمور لا قبل لهم بها ، يخوضون بلا علم ويتكلمون بلا روية في مسائل عظيمة وخطيرة لا يتكلم عنها أصالة إلا أهل العلم الأكابر ، وهذه ظاهرة غير صحية منتشرة بين كثير من طلبة العلم المبتدئين المتحمسين وهي أحد أسباب اشتعال نار الفتنة بين السلفيين في العالم العربي والإسلامي وإن لم يتدارك الأمر مبكرا ولم يتحرك المشايخ الذين يقتدي بهم هؤلاء الشباب لإحداث تغيير جذري لكبح هذه الفتنة وتركوا الأمر كما هو الآن أخشى أن يتفاقم الأمر أكثر وأشد ومن ثم أن يخرج الأمر عن السيطرة فيحصل عواقب وخيمة لا تحمد عقباها يعاني منها المشايخ والدعاة أنفسهم من قِبل الفتية ويذقوا الأمرين كما حدث في كثير من البلدان من خلافات وتصدعات وصراعات مريرة بين أهل السنة وقد رأينا بعض طلبة العلم في بعض الدول العربية وهم يعظمون بعض المشايخ ويجعلونهم مرجعيات ثم ما لبثوا أن انقبلوا عليهم طعنا وتجريحا وقد حدث في الحبشة ما يضارع ذلك قبل مدة حيث انقلب بعص الدعاة على المشايخ الذين كانوا يجلهم أيما إجلال ومعظمكم تعرفون القصة وفيها العظة والعبرة والتاريخ قد يعيد نفسه، وحاليا التعصب والحماس الموجود لدى البعض رؤية ما يدور كما ينبغي بسبب غشاوةِ الحماس
 
ولن يشاد الدين أحد إلا غلبه
 
وستذكرون ما أقول لكم إن والسعيد من اتعظ بغيره ومن وقي الفتن.
 
ورحم الله الإمام الوادعي الذي حذر عن شرارة هذه الفتنة بقوله : ينبغي لنا جميعًا أن لا نمكن الفوضويين من الدعوة، فإنهم سيحطمون الجماعة، وستذكرون ". ”السير الحثيث" (ص438).
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ሁድሁድ፡ ተአምረኛው ወፍ!
~
ነብዩ ሱለይማን ብኑ ዳውድ ﷺ እጅግ አስደናቂ በሆነ መልኩ አላህ ሁሉን ነገር የገራላቸው ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡ ከቁርኣን ጥቂት ቀንጨብ ላድርግማ፡-
وَلَقَدْ آتَيْنَا دَاوُودَ وَسُلَيْمَانَ عِلْمًا ۖ وَقَالَا الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي فَضَّلَنَا عَلَىٰ كَثِيرٍ مِنْ عِبَادِهِ الْمُؤْمِنِينَ
{ለዳውድና ለሱለይማንም እውቀትን በእርግጥ ሰጠናቸው፡፡ አሉም፡- “ምስጋና ለአላህ ይገባው፡፡ ለዚያ ከምእምናን ባሮቹ በብዙዎቹ ላይ ላበለጠን፡፡”}
وَوَرِثَ سُلَيْمَانُ دَاوُودَ ۖ وَقَالَ يَا أَيُّهَا النَّاسُ عُلِّمْنَا مَنْطِقَ الطَّيْرِ وَأُوتِينَا مِنْ كُلِّ شَيْءٍ ۖ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْفَضْلُ الْمُبِينُ
{ሱለይማንም ዳውድን ወረሰ፡፡ አለም፡ “ሰዎች ሆይ! የወፍን ቋንቋ ተስተማርን፡፡ ከነገሩ ሁሉም ተሰጠን፡፡ ይህ እርሱ በእርግጥ ግልጽ የሆነ ችሮታ ነው!”}
وَحُشِرَ لِسُلَيْمَانَ جُنُودُهُ مِنَ الْجِنِّ وَالْإِنْسِ وَالطَّيْرِ فَهُمْ يُوزَعُونَ
{ለሱለይማንም ሰራዊቶቹ ከጂን፣ ከሰውም፣ ከወፍም የሆኑት ተሰበሰቡ፡፡ እነሱም በስርኣት ይደራጃሉ፡፡}
حَتَّىٰ إِذَا أَتَوْا عَلَىٰ وَادِ النَّمْلِ قَالَتْ نَمْلَةٌ يَا أَيُّهَا النَّمْلُ ادْخُلُوا مَسَاكِنَكُمْ لَا يَحْطِمَنَّكُمْ سُلَيْمَانُ وَجُنُودُهُ وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ
{በጉንዳንም ሸለቆ በመጡ ጊዜ አንዲት ጉንዳን “እናንተ ጉንዳኖች ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ፡፡ ሱለይማንና ሰራዊቱ እነርሱ የማያውቁ ሲሆኑ እንዳይሰባብሩዋችሁ” አለች፡፡}
 
