UMMA TOKEN INVESTOR

redwan mekiyu shared a
Translation is not possible.

"ዓቂቃ"

አቂቃ ማለት አዲስ ለተወለደ ህፃን ልጅ የሚታረድ መስዋእት

የሚደረግ እርድ ነው። የተወደደ እና የተፀና የተከበደ ነቢያዊ ፈለግ

እርድ ነው።

“ዐቂቃ ማረድ በጣም የጠበቀ እና የተወደደ ሱና (ሱና ሙአከዳ)

ነው።

ምክንያቱም ነብዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል

"ማንኛውም ልጅ በ7ኛው ቀን በሚታረድለት ዐቂቃ የተያዘ ነው ።

ይህም ማለት ዐቂቃ የሚታረድለት ሕፃን ለወላጆቹ በቂያማ ቀን

ሸፈዐ ይሆናል ።ስሙ የሚወጣለትም ራሱንም (ፀጉሩን)

የሚላጨው በዛን ዕለት ነው።" ሲሉ መናገራቸውን ነው

(አቡዳውድ እና ነሳኢ) ዘግበውታል።

የዐቂቃ ዓላማው (የተደነገገበት) ምክንያት ለአላህ ሱብሃነሁ

ወተዓላ ምስጋና ለማድረስ ነው። ይህም አንድ ሰው ልጅ

ስለተወለደለት በመደሰት በ 7ኛው ቀን ደስታውን ለመግለፅ እና

ይህንንም ደስታውን ሰዎች እንዲያውቁት ለማድረግ እና

የተወለደውም ልጅ የማን እንደሆነ ለማሣወቅ ነውና አላህ ደግሞ

ልጁን እንደሚጠብቀው፣ሷሊህ ልጅ እንዲሆንለት ምክንያትም

እንዲሆነው የሚደረግ አርዶ ሰውን የማብላት ስርኣት # አቂቃ

ይባላል።

በአብዛኞቹ ሙስሊም ምሁራን እንዳሉት ዐቂቃ መደረግ ያለበት

ትልቅ ሱና (ሱና ሙአከዳ) ነው። እንደ አንዳንድ ምሁራን ደግሞ

ዐቂቃ ማድረግ ዋጅብ (ግዴታ) ነው የሚሉ ዑለማዎችም አሉ።

በላጩና የተመረጠው የዐቂቃ ማውጫ ጊዜም ልጅ በተወለደ

በሰባተኛው (7ኛው) ቀን ነው የሚሆነው።

☞ ወላጆች (እናትና አባት) አሊያም አያቶች ማለትም የወላጅ

አባት እና እናት ለልጃቸው አሊያም ለልጅ ልጃቸው ዐቂቃ

ማውጣት አለባቸው፣ይችላሉም።

የተወለደው ልጅ ወንድ ከሆነ ሁለት በግ(ፍየል) ሴት ከሆነች

ደግሞ 1 በግ(ፍየል) ሊታረድ ይወደዳል ።

ምክንያቱም ነብዩ ሙሐመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የአሊይ(ረዐ)

ልጅ ሐሰን በተወለደበት ጊዜ ሁለት በግ አርደዋል ።

(ቲርሚዚ ዘግበውታል)

እንዲሁም ስሙን ደህና ኢስላማዊ ስም በመምረጥ ሊጠራው

ይገባል።

ለምሳሌ ወንድ ከሆነ አብዱረህማን, አብዱላህ፣ሙሀመድ ወዘተ

....... ሴት ከሆነችም ደግሞ አሲያ፣ መሪየም፣ ኸዲጃ፣ ፈጢማ

ወዘተ......ብሎ ስም ቢያወጣላቸው ይወደዳል።

ሰባተኛው ቀን ያልታረደ እንደሆነ በ14ኛው ቀን ሊታረድ ይችላል

ያም ካልሆነ በ 21ኛው ቀን ቢያወጣ ችግር የለውም ይላሉ

ኡለማዎች፣

በአጠቃላይ አንድ ልጅ እስኪጎረምስ ድረስ አቂቃ ማውጣት

ይችላል የሚሉ ኡለማዎችም አሉ፣ እናም ቀኑ አልፎዋል ብለን

ይህን የጠበቀና የተወደደ የረሱል(ሰአወ) ሱና ከመተግበር

አንዘናጋ።

ምን አልባት ህፃኑ ሰባት ቀን ሳይሞላው የሞተ እንደሆነ ዐቂቃ

ማረዱ አስፈላጊ አይሆንም ብለዋል ኡለማዎች።

አንድ ሰው በህፃንነቱ ወላጆቹ አቂቃ ካላወጡለትና ትልቅ ሰው

ከሆነ በሁዋላ ና አቅሙ ካለው ጓደኞቹን ሰብስቦ አላማውን

ነግሯቸው(ዐቂቃ እንደሆነ ነግሯቸው) አቂቃ ማውጣት ይችላል

ብለዋል።( ኢብን ባዝ ረሂመሁላህ)

