UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
መቆሚያ ያጣው የመርከዙ የቁልቁለት ጉዞ!
~
የሸሪዐ ቀዳሚ ግብ ጉዳትን ማስወገድ፣ ካልሆነ መቀነስ እንዲሁም ጥቅምን ማስገኘት ነው። አንዳንዴ የከፋውን ሸር ለማለፍ ወይም ለመቀነስ ሲባል ያነሰውን ሸር እንፈፅም ዘንድ ጫና ሊገጥመን ይችላል። በዚህ የተነሳ ለአጠቃላዩ የደዕዋ መስለሐ ሲባል ውስጣችን የማያምንበት ጉዳይ ላይ ልንነካካ እንችላለን። ይሄ ብስለት አልፎም ድፍረት የሚፈልግ ጉዳይ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ከእለት ወደ እለት መንሸራተቱን በ "መስለሐ" ወረቀት እየጠቀለለ የሚያቀርብ ብኩን አለ። ማዶ ላይ ያለን "መስለሐ" ሲያስብ ዙሪያውን ስላለው ተጨባጭ አያስብም። "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደሚባለው ማለት ነው።
የመርከዝ ኢብኑ መስዑድ አካሄድ እዚህ ላይ ነው ያለው። መሪዎቻቸው በዑጅበ ነፍስ የተወጠሩ፣ ቀድራቸውን የማያውቁ፣ "ከኛ ወዲያ መስለሐ እና መፍሰዳ የሚለይ ላሳር" ውስጥ የገቡ ናቸው። ይሄ አዲስ የመጣ ሳይሆን ነባር አመላቸው ነው። በዙሪያቸው ያለው "አገር ለመምራት እድሉ ቢስሰጣቸው መምራት የሚያስችል ብቃት አላቸው" የሚል፣ ቢያጥፉት የሚታጠፍ፣ ቢዘረጉት የሚዘረጋ እንዳሻቸው የሚሰሩት ስብስብ ለራሳቸው የተሳሳተ ግምት እንዲይዙ አድርጓቸዋል። የፈለገ ቢወርዱ "ኧረ አሁንስ በዛ!" የሚል ድፍረት ያለው ከኖረ ከስንት አንድ ነው። እሱውም ከተገኘ። ሰው በዚህ መጠን እንዴት በጋራ ጭፍን ተከታይ ይሆናል? የሚገርም ነው!
ወላሂ! መርከዙን የምታድኑት ኢኽላስን መሰረት ባደረገ እውነተኛ አካሄድ እንጂ በጭፍን ውግንና አይደለም። ሰዎቹንም ሲያጠፉ እጃቸውን በመያዝ እንጂ በጭፍን ብትከላከሉ እነሱንም ላትጠቅሙ ራሳሁንም ትጎዳላችሁ። ይልቁንም ከዚህ "እናንተን የማይታያችሁ ይታየናል" ከሚል አጉል ግብዝነት እንዲወጡ ብታግዟቸው ነው የሚሻለው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram: Contact @IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

كناشة ابن منور
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ግንኙነት ያልተፈፀመበት ኒካሕ
~
አንድ ሰው አንዲትን ሴት ኒካሕ አድርጎ ካገባ በኋላ ነገር ግን በመሃላቸው ግንኙነት ሳይፈፀም ከፈታት ፤ ለምሳሌ የተለያየ ሃገር እየኖሩ ኒካሕ ከታሰረ በኋላ ሳይገናኙ ፍቺ ቢፈፅም ዒዳ የለባትም። ምክንያቱም አላህ እንዲህ ብሏልና፦
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آَمَنُوا إِذَا نَكَحْتُمُ الْمُؤْمِنَاتِ ثُمَّ طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِنْ قَبْلِ أَنْ تَمَسُّوهُنَّ فَمَا لَكُمْ عَلَيْهِنَّ مِنْ عِدَّةٍ تَعْتَدُّونَهَا فَمَتِّعُوهُنَّ وَسَرِّحُوهُنَّ سَرَاحًا جَمِيلًا
{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ምእምናትን ባገባችሁና ከዚያም ሳትነኳቸው በፊት በፈታችኋቸው ጊዜ ለእናንተ በእነርሱ ላይ የምትቆጥሯት ዒዳ ምንም የላችሁም፡፡ አጣቅሟቸውም፤ (ጉርሻ ስጧቸው)፡፡ መልካም ማሰናበትንም አሰናብቷቸው፡፡} [አል አሕዛብ፡ 49]
* ይሄ ጉዳይ የዑለማእ ኢጅማዕ ያለበት ነው።
ማሳሰቢያ፦
* ዳግም ማግባት ከፈለገ መስፈርቱን ያሟላ አዲስ ኒካሕ ማሰር እንጂ እንዲሁ መልሻለሁ ብሎ መመለስ አይችልም።
* ለመመለስ ሌላ አግብታ መፈታቷ ሸርጥ አይደለም። ሌላ አግብታ የተፈታች ባይሆንም ማግባት ይችላል። ነገር ግን የባለፈው ፍቺ አንድ ተብሎ ይቆጠራል። ስለዚህ ሁለት ኒካሕ ነው የሚቀረው ማለት ነው።
.
በፍቺ ሳይሆን በሞት ከተለየ ግን የዒዳው ብይን ይለያል። ማለትም ኒካሕ ታስሮ ግንኙነት ሳይፈፀም በፊት ባል ከሞተ አራት ወር ከ 10 ቀን ዒዳ ትቆጥራለች። ከንብረቱም ትወርሳለች። ሙሉ መህሯንም ትወስዳለች። የመህሯ መጠን ቀድሞ ያልተወሰነ ከሆነ የአምሳያዎቿ መህር ታሰቦ ይሰጣታል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
Telegram: Contact @IbnuMunewor

