Al bani Ethiopia Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

ترجمہ ممکن نہیں

بسم الله،

عند الكلام عن القدس وبني إسرائيل هذه أكثر آية يُستشهد بها، في مخالفة واضحة لتفسير السلف رضي الله عنهم، رغم أن من التفاسير المعاصرة تقرر هذا أيضاً، كـأبي بكر الجزائري رحمه الله.

ويكفي جدا ما جاء بـ📖تفسير الإمام عبد الرازق الصنعاني...

{وَقَضَينا إِلى بَني إِسرائيلَ فِي الكِتابِ لَتُفسِدُنَّ فِي الأَرضِ مَرَّتَينِ وَلَتَعلُنَّ عُلُوًّا كَبيرًا}

عن قتادة، في قوله تعالى: {لَتُفْسِدُنَّ فِي ٱلأَرْضِ مَرَّتَيْنِ}: [الآية: 4]،

قال: ✪أما المرَّة الأولى، فسلَّطَ الله عليهم جالوتَ، حين بعث طالوت ومعه داود، فقتله داود ثم رُدَّت الكرة لبني إسرائيل، ثم جاء وعدُ الآخرة من المرتين {لِيَسُوءُواْ وُجُوهَكُمْ}: [الآية: 7]، قال: لِيُقَبّحُوا وجوهكم

{وَلِيُتَبِّرُواْ مَا عَلَوْاْ تَتْبِيراً}: [الآية: 7]، قال: ليدمروا ما علو تدميراً.

قال:✪ هو بُخْتَنَصَّر، قال: بعث عليهم في المرة الآخرة،

ثم قال:✪{عَسَىٰ رَبُّكُمْ أَن يَرْحَمَكُمْ وَإِنْ عُدتُّمْ عُدْنَا}: [الآية: 8]، فعادوا، فبعث الله عليهم محمداً صلى الله عليه وسلم، فَهُمْ يعْطُون الجزية عن يد وهم صاغرون.

1542-عن قتادة، في قوله تعالى: {وَجَعَلْنَا جَهَنَّمَ لِلْكَافِرِينَ حَصِيراً}: [الآية: 8]، قال: مَحْبَساً حُصِرا فيها. وقال الحسن: {حَصِيراً} فراشاً مِهَاداً. [الإسراء - آية ٤]

#islam #gaza #quran

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ترجمہ ممکن نہیں

እጅግ ልብ የሚነካ ታሪክ

አንድ ሰሃቢ ወደ ነብዩ ሙሀመድ(ሰ ዐ ወ) በመምጣት "አንቱ የአላህ

መልዕክተኛ አባቴ ሳያስፈቅደኝ ገንዘቤን ተጠቀመበት" ብሎ ስሞታ አቀረበ።

ነብዩ ሙሀመድ(ሰ ዐ ወ) አባቱን ይዞ እንዲመጣ ነገሩት። አባትየውን ሲጠሯቸው

ለምን እንደሆነ ጠየቁ። ልጃቸው ቅሬታ አቅርቦባቸው መሆኑን ሰሙ።

እጅግ በጣም ቅር አላቸው። ሲመጡ በመንገዳቸው በልባቸው የተሰማቸውን

በግጥም መልክ አሉት። ነብዩ ሙሀመድ(ሰ ዐ ወ) ወዳሉበት ቦታ ሄዱ። ቦታው

ላይ ከመድረሳቸው በፊት ጅብሪል(ዐ ሰ) ወደ ነብዩ ሙሀመድ(ሰ ዐ ወ)

መልዕክት ይዞ ብቅ ብሎዋል። "አባትየው ሲመጡ አስቀድመህ በልቡ ይል

የነበረውን ትጠይቀው ዘንድ የአላህ(ሱ ወ) መሺዓ ነው" አላቸው።

አባትየው ድምፅ አውጥተው ባይናገሩትም የልብ አዋቂው ጌታችን አላህ(ሱ ወ)