ስለዚህ እድሜያችን የፈለገ ያህል ቢሆንም አቂቃን ነይተን

ማውጣት እንችላለንና አንዘናጋ

የታረደው እንሠሣ ሥጋው በዒድ አል-አድሃ በዓል እንደሚደረገው

ሁሉ ሦስት ቦታ መከፈል አለበት። አንድ ሦስተኛው- ለድሃ፣ አንድ

ሦስተኛው- ለጓደኞች እና አንድ ሦስተኛው ደግሞ ለቤተሰብ

ይሠጣል።

አንድ ሰው የታረደውን ሥጋ ሁሉንም ለድሆችና ችግረኛ ሰዎች

መስጠት ይችላል።

ልጆች የአላህ ስጦታ ናቸው። እናም ይህን ታላቅ ፀጋ የሠጠንን

አላህን ማመስገን ይኖርብናል። ልጆችንም ገና ከህፃንነታቸው

ጀምሮ ልንንከባከባቸውና በኢስላማዊ አስተዳደግ እና ትምህርት

ያድጉ ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት ልናደርግላቸው ይገባል።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
redwan mekiyu Сhanged his profile picture
7 month
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
redwan mekiyu shared a
Translation is not possible.

ምዕራቡ አለም በብሪቴይን እርግዝና በፈረንሳይ አዋላጅነት በጥቅመኛ አረቦች አጨብጫቢነት የወለዷትን የግፍና የበደል ልጅ መጠበቅ ላይ መተባበር መያዛቸው ብዙ አያስገርምም። ታማኝነት አልባ፣ የሁለት ሚዛን ባለቤት ከሆኑት የግፍ መሪዎችና ልሂቃን ስብስብ ከዚህ የተለየ መጠበቅም የዋህነት ነው። ቅሉ ሁሉም ነገር ማብቂያ አለው፤ ሁሉም ነገር መጠናቀቂያ አለው።

★ ማብቂያውም ፍትህን ለተነፈጉት ሁሉ ብርሃን መሆኑ ነው። ወላዱም፣ ያዋለደውም፣ ያጨበጨበውም፣ የተወለደውም የበደልና የግፍ ልጅም መዋረዳቸው አይቀርም። በነፍሶቻቸው ውስጥ የነገቡት የበላይነትና ሁሉን አድራጊነት መንፈስ ቅዠት መሆኑ አይቀርም። የአላህ ቃል እንዲህ ይላል።

« إن الذين كفروا ينفقون أموالهم ليصدوا عن سبيل الله فسينفقونها ثم تكون عليهم حسرة ثم يغلبون… »

« እነዚያ የካዱት ሰዎች ከአላህ መንገድ ሊከለክሉ ገንዘባቸውን ያወጣሉ። በእርግጥም ያወጣሉ። (ካወጡም በኃላ) ፀፀት ትሆንባቸዋለች። ከዚያም ይሸነፋሉ። የካዱት ሰዎች ወደ ገሀነምም ይሰበሰባሉ።»

እንዲህም ይላል።

« …عسى الله أن يكف بأس الذين كفروا والله أشد بأسا وأشد تنكيلا »

« … አላህ የካዱትን ሰዎች ኃይል ሊከለክልልህ ይከጀላል (ይከለክልልሃል)። አላህም በኃይል ሲይዝ የበረታ፤ ቅጣቱም እጅግ ጠንካራ ነው። »

★ በተቃራኒው በበደል ውስጥ በትግልና በትእግስት፣ በትእግስትና በትግል ያለፉት ሁሉ የአላህ እርዳታ እየጨመረላቸው፤ እዝነቱንና እገዛውን እያሰፋላቸው፤ የድልን ካባ እንደሚያጎናፅፋቸው እርግጥ ነው።

ለተወዳጁ መልእክተኛው (ሰዐወ) አላህ እንዲህ ይላቸዋል።

« …فسيكفيكهم الله وهو السميع العليم »

« … ከእነርሱም (ከከሃዲያኑ) አላህ ይበቃሃል። እርሱ ሰሚና ዐዋቂው ነው። »

እንዲህም ይላል።

« أليس الله بكاف عبده ويخوفونك بالذين من دونه… »

« አላህ ለባሪያው በቂ አይደለምን? ከእርሱ ውጪ (በታች በሆኑት ጣኦቶቻቸው) በሆኑት ነገሮች ያስፈራሩሃል። … »

اللهم افرغ على المجاهدين الصابرين الصبر وانصرهم على الظالمين الغاصبين

#الأقصى حياتنا

والموت في سبيلها اسمى امانينا

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group