UMMA TOKEN INVESTOR

About me

Allahmdulilah for everything

Translation is not possible.

ጀግንነት ሁል ጊዜ በመናገር አይደለም፣ ጥበብም ሁል ጊዜ በዝምታ ውስጥ አይደለችም። አላህ ዘንድ ያለውን ምንዳ ከጅለው በዒልም ለሚናገሩ እና በጥበብ ዝም የሚሉ ሁሉ የአላህ እዝነት በነርሱ ላይ ይሁን።

✍አሸይኽ ሱለይማን አር–ሩሓይሊ ሐፊዘሁላህ

ከቲውተር ገፃቸው የተወሰደ

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

በመንሀጃቸው ሳይዋልሉ ለፀኑት እህቶቼ ብቻ!!

«የሴትነት ሞራል»

----------------------------

በነገ ተስፋ ላይ እቅዷን ሰንቃ፡

ሁሉን እየቻለች ችግሮችን ንቃ፡

መንሀጀ ሰለፍ ላይ ህልሞቿን ሰክካ፡

አንድ ጊዜ ስትቆርጥ ሽ ጊዜ ስትለካ፡

እንደነ-ኸድጃ ደግሞ እንደ በረካ፡

በዱንያዊ ወረት በጌጦች ሳትረካ፡

ሴትነት እንደዚህ ተዓምር ነው ለካ!!

-----------------------------------

በነበር ለሚከስም ለዱንያ ፈተና ብዙ አትጨነቂ፡

አሳዛኙ ጊዜ አስለቃሹ ክስተት እንደሚያልፍ እወቂ፡

ዘወትር አይኖርም ታሪክ ይቀየራል፡

ነገ በአሏህ ፈቃድ ጨለማው ይበራል፡

የሙስሊሞች ጠላት ሙቶ ይቀበራል፡

--------------------------------

«ቢሆንም አንች ግን.....»

ማለፍ ይልመድብሽ መከራን በፅናት፡

ለሌሎች አሳቢ ጀግና ሁኝ እንደ እናት፡

በፈገግታሽ ውበት ጠላት አሸንፊ፡

እቅድሽ ይሳካል አይዞሽ አትከፊ፡

------------------------------

ወርቅ ነው አምሳያው ሲፈተን ያበራል፡

ሞገስና ግርማው መልኩ ይጨምራል፡

ሚስጥሩ ረቂቅ ነው የሴትነት ሞራል፡፡

---------------------------------

ከሰለፍያ መንደር Copy🌹🌹🌹🌹🌹

----------------------------------

Send as a message
Share on my page
Share in the group
hikma kasim shared a
Translation is not possible.

በአንድ ወቅት በአውሮፓ አየር መንገድ የመጀመሪያ ደረጃ ክፍል

(Buisness Class) ውስጥ የተቀመጠ አንድ ሙስሊም ወጣት

ተሳፋሪ ነበር፡፡

በጉዞ ላይ ሳለ ከአውሮፕላኑ አስተናጋጆች አንዷ ለዚህ ሙስሊም

ወጣት የነፃ መጠጥ ይዛለት መጣች፡፡

መጠጡ የአልኮል መጠጥ ስለነበረ ሙስሊሙ ወጣት

አልተቀበለም፡፡

አስተናጋጇም ከመጠጫው ችግር ይሆን በሚል በሚስብና

በሚያምር ዲዛይን በተሰራ የመጠጥ ማቅረቢያ በድጋሚ ይዛለት

መጣች፡፡

ሙስሊሙ ወጣት የአልኮል መጠጥ እንደማይጠጣ በመናገር

አሁንም አልተቀበለም፡፡

አስተናጋጇ ጉዳዩ አሳሰባትና ለአውሮፕላኑ ማናጀር አሳወቀች፡፡

ማናጀሩ ይበልጥ ባሸበረቀ እቃ መጠጡን ይዞ መጣና ቀርቦ

ያናግረው ጀመር

“ወንድም በአገልግሎታችን ላይ ችግር አለ ወይ ሲል ጠየቀውና

ይህ ነፃና የጉዞ መክፈቻ መጠጥ ነው፤ እባክህ ጠጣ እንጂ” ሲል

ጠየቀው

ወጣቱ ሙስሊም “እኔ ሙስሊም ነኝ አልኮል መጠጥ አልጠጣም”

በማለት መለሰ፡፡

ማናጀሩ መጠጡን እንዲወስድ አሁንም መወትወቱን ቀጠለ. . .