ስሞታቸውን አድምጧቸዋል። ለኛ መማሪያ ይሆን ዘንድ መላይካውን ጅብሪል(ዐ

ሰ) ላከልን። ነብዩ ሙሀመድ(ሰ ዐ ወ) "ጉዳዩ ላይ ከመግባታችን በፊት ስትመጣ

በልብህ ትለው የነበረውን እንድትነግረኝ እፈልጋለሁ" አሉት።

አባትየው በመገረም "አንቱ የአላህ መልዕክተኛ መሆናችሁን እመሰክራለሁ።

እውነት ነው በመንገዴ ስመጣ አዝኜ በውስጤ ሳወራ ነበር። በልቤ ብናገረውም

አላህ ሰምቶኛል። አንተም ሀቅ ነህ ጌታህም ሀቅ ነው" አሉት። ነብዩ ሙሀመድ(ሰ

ዐ ወ) "ምን ነበር ትናገር የነበረው?" ብለው ጠየቁት።

አባትየውም ያሉትን ተናገሩ። "ልጄ አንተን ከወለድን ጀምሮ ለኛ መኖር ትተን

ላንተ መኖር ጀመርን። አንተን ለማስጠለል ነፋስን ታገልን። ቅዝቃዜ እንዳይነካህ

በረዶ ላይ ሰራን። ፈገግታህን ለማየት በማታ ሰራን። ሙሉ ለሊት እንደ እንስሳ

ለፋን። የወጣትነት ጉልበቴን አድክሜ አጥንትህን አጠነከርኩ። ላንተ ወጣትነት

ስለፋ እኔ አረጀሁ። ጀርባዬን አጥፌ ጀርባህን አቀናሁ።

በእግርህ ቆመህ እንድትሄድ ስለፋ እግሮቼ ሀይል አጡ። እጆችህ ሲጠነክሩ

የኔው ይንቀጠቀጥ ጀመር። ላንተ ስል ደከምኩ አንተ ግን አመፅክብኝ። ላን ስል

መድከሜ፣ ዱዓ ማድረጌ፣ ረፍት ማጣቴ እያደር እገዛ ይሆነኛል ብዬ አስቤ ነበር።

ነገር ግን ወጣትነት አንተ ላይ ሲነግስ እኔን እርጅና ጨረሰኝ። ወጣትነት ላንተ

ውበት ሲለግስህ እርጅና እኔን አረገፈኝ።

እርጅና ቢጠናብኝ ፊትህን አዞርክብኝ። ባሪያህ አደረከኝ። እኔ ታዛዥ አንተ አዛዥ

ሆንክ። የ30 አመት ልፋቴን አስዋሸሁ። አባትነቴን ረሳሁ። ባሪያህ ሆንኩኝ። ልጄ

ቢሆን ኖሮ ይህን አያደርግም ብዬ አሰብኩ። በብርድና በሞቃት ቀን ከለሊት

መልፋቴን ረሳህ። ስሜቴንና ደስታዬን ቀበርኩት። ዛሬ ላይ አንተ አለቃዬ እኔ

ባሪያህ ሆንኩኝ። እሺ ባሪያህ መሆኔን ልቀበል ግን ጎረቤትህም ጭምር ነኝ።

ሰው ጎረቤቱን ይጠይቃል። እየኝ ዛሬ እያለቀስኩ ነው" ብለው በሲቃ ድምፅ

ተናገሩ።

የአባትየውን ቃላቶች አማርኛ ችሎ አይገልፀውም። ነብዩ ሙሀመድ(ሰ ዐ ወ)

ይህን ሲሰሙ አለቀሱ። የልጁን ኮሌታ አጥብቀው ያዙና "ከዚህ ጥፋ። አንተም

ሆነ ያንተ ንብረት ያባትህ ነው። የኔ ነው የምትለው ሁሉ ያባትህ ነው" አሉት።

የአባቶቻችንን ሀቅ እንጠብቅ። ለኛ ብለው የደከሙትን አላህ ብቻ ነው

የሚያውቀው። አባት ቀልብ ያደረገበት ልጅ አያልፍለትም። ዱንያም አሄራውም

አያምርም። የአባቶችን ሀቅ ከሚጠብቁ ሙዕሚኖች አላህ ያድርገን።

በማያልቀው የአላህ አጅር ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ ይህን መል ክት ሼር በማድረግ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
ترجمہ ممکن نہیں

