UMMA TOKEN INVESTOR

nuredin idris Сhanged his profile picture
1 years
Translation is not possible.
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
nuredin idris shared a
Translation is not possible.
ሙዓዊያ እና ዐሊይ ረዲየላሁ ዐንሁማ በተጋጩ ግዜ ሁለት
ኢስላማዊ ስረወ መንግስት ተመሰረተ የሮሙ ንጉስ ይህን ሰምቶ
እንዲህ ሲል ደብዳቤ ፃፈ።
<<ከሮም ንጉሰ ነገስት ለ ሙስሊሞች መሪ ሙዐዊያ አቡ ሱፍያን!!
ባንተ እና በዐሊይ መካከል የተከሰተውን ግጭት
ሰምተናል።ስለዚህም ለሙስሊሞች መሪ አንተ መሆን
እንዳለብህም ስለምናምን አንተ ፍቃድህ ከሆነ የዐሊይን ጭንቅላት
ቀንጥሶ የሚያመጣልህን ወታደር ልላክልህ>>
ይህ ደብዳቤ ሙዐዊያ ጋር እንደደረሰም ሙዓዊያም
<<ከሙዓዊያ ለሮም መሪ!!! ሁለት ወንድማማቾች ስለተጣሉ
አንተ ምን አገባህ? አፍህን የማትዘጋ ከሆነ ጅማሬው እኔ ጋ የሆነ
እና ፍፃሜው አንተ ጋ የሆነ ሰራዊት ልኬ አንገትህን በማስቀንጠስ
ለዐሊይ በስጦታ መልኩ አበረክትለታለሁ>>
#ይህ_ትክክለኛ_ሙስሊሞች_ሳለን_ነው
_____
___
ካሊድ ኢብን ወሊድ ለፐርሺያው ንጉሰ ነገስት እንዲህ ሲል
ደብዳቤ ፃፈለት
<<ስለም ትድናለህ። እንቢ ያልክ እንደሆን ግን፤ እናንተ ህይወትን
የምትወዱትን ያህል ሞትን የሚወዱ ሰራዊቶችን ይዤልህ
እመጣለሁ።>>
ንጉሱ ይህን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ የቻይናውን ንጉስ የጦር እርዳታ
ሊለምነው ደብዳቤ ፃፈለት።
የቻይናውም ንጉስ እንዲህ ሲል ደብዳቤ መልሶ ላከለት።
<<ንጉስ ሆይ! ተራራን እንኳን ለመናድ ካሰቡ ምንም
ከማያግዳቸው ወታደሮች ጋር ለመጋፈጥ አቅሙ ስለሌለኝ
ጥያቄህን መፈፀም አልችልም።>>
# ምን_ያህል_ሀያላን_እንደነበርን_ተመልከቱ
_____
____
በደውለቱል ዑስማኒያ የአገዛዝ ዘመን የሙስሊም ወታደሮች የጦር
መርከቦቻቸውን ይዘው በአውሮፓ ደሴቶች ሲያልፉ በአከባቢው ያሉ
አብያተ ክርስትያናት በሙሉ ሙስሊሞች መጥተው ፈትህ
እንዳያደርጉ በመፍራት ከበሮ ከመምታት እና ምንም አይነት ድምፅ
ከማሰማት ይቆጠቡ ነበር።
#ያኔ_ጀግና_ሳለን
_____
____
በደውለቱል ኡስማኒያ የአገዛዝ ዘመን በያንዳንዴ ቤት ደጅ ላይ
ሁለት የበር ማንኳኩያዎች ይኖራሉ። አንዱ ትልቅ ሲሆን አንዱ ትንሽ
ነው። በትልቀኛው ከተንኳኳ አንኳኪው ወንድ ነው'ና በሩን ሊከፍት
ሚመጣው ወንድ ይሆናል። ነገር ግን በትንሸኛዋ ከተንኳኳ
አንኳኪዋ ሴት መሆኗ ስለሚታወቅ ሴት ትከፍትላታለች።
በዚያ ምርጥ ዘመን አንድ ቤት ውስጥ ሰው ከታመመ ደጅ ላይ
ቀይ አበባ ይንጠለጠል ነበር። ያን አበባ የተመለከቱ ሰዎች ሁሉ
እዝያ ቤት በሽተኛ መኖሩን ስለሚያውቁ በበሩ ሲያልፉ ድምፃቸውን
ዝቅ ያደርጉ ነበር።
#ሹፍ_ምን_እንመስል_እንደነበር !!!