فَتَبَسَّمَ ضَاحِكًا مِنْ قَوْلِهَا وَقَالَ رَبِّ أَوْزِعْنِي أَنْ أَشْكُرَ نِعْمَتَكَ الَّتِي أَنْعَمْتَ عَلَيَّ وَعَلَىٰ وَالِدَيَّ وَأَنْ أَعْمَلَ صَالِحًا تَرْضَاهُ وَأَدْخِلْنِي بِرَحْمَتِكَ فِي عِبَادِكَ الصَّالِحِينَ
{(ሱለይማን) ከንግግርዋም እየሳቀ ፈገግ አለ፡፡ “ጌታዬ ሆይ! ያቺን በእኔና በወላጆቼ ላይ የለገስካትን ጸጋህን እንዳመሰግን፣ የምትወደውንም በጎ ሥራ እንድሰራ ምራኝ፡፡ በችሮታህም በመልካሞቹ ባሮችህ ውስጥ አግባኝ” አለ፡፡}
وَتَفَقَّدَ الطَّيْرَ فَقَالَ مَا لِيَ لَا أَرَى الْهُدْهُدَ أَمْ كَانَ مِنَ الْغَائِبِينَ
{ወፎቹንም ተመለከተ፤ አለም፡ “ምነው ሁድሁድን አላየውም?! ወይስ (በቦታው) ከሌሉት ሆኗልን?”}
لَأُعَذِّبَنَّهُ عَذَابًا شَدِيدًا أَوْ لَأَذْبَحَنَّهُ أَوْ لَيَأْتِيَنِّي بِسُلْطَانٍ مُبِينٍ
{“በእርግጥ ብርቱ ቅጣትን እቀጣዋለሁ፡፡ ወይም በእርግጥ አርደዋለሁ!! ወይም (ለመጥፋቱ አሳማኝ የሆነ) ግልፅ የሆነን ማስረጃ ያመጣልኛል” (አለ፡፡)}
 
فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍ فَقَالَ أَحَطْتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِ وَجِئْتُكَ مِنْ سَبَإٍ بِنَبَإٍ يَقِينٍ
{(ሁድሁድ ግን) ሩቅ ያልሆነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም፡ “ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ፡፡”}
إِنِّي وَجَدْتُ امْرَأَةً تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِنْ كُلِّ شَيْءٍ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌ
{“እኔ የምትገዛቸው (ሰዎች ያሏት) የሆነችን፣ ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችን ሴት አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡}
وَجَدْتُهَا وَقَوْمَهَا يَسْجُدُونَ لِلشَّمْسِ مِنْ دُونِ اللَّهِ وَزَيَّنَ لَهُمُ الشَّيْطَانُ أَعْمَالَهُمْ فَصَدَّهُمْ عَنِ السَّبِيلِ فَهُمْ لَا يَهْتَدُونَ
{“እርሷንም ሕዝቦችዋንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም፡፡”}
 
