Seyfedin Munir Profile Picture
UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ሶስት ፍልስጤማውያን ተማሪዎች በአሜሪካ ካምፓስ አካባቢ ተተኮሰባቸው

በአሜሪካ ቬርሞንት ቅዳሜ እለት ሶስት የፍልስጤም ተማሪዎች  የጥይት ጥቃት ሰለባ የሆኑ ሲሆን የጥላቻ ወንጀል ስለመሆኑ ፖሊስ እንዲያጣራ የተጎጂ ቤተሰቦች አሳስበዋል። ሂሻም አዋርታኒ፣ ታህሲን አህመድ እና ኪናን አብዳልሃሚድ በቨርሞንት ካምፓስ አቅራቢያ ከአንድ ሰው ጋር ፀብ ውስጥ ከገቡ በኃላ በጥይት መመታተቸውን የበርሊንግተን ፖሊስ ተናግሯል። የፖሊስ መኮንኖቹ ምክንያቱን በማጣራት ላይ ሲሆን ጥቃት ሲደርስባቸው ኬፊዬ የተሰኘውን ባህላዊ ስካርፍ ለብሰው እና አረብኛ እየተናገሩ ነበር ብለዋል።

ፖሊስ ተጠርጣሪውን በማፈላለግ ላይ ይገኛል። የበርሊንግተን ፖሊስ አዛዥ ጆን ሙራ ሁለቱ ተጎጂዎች በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን በመግለፅ ሦስተኛው በጣም የከፋ ጉዳት ደርሶበታል ሲሉ ተናግረዋል።ሦስቱም ተጎጂዎች በራማላህ ትምህርት ቤት ተምረዋል፣ የቤተሰብ አባላት እንደተናገሩት ደግሞ አብዳልሃሚድ፣ በሃቨርፎርድ ኮሌጅ መማሩን ገልፀዋል። የተቀሩት ሁለቱ በብራውን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ትሪኒቲ ኮሌጅ ገብተው ሲማሩ ነበር። ከተጎጂዎቹ የአንዱ አጎት የሆኑት ሪች ፕራይስ፣ ሦስቱ በ20ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ እና የስምንት ዓመት ልጅ የልደት ድግስ ላይ ከጥቃቱ በፊት ተገኝተው ነበር ብለዋል።

ከቤታችን ከወጡ ከአምስት ደቂቃ ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የአምቡላንስ የሳይረን ድምፅ መሰማቱን የተጎጂዎቹ ቤተሰቦች ተናግረዋል።ይህንን ጥቃት እንደ ጥላቻ ወንጀል መቁጠርን ጨምሮ የህግ አስከባሪ አካላት ጥልቅ ምርመራ እንዲያደርጉ እንጠይቃለን ሲሉ አክለዋል። አጥቂው ግለሰብ ለፍርድ እስካልቀረበ ድረስ ምቾት አይኖረንም ሲሉ ተደምጠዋል። የአሜሪካ እስላሚክ ግንኙነት ምክር ቤት ተጠርጣሪው ማን እንደሆነ መረጃ ለሚሰጠን የ10,000 ሺ ዶላር ጉርሻ እሰጣለሁ ሲል አስታውቋል።

የቬርሞንት ሴናተር እና የቀድሞ የዴሞክራት ፕሬዚዳንታዊ እጩ በርኒ ሳንደርስ ጥቃቱን አውግዘዋል። ሳንደር በኤክስ ላይ ባሰፈሩት መልዕክት  “ሦስት ወጣት ፍልስጤማውያን እዚህ ቡርሊንግተን ቨርሞንት ውስጥ በጥይት መመታቸው አስደንጋጭ እና እጅግ አሳዛኝ ነው። ጥላቻ እዚህም ሆነ በየትኛውም ስፍራ ቦታ  የለውም” ብለዋል። በዩናይትድ ኪንግደም የፍልስጤም ሚሲዮን ኃላፊ አምባሳደር ሁሳም ዞምሎት የሶስቱን ወጣቶች ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በማጋራት “በፍልስጤማውያን ላይ እየተፈጸመ ያለው የጥላቻ ወንጀሎች መቆም አለባቸው” ሲሉም አክለዋል።

umma life news

-seya_smoke

don't forget #follow and #like

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ዱኒያ... የፈተናዎች አዳራሽ!