ምዕራቡ አለም በብሪቴይን እርግዝና በፈረንሳይ አዋላጅነት በጥቅመኛ አረቦች አጨብጫቢነት የወለዷትን የግፍና የበደል ልጅ መጠበቅ ላይ መተባበር መያዛቸው ብዙ አያስገርምም። ታማኝነት አልባ፣ የሁለት ሚዛን ባለቤት ከሆኑት የግፍ መሪዎችና ልሂቃን ስብስብ ከዚህ የተለየ መጠበቅም የዋህነት ነው። ቅሉ ሁሉም ነገር ማብቂያ አለው፤ ሁሉም ነገር መጠናቀቂያ አለው።

★ ማብቂያውም ፍትህን ለተነፈጉት ሁሉ ብርሃን መሆኑ ነው። ወላዱም፣ ያዋለደውም፣ ያጨበጨበውም፣ የተወለደውም የበደልና የግፍ ልጅም መዋረዳቸው አይቀርም። በነፍሶቻቸው ውስጥ የነገቡት የበላይነትና ሁሉን አድራጊነት መንፈስ ቅዠት መሆኑ አይቀርም። የአላህ ቃል እንዲህ ይላል።

« إن الذين كفروا ينفقون أموالهم ليصدوا عن سبيل الله فسينفقونها ثم تكون عليهم حسرة ثم يغلبون… »

« እነዚያ የካዱት ሰዎች ከአላህ መንገድ ሊከለክሉ ገንዘባቸውን ያወጣሉ። በእርግጥም ያወጣሉ። (ካወጡም በኃላ) ፀፀት ትሆንባቸዋለች። ከዚያም ይሸነፋሉ። የካዱት ሰዎች ወደ ገሀነምም ይሰበሰባሉ።»

እንዲህም ይላል።

« …عسى الله أن يكف بأس الذين كفروا والله أشد بأسا وأشد تنكيلا »

« … አላህ የካዱትን ሰዎች ኃይል ሊከለክልልህ ይከጀላል (ይከለክልልሃል)። አላህም በኃይል ሲይዝ የበረታ፤ ቅጣቱም እጅግ ጠንካራ ነው። »

★ በተቃራኒው በበደል ውስጥ በትግልና በትእግስት፣ በትእግስትና በትግል ያለፉት ሁሉ የአላህ እርዳታ እየጨመረላቸው፤ እዝነቱንና እገዛውን እያሰፋላቸው፤ የድልን ካባ እንደሚያጎናፅፋቸው እርግጥ ነው።

ለተወዳጁ መልእክተኛው (ሰዐወ) አላህ እንዲህ ይላቸዋል።

« …فسيكفيكهم الله وهو السميع العليم »

« … ከእነርሱም (ከከሃዲያኑ) አላህ ይበቃሃል። እርሱ ሰሚና ዐዋቂው ነው። »

እንዲህም ይላል።

« أليس الله بكاف عبده ويخوفونك بالذين من دونه… »

« አላህ ለባሪያው በቂ አይደለምን? ከእርሱ ውጪ (በታች በሆኑት ጣኦቶቻቸው) በሆኑት ነገሮች ያስፈራሩሃል። … »

اللهم افرغ على المجاهدين الصابرين الصبر وانصرهم على الظالمين الغاصبين

#الأقصى حياتنا

والموت في سبيلها اسمى امانينا

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ترجمہ ممکن نہیں

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮችን ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የክብር ዶ/ር ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የአውሮፓ ኡለሞች ህብረት ዋና ፀሀፊ ጋር በቢሯቸው ተወያዩ!

...

(ሀሩን ሚዲያ፦ጥቅምት 14/2016)

...

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮችን ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የክብር ዶ/ር ሼኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ የአውሮፓ ኡለሞች ህብረት ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ፋይድ ሙሀመድ ሰኢድ ጋር በቢሯቸው ተወያይተዋል።

...

የአውሮፓ ኡለማዎች ህብረት ዋና ፀሀፊ ለስራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ሲሆን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት እና ከፍተኛ አመራሮች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

...

በውይይታቸውም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ያለበት ሁኔታ እና ሁለቱ ተቋማት በጋራ ስለሚሰሩባቸው መንገዶች መነጋገራቸው ተገልጿል።

...

©ሀሩን ሚዲያ

image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
ترجمہ ممکن نہیں

4 views
Send as a message
Share on my page
Share in the group