_____
_
ግዜው ሰላሁዱን አል አዩቢ በይተል መቅዲስን ባስመለሰበት ግዜ
ነበር። እና ጦርነቱ ነገውን ሊጀመር ማታ ላይ የጦር መሪው
ሰላሁዲን የወታደሮቹን ድንኳን እየዞረ ሲያዳምጥ፤ ግማሹ ለይል
ይሰግዳል፣ ሌላው ቁርአን ይቀራል፣ የተቀሩት ደግሞ ይዘክራሉ።
ግን ድንገት በሆነ ድንኳን አጠገብ ሲያልፍ በድንኳኑ ውስጥ ያሉት
ሁሉም ተኝተው ነበር። ይህን ግዜ፦"በዚህች ድንኳን አዳሪዎች
ምክንያት ልንሸነፍ እንችላለን" ብሎ አለፈ።
#ማንተኛበት_ዘመን
_____
___
ቀደምት ዑለማኦች በሶስት ነገራት አደራ ይባባሉ ነበር።
1፦ሰውዬው በሱ እና በአላህ መካከል ያለውን ግንኙነት ካሳመረ፤
በሱ እና በሌሎች መካከል ያለው ግንኙነት ያምርለታል።
2፦ሰውዬው ሚስጥራዊ ተግባሩን ካሳመረ አላህ ይፋዊ ተግባሩን
ያሳምርለታል።
3፦ሰውዬው የአኪራው ጉዳይ ካስጨነቀው አላህ የዱንያውንም
የአኪራውንም ጉዳይ ያግራራለታል።
_____
_
#ትልቁ_ኪሳራ_ማለት_ይህ_ነው
ጀነት ስፋቷ የምድርን እና የሰማያትን ያህል ሁና ላንተ በሷ ቦታ
ሳይኖርህ ሲቀር...ትልቅ ኪሳራ ነው።
በእለታዊ ፕሮግራምህ ውስጥ ቁርአንን መቅራት ካልተካተተ ትልቅ
ኪሳራ ነው።
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
nuredin idris shared a
Translation is not possible.
እናትና ልጅ በጠባቧ ክፍላቸው ውስጥ ተቀምጠዋል።
"እማ ርቦኛል" አለ ዩሱፍ ሆዱን እያሻሸ።
"ሀቢቢ ትንሽ ጠብቀኝ ቲማቲም ስልስ እሰራልሃለሁ" አለች እናት ፀጉሩን እያሻሸች።
ቤት ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ ባለመኖሩ የዩሱፍን ርሐብ ለማስታገስ ሁለት የቲማቲም ዘለላዎችን ፍለጋ ከቤት ወጣሁ። በበር በኩል አጮለቅኩና እስክመለስ በሩን እንዲዘጋ ነገርኩትና ወደ ጎረቤታችን ቤት አቀናሁ። ደጋግሜ አንኳኳሁ። መልስ የሚሰጠኝ አላገኘሁም። ከመንገዱ ማዶ ወደሚገኘው ወደ ኡሙ ሚቅዳድ ቤት አመራሁ።
አንኳኩቼ ገባሁ። እንዴት ነሽ ልጆችሽስ ብዬ ሰላምታን አቀረብኩላት።
"አልሀምዱሊላህ ደህና ነን አላህ ይጠብቀን" ብላ መለሰችልኝ።
እያንዳንዱ ሰከንድ የመጨረሻ ሊሆን ይችላልና እኛ ፍልስጤማዊያን ጦርነት ውስጥ ስንሆን እንዲህ ነን ብዙ አንናገርም።
"ባለቤቴ ውሎ አዳሩ ሆስፒታል ሆኗል። ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ወደ ቤት አልተመለሰም። አልሐምዱሊላህ" አልኩና ቲማቲም ካላት እንድትሰጠኝ ጠየቅኳት። በፌስታል ቋጥራ ያቀበለችኝን ቲማቲም ይዤ ልወጣ ስል "ሁኔታዎች ከባድ ሆነዋል በዱዓ እንተዋወስ" አለችኝ።
"በአላህ እርዳታ ይህ ሁሉ ያልፋል ኢንሻ አላህ..." እያልኳት ገና ንግግሬን ሳልጨርስ ከባድ ፍንዳታ ተሰማ። በጥቁር ደመና አየሩን ተሸፈነ። አካባቢው በአቧራ ተሞላ። አእምሮዬ የዩሱፍን ስም አቃጨለ። ከራሴ ጋር እየታገልኩ ወደ ጎዳናው ሮጥኩ። ሁሉም ይጮኻል።
ዩሱፍን አይታችዋል..? እዚህ አካባቢ አንድ ትንሽ ፍሪዝ የሆነ ልጅ አጊኝታችኋል? እያልኩ ጮኽኩ። መልስ የሰጠኝ ማንም አልነበረም። በአንቡላንስ ተጭኜ ሄድኩ። የመኪናው በር ሲዘጋ በዩሱፍ ላይ የዘጋሁት በር ታወሰኝ።
እየተብሰለሰልኩ አሽ-ሺፋእ ሆስፒታል ደረስኩ። ዩሱፍ....የሱፍ.... ብዬ ተጣራሁ። ለአላፊ አግዳሚው የ7 አመት ቆንጅዬ ልጄን አይታቹታልን? እያልኩ ጠየቅኩ።
የዓይኔ ማረፍያ ባለጥቅልል ፀጉሩ ጥቃቱ ፊቱን ከማበላሸቱ በፊት ቆንጆ ምስሉን በአእምሮዬ ሳልኩ። ፍርስራሽ አቧራ ከሰውነቱ ጋር ተጣብቆ በደም ተጨማልቆ አልጋ ላይ ተንጋሎ አገኘሁት። ዩሱፍ በባዶ ሆዱ ጌታውን ተገናኘ።
@STRONG_IMAN
@STRONG_IMAN
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
nuredin idris Сhanged his profile picture
1 year
Translation is not possible.
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group