Telegram: Contact @IbnuMunewor

كناشة ابن منور
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
ከትዳር በፊት ፍቅር የለም ብዬ የኸዲጃን ፍቅር ገደል አልከተውም… ምክንያቱ ምንም ይሁን አፍቅራ እንዳገባቻቸው አልጠራጠርም… በሪራ በሚሏት ሰሓቢት ፍቅር ተለክፎ በመዲና መንገዶች ላይ ከኋላዋ እየተከተለ… የእንባ ቋንጣውን በመዲና አድማስ ሲወረውር የነበረውን ሰሓባው ሙጊስ … አፍቃሪ አልነበርክም ልለው አልችልም… ቀድመው ቢለያዩና ከዚያ በኋላ ባያገባትም “ሙጊስ ለበሪራ ባለው ፍቅር፣ በሪራ ደግሞ ለሙግስ ባላት ጥላቻ አልተገረምክም ወይ” የተባለለት አፍቃሪ ነው… ያውም በረሱል አንደበት።
አንድ ነገር ግን አምናለሁ… ፍቅር በስሙ የሚደረጉ ኃጥያቶችን እንደማያውቃቸውና የአፍቃሪ መድሀኒቱም ትዳር እንደሆነ… ማንነትህን ፣ እምነትህንና ጉዞህን የሚያመክንብህ ከሆነ በሽታ እንደሆነ… አምናለሁ። ነብይህ “ለተዋደዱ ሰዎች ከኒካህ ውጪ (አማራጭ) አላየሁም” ሲሉም… ከትዳር በፊት መዋደድ እንዳለና ኒካህ ካልታከለበት ግን የኪሳራ መንገድ ሊሆን እንደሚችል ነው… አፍቅርሃል? በበር በኩል ና በቃ … በፍቅር ስም ሙድ አትያዝ!!
t.me/abdu_rheman_aman
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.
እየተማማራችሁ»አስተምሪዉ አስተምራት
እንደኔ ግን በሁሉም ወንድ ልጅ ሲበልጥ ነዉ የሚል አቋም አለኝ"በተለይ በዚህ ቁፅል እዉቀትና ኢማን በሆነበት ጊዜ,~~
ግንኮ ስንትና ስንት እንቁ ሴቶችም አልፈዋል!
~~
የሰዒድ ኢብኒል ሙሰየብ ሴት ልጅ ከአባቷ የያዘቺው ጥሩ የሚባል ዒልም ነበራትና
ያገባችውም ከአባቷ ሰኢድ ኢብኒል ሙሰየብ ደረሶች ውስጥ አንዱን ነበር በተጋቡም ከተወሰኑ ቀናቶች በኋላ ደረሳ ባልዋ ኩታውን ደርቦ ከቤት ሊወጣ ሲል ሚስት ወደት ልትሄድ ነው? ብላ ትጠይቀዋለች እርሱም ወደ አባትሽ የቂርዓት ቦታ በሚል መለሰላት"
እሷም አትሂድ"ተቀመጥ እኔ አባቴ የሚያስተምርህን ዒልም አስተምርሃለው በማለት አስቀረችዉ!!
[مصدر من الكتاب المدخل لابن الحاج ١/٢١٥]
https://t.me/+JILwkIarUT40YjFk
Telegram: Join Group Chat

Telegram: Join Group Chat

https://t.me/+JILwkIarUT40YjFk كُن نافعاً ولو بِالنية فإن الله إذا رأى فيك خيراً ، يسّرك للخير تَمَسَّكْ بِحَبْلِ اللهِ وَاتَّبِعِ الهُدَى ....
Send as a message
Share on my page
Share in the group