أَلَّا يَسْجُدُوا لِلَّهِ الَّذِي يُخْرِجُ الْخَبْءَ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَيَعْلَمُ مَا تُخْفُونَ وَمَا تُعْلِنُونَ
{“ለዚያ በሰማያትና በምድር የተደበቀውን ለሚያወጣው፣ የምትሸሽጉትንና የምትገልፁትንም ሁሉ ለሚያውቀው አላህ እንዳይሰግዱ (ሰይጣን አግዷቸዋል)፡፡”}
اللَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ رَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ
{“አላህ ከርሱ ሌላ (የእውነት) አምላክ የለም፡፡ የታላቁ ዐርሽ (ዙፋን) ጌታ ነው፡፡”}
قَالَ سَنَنْظُرُ أَصَدَقْتَ أَمْ كُنْتَ مِنَ الْكَاذِبِينَ
{(ሱለይማንም) አለ፡- “እውነት እንደ ተናገርክ ወይም ከውሸታሞቹ እንደ ሆንክ ወደፊት እናያለን፡፡”}
اذْهَبْ بِكِتَابِي هَٰذَا فَأَلْقِهْ إِلَيْهِمْ ثُمَّ تَوَلَّ عَنْهُمْ فَانْظُرْ مَاذَا يَرْجِعُونَ
{“ይህንን ደብዳቤዬን ይዘህ ሂድ፡፡ ወደ እነርሱም ጣለው፡፡ ከዚያም ከእነሱ ዘወር በል፡፡ ምን አንደሚመልሱም ተመልከት፡፡”}
 
ሁድሁድ የታዘዘውን ፈፀመ፡፡ ደብዳቤውንም ከሱለይማን ወስዶ የመን ደርሶ የሰበእ (ሳባ) ንግስት ከምትገኝበት ስፍራ ጣለው፡፡ ተልእኮው ግቡን መቷል፡፡ ደብዳቤው ከንግስቲቷ እጅ ገባ፡፡ ይህኔም፡
قَالَتْ يَا أَيُّهَا الْمَلَأُ إِنِّي أُلْقِيَ إِلَيَّ كِتَابٌ كَرِيمٌ
{አለች፡ “እናንተ መማክርቶች ሆይ! እኔ የተከበረ ደብዳቤ ወደኔ ተጣለ፡፡”}
إِنَّهُ مِنْ سُلَيْمَانَ وَإِنَّهُ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
{“እነሆ እርሱ ከሱለይማን ነው፡፡ እርሱም በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” (የሚል መክፈቻ አለው፡፡)}
أَلَّا تَعْلُوا عَلَيَّ وَأْتُونِي مُسْلِمِينَ
{“በእኔ ላይ አትኩሩ፡፡ ታዛዦችም ሆናችሁ ወደኔ ኑ” (የሚል ነው)፡፡} [አነምል፡ 15 - 31]
 
ይህን ልብ አንጠልጣይ ታሪክ መጨረስ የፈለገ ጥሩ የሆነ ተፍሲር ይዞ እስከመጨረሻው መከታተል ይችላል፡፡ እኔ ግን አንድ ጥያቄ ጠይቄ ፅሁፌን ልቋጭ፡፡ ሁድሁድ፡ ንግስተ-ሳባ የታደለችውን ሀብትና ድሎት ከገለፀ በኋላ ፀሀይ አምላኪ የሆኑትን ንግስቷን እና ህዝቦቿን ከእውነተኛው የተውሒድ መስመር ያፈነገጡ እንደሆኑ በሚደንቅ ሁኔታ እንዲህ ሲል ገልፁዋቸዋል፡-
 
“እርሷንም ሕዝቦቿንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም!”
 
አላሁ አክበር! ዛሬም ልክ እንዲሁ ሸይጧን ጥፋታቸውን አስውቦላቸው በአላህ ላይ ማጋራታቸውን እንደ ተውሒድ፣ እንደ ፅድቅ የሚቆጥሩት ስንትና ስንት ናቸው?! ህሊና ያላችሁ አስተውሉ! ሁድሁድ ቀጠለ፣ የሰዎቹ ምግባር ማስተዋሉን ላልተነፈገ ከህሊና ጋር የሚጋጭ እንደሆነ እንዲህ ገለፀው፡-
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
3 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group