ወጣቱ ሙስሊም “ማናጀር መጠጡን መጀመሪያ ለአውሮፕላን

አብራሪው ስጡት” አለ፡፡

ማናጀሩ “እንዴት አብራሪ እያበረረ አልኮል ይጠጣል? እሱኮ

ተልዕኮ ላይ ነው፡፡ አውሮፕላኑ እንዲከሰከስ ትፈልጋለህ ወይ ሲል

ጠየቀው ?” ወጣቱ ሙስሊም ረጋ ባለ አነጋገር “እኔ ሙስሊም ነኝ

ሁሌም ተልዕኮ ላይ ነኝ፡፡

ኢማኔን የመጠበቅ የሁልጊዜም ተልዕኮዬ ነው፡፡ ከጠጣሁ

የዚህንም የመጪውንም ሀገሬን ነው ማበላሸው” የሚል

የማያዳግም ምላሽ ሰጠው፡፡

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
hikma kasim shared a
Translation is not possible.

አንድ ትንሽዬ ልጅ ለወላጆቹ፦"3 ጥያቄዎቼን የሚመልስልኝ

ጠንካራ ዑለማ አምጡልኝ" አላቸው።

ወላጆቹም በአከባቢያቸው ያለ አንድ ኡስታዝ አመጡለትና

አገናኙት።

💧ልጁ፦"ማን ነህ አንተ? እኔ ስለምጠይቀውስ ጥያቄ መልስ

እንዳለህ ምን ያህል እርግጠኛ ነህ?"

➣ኡስታዙ፦"ስሜ ዐብዱላህ ይባላል ከአላህ ባሪያዎችም አንዱ

ነኝ።ለምትጠይቀኝ ጥያቄዎችም በአላህ ፍቃድ መልስ

እሰጥሀለሁ።"

💧ልጁ፦"አንተ ግን ብዙ ዑለማኦች ሊያብራሩልኝ ያልቻሉትን

ጥያቄዬን እንደምትመልስልኝ ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነህ?

➣ኡስታዙ፦"ልመልስልህ እሞክራለሁ በአላህ እገዛ።"

💧ልጁ፦" 3 ጥያቄዎች አሉኝ።

❶ ➛ እውነት ፈጣሪ አለ? አዎ አለ የምትል ከሆነ አሳየኝ የት ነው

ያለው?

❷ ➛ ቀዷ እና ቀደር ምንድነው?

❸ ➛ እውነት ሸይጣን ከእሳት የተፈጠረ ከሆነ እንዴት በእሳት

ይቀጣል? ከእሳት ተፈጥሮ እሳት አያቃጥለውም።

"ይሄን ግዜ ኡስታዙ እሳት በሆነች ጥፊ ልጁን አጮለው።

💧ልጁ፦"እንዴ!!! ለምን ትመታኛለህ? ምን ሚያስመታ ነገር

ተናገርኩ?

➢ኡስታዙ፦"አረ!!! እኔ አልተቆጣሁም ግን ያሁኗ ጥፊ ለሶስቱም

ጥያቄዎችህ መልስ ናት።

💧ልጁ፦"እንዴት? አልገባኝም...

➢ኡስታዙ፦"በጥፊ ስመታህ ምን ተሰማህ?

ልጁ፦"በጣም ህመም ተሰማኝ።

➢ኡስታዙ፦"ህመም እንዳለ ታምናለህ?"

💧ልጁ፦"አዎ አምናለሁ።"

➢ኡስታዙ፦"አሳየኝ የት ነው ያለው?"

ልጁ፦"አይ አለ ግን ማየት እንኳን አይቻልማ"

➢ኡስታዙ፦"ይህ ለመጀመሪያ ጥያቄህ መልስ ነው።ሁላችንም

አላህ እንዳለ እናምናለን ነገር ግን ማየት አንችልም።

እሺ ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ ገምተህ ነበር?"

ልጁ፦"አልገመትኩም።"

➢ኡስታዙ፦"እሺ እኔስ አንተን ዛሬ እንደምመታህ ትናንት ማታ አስቤ

ነበር?

💧ልጁ፦"አላሰብክም።"

➢ኡስታዙ፦"ለ2ኛ ጥያቄህ መልስ ይህ ነው ቀዷ ቀደር

የሚባለው።

እሺ እኔ አንተን የመታሁበት እጄ 💧ከምንድነው የተፈጠረው?"

ልጁ፦"ከአፈር"

➢ኡስታዙ፦"እሺ በእጄ የመታሁት ያንተ ፊትስ ከምንድነው

የተፈጠረው?"

ልጁ፦"ከአፈር"

➢ኡስታዙ፦"ስመታህ ምን ተሰማህ?"

💧ልጁ፦"አመመኝ"

➢ኡስታዙ፦"ከአፈር የተሰራ አፈርን ሲመታው

እንደሚያሳምመው ሁላ ከእሳት የተሰራውም ሸይጣን በእሳት

ሲቀጣ በጣም ያመዋል።"

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

አንደሉስ ሲከፈት የሙስሊም ሰራዊቶች

አስራ ሁለት ሺህ ነበሩ ተባለ;

አንደሉስ ስትወድቅ ግን በውስጧ በሚሊየን የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ነበሩ።

  ቁም ነገሩ፦ የኢማን ጥንካሬ እንጂ

  የቁጥር ብዛት አ ይ ደ ለ ም!!

Send as a message
Share on my page
Share in the group