በዚህች ምድር ላይ ሲኖር የማይፈተን ማንም የለውም። ልዩነቱ ያለው የፈተናው ዓይነትና ብዛት ላይ ብቻ ነው።

በተለያየ መልኩ ልንፈተን እንደምንችል አላህ   سبحانه وتعالى ምሎ ነግሮናል

▪በፈተና ጊዜ የማይታገሱን አውግዟል የጌታቸውን ውሳኔ ወደው የሚቀበሉና የሚታገሱትን አወድሷል በዚህች ምድርም መጨረሻቸው እንደሚያምርና በቀጣዩ ዓለም ህይወታቸውም እጥፍ ድርብ ምንዳ እንደሚለግሳቸው ቃል ገብቷል።

💥እንደሚፈተኑና ፈተናዎች ውስጥ መሆንን አለማወቅ እራሱ አንድ ፈተና ነው።

▪ከፈተናዎች ሁሉ ከባዱ ፈተና ደግሞ ዋና ሃብታችን የሆነው እምነታችንን(ዲናችንን) የሚጎዳ ፈተና ነው።

ከዚህ ውጭ ያሉ ፈተናዎችን በሙሉ በአላህ እገዛ ተቋቁሞ ማለፍ ይቻላል ቢወድቁና ቢሰናከሉም ዳግም የመነሳት እድል ይኖራል ምክንያቱም የዲን ገመዱ ጠንካራ የሆነ ሰው ወድቆ አይቀርምና ነው!

▪ሌሎች ፈተናዎች ሲበዙብን ወደ አላህ በመሸሽ የዲን/የኢማን ምሽግ ውስጥ በመግባት መዳን እንችላለን

ዲናችንን የሚያደክም ፈተና ከበዛ ግን መሸሻ

እናጣለን ለዚህም ነው ፥

( ولا تجعل مصيبتنا في ديننا)

"አላህ ሆይ፥ የሚደርስብንን ችግር ዲናችን ላይ ያነጣጠረ አታድርግብን" የሚለው ዱዓ ከተመረጡ ዱዓዎች መካከል አንዱ የሆነው።

ህመም፣ድህነትና ረሃብ ወዳጅን በሞት ማጣትና የህይወት አለመረጋጋት ወዘተ ዱኒያ ላይ ሊገጥሙን የሚችሉ *ፈተናዎች* ናቸው

▪ማጣት ብቻ ሳይሆን ማግኘትም ፈተና ነው!

▪መታመም ብቻ ሳይሆን ሁሌ ጤነኛ መሆንም ፈተና ነው!

▪አላዋቂነት ብቻ ሳይሆን ማወቅም ፈተና ነው

በጥቅሉ፥ ዱኒያ ላይ ያለ ነገር በሙሉ ፈታኝ ነው ማለት ይቻላል!

ለዚህም ነው ጌታችን አላህ፥

(إِنَّا جَعَلْنَا مَا عَلَى الْأَرْضِ زِينَةً لَهَا لِنَبْلُوَهُمْ أَيُّهُمْ أَحْسَنُ عَمَلًا)[سورة الكهف 7]  ያለው

ሁሉም የሰው ልጅ  የፈተና ድርሻ እንዳለው አውቆ ማደርና ተራችን ሲደርስም በትዕግስትና አላህን በመመካት ከችግሮች ለመውጣት መጣር ተገቢ ነው።

اللهم لا تجعل مصيبتنا في ديننا

ولا تجعل الدنيا أكبر همنا ولا مبلغ علمنا ولا إلى النار مصيرنا

واغفر اللهم لنا ولوالدينا

ومن خزي الدنيا وعذاب الآخرة أجرنا

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

👉ክፍል አራት

↝የትንሹ ዚና አደገኝነት

በዑለሞች አተያይ የእጅ ዚና ሲባል የዘመኑ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ባዳ(አጅ ነቢ)ሴቶችና ወንዶች የሚጻጻፉትና የሚላላኩት የተለያዩ ሕገወጥ መልዕክቶችም በዚህ ውስጥ ይጠቃለላሉ፡፡! በተለያዩ መንገዶች ቴክስት ሜሴጆችን የሚጽፉ ጣቶችም ከእጅ ይቆጠራሉ፡፡ የሞባይል ስክሪኖችን የሚነካኩና ቻት ሴክስን፣ ፎን ሴክስንና የወሲብ ፊልምን ሳይቀር ጠቅ ጠቅ የሚያደርጉ ጣቶችም በዚሁ ውስጥ ይካተታሉ፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ይህ እውነታ ወደ ዓይን ዚና፣ ወደ ምላስ ዚና፣ ወደ ጆሮ ዚናና ወደሌሎችም ሁሉ በየፊናቸው በሚኖራቸው ተሳትፎ ልክ ይለጠጣታል፡፡❗️

     👉 ⑤/ የእግር ዚና አደገኛነት

አንድ የአላህ(ﷻ)ባሪያ መልካም ነገርን ለመሥራት ሲሄድ በተራመደ ቁጥር አጅር ያገኛል፡፡ የእግሮቹ ዱካ ያረፉበት ቦታ ሁሉ ይጻፍለታል፡፡ ይህንኑም ቀጥሎ ካለው ቁርኣናዊ አንቀጽ መረዳት ይቻላል፡፡

Surah Ya-Sin (يس), verses: 12

إِنَّا نَحْنُ نُحْىِ ٱلْمَوْتَىٰ وَنَكْتُبُ مَا قَدَّمُوا۟ وَءَاثَٰرَهُمْ وَكُلَّ شَىْءٍ أَحْصَيْنَٰهُ فِىٓ إِمَامٍ مُّبِينٍ

እኛ ሙታንን እኛ በእርግጥ ሕያው እናደርጋለን፡፡ ያስቀደሙትንም ሥራ ፈለጎቻቸውንም እንጽፋለን፡፡ ነገሩንም ሁሉ ገላጭ መሪ በኾነ መጽሐፍ ውስጥ አጠቃለልነው፡፡

በዚህ አንቀጽ ውስጥ «ወኣሣረሁም»(ፈለጎቻቸውንም) የሚለውን ቃል አንዳንድ ዑለሞች ሲተረጉሙት የእግሮቻቸውን ፋና(ዱካ)ማለት ነው ይላሉ፡፡

በዚሁ መሠረት አንድ ሰው ወደ ኸይርም ሆነ ወደ ሸር ሲራመድ እርምጃው ሁሉ ይመዘገባል፡፡ ግለሰቡ ወደ ሸር ሲራመድም የእግር ወለምታ አጋጥሞታል ይባላል፡፡ የእግር ወለምታ ደግሞ ልክ እንደ ምላስ ወለምታ ሁሉ ከባድ ነው፡፡ አላህ(ﷻ)በሱረቱል ፉርቃን ውስጥ ስለ ዲባዱር-ረሕማን ባህሪያት በተናገረባቸው አንቀጾች ውስጥ እነርሱ በንግግራቸውም ሆነ በእርምጃቸው ትክክለኞችና ቀጥተኞች እንደሆኑ ግልጿል፡፡ አላህ(ﷻ)እንዲህ ይላል፡-

Surah Al-Furqan verses: 63

وَعِبَادُ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلَّذِينَ يَمْشُونَ عَلَى ٱلْأَرْضِ هَوْنًا وَإِذَا خَاطَبَهُمُ ٱلْجَٰهِلُونَ قَالُوا۟ سَلَٰمًا

የአልረሕማንም ባሮች እነዚያ በምድር ላይ በዝግታ የሚኼዱት፣ ባለጌዎችም(በክፉ) ባነጋገሩዋቸው ጊዜ ሰላም የሚሉት ናቸው፡፡

      (አላህ የላቀና ይበልጥ አዋቂ ነው)

  ኢንሻ አላህ 👉 የልብ ዚና አደገኛነት ይቀጥላል

ከእነዚህን የሸይጧን ወጥመዶች ራሳችንን ቁጥብ ካደረግን ከብዙ መጥፎ መዘዞች እንርቃለን ነገር ግን እንደ ቀልድ ምንዳፈራቸው ከሆነ መጨረሻው መጥፎ ነው ሚሆነው።

ሁላችንም በምንችለው በውስጥ መስመር ለጓደኞቻችን ሼር እናድርግላቸው።

      👉 ሼር ሼር ሼር ሼር ሼር

https://t.me/menhaj_Asselefiy101A

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

"ኦኛም ተራ በተራ እየተጠባበቅን ነው"።

የጋዛ ፍልስጤማውያን ጋዜጠኛ በእስራኤል ጥቃት አንድ የሥራ ባልደረባው ከተገደለ በኋላ የቀጥታ ዘገባውን ሲያቀርብ የመከላከያ ልብሱን አውልቆታል።

እስቲ ላይክ እና ሼር በማድረግ አጋሩት!!

“We are waiting for our turn, one after the other.” A Palestinian journalist from Gaza ripped off his protective gear during a live report after one of his colleagues was killed in an Israeli attack.

image
image
image
image
image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group