UMMA TOKEN INVESTOR

Translation is not possible.

ሙስሊም አማራ አለ ግን?

~

በተያያዘው ቪዲዮ ላይ የሚታዩት ማኅበረ ደና ቁራ ን እንደሚያስተጋቡት የአማራ ህዝብ የአይሁድ ነገድ አይደለም። ይሄ ፍጥጥ ያለ ውሸት ነው። እንዲያውም "የአይሁድ ነገድ ነን" የሚል አካል በራሱ ላይ "መጤ ነኝ" ብሎ እየመሰከረ ነው። በርግጥ መጤነት የሰለጠኑ ሰዎች ዘንድ ነውር አይደለም። ነውር የሚሆነው በመጤነታቸው የሚኮፈሱ አካላት ሌሎችን "መጤዎች" እያሉ ሊያነውሩ ሲሞክሩ ነው። እንዲህ አይነቶቹን ነውር ጌጡዎች በ"ነውራችሁ" አታጊጡ ብለን እናስታውሳለን።

መታወቅ ያለበት ሐቅ ብሄርና ቋንቋ በዘመናት ውስጥ ውልደት፣ እድገትና ሞት ያስተናግዳሉ። አንድ የነበረ ቋንቋ በአካባቢ መለያየትና መራራቅ የተነሳ በሂደት የተለያየ ቋንቋ ወደመሆን ሊቀየር ይችላል። ይሄ ውልደት ነው። ከሌሎች ቋንቋዎች እየወሰደ የሚዳብርና የሚሰፋም አለ። የቋንቋ እድገት አንዱ መገለጫ ይሄ ነው። የተለያዩ ቋንቋዎች በሌሎች ተውጠው ሊጠፉም ይችላሉ። ይሄ የቋንቋ ሞት ነው። በውጭው በእንግሊዝኛ፣ በፈረንሳይኛ፣ በዐረብኛ፣... ተውጠው ብዙ ቋንቋዎች ሞተዋል። በሃገራችንም የከሰሙና በመክሰም ላይ ያሉ ቋንቋዎች አሉ።

የአማራ ብሄርና ቋንቋም በዘመናት ውስጥ ሌሎች ህዝቦች የቋንቋው ተናጋሪ በሆኑ ቁጥር እየሰፋ የመጣ ቅይጥ ማንነት ነው። የጋፋት ቋንቋ በዚህ ዓይነት ሂደት ጠፍቷል። የአርጎባ ህዝብ የራሱን ቋንቋ ጥሎ የአማርኛና የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ ሆኗል። ይሄ የአማርኛ ብቻ ሳይሆን የብዙ ቋንቋዎች የጋራ ባህሪ ነው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በታሪክ አማራ የሚለው ቃል ክርስቲያን ማለት እንደነበር እስከ ቅርብ ጊዜ የሚታወቅ ነው። ይህ የሆነው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪው በአመዛኙ ክርስቲያን በመሆኑ እንጂ አማራነት በራሱ ክርስትና ስለሆነ አይደለም። ብሄር ማለት የጋራ ቋንቋና ማንነት ያላቸውን ህዝቦች ለመግለፅ እስከዋለ ድረስ በእምነት ቢለያዩም አማርኛ ቋንቋ የሚያገናኛቸው ህዝቦች አሉ፣ ዛሬ። ትኩረቴ አማራ ከሚለው ጥሬ ቃል ላይ አይደለም። ወደ ኋላ ረዘም ያለ ዘመን ብንመለስ ብዙ ብሄሮችን የዛሬ ስማቸውን ከነ ጭራሹ አናገኝም። ይሄ ማለት የጋራ ማንነት አልነበረም ማለት አይደለም።

ስለዚህ ዛሬ የትናንቱ የአማራነት ፅንሰ ሃሳብ የለም። አማራ ማለት ዛሬ ብሄር እንጂ ሃይማኖት ገላጭ አይደለም። በብሄር መለኪያ ከአማርኛ ተናጋሪው ክርስቲያን ጋር አንድ የሆኑ ሙስሊሞችን "አማራ አይደላችሁም" አይባልም። ብሄሩ ውስጥ የመሸጉ ገፊ አካላት መኖራቸውም የሚቀይረው ነገር የለም። "ትግሬ ብሎ ሙስሊም የለም" ብለው የሚያምኑ አግኣዚያን ስለኖሩ ሙስሊም ትግሬዎችን ትግሬነታቸውን መግፈፍ አይቻልም። "የኦሮሞ ነባር እምነት ዋቄፈና ነው" የሚሉ አካላት ስላሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሙስሊምና ክርስቲያን ኦሮሞዎችን ኦሮሞነታቸውን መግፈፍ ይቻላል? አይሆንም። በብሄርና በቋንቋ የለየንኮ ፈጣሪ እንጂ ፖለቲከኞች አይደሉም። ከአፋር ቤተሰቦች የተወለደን አካል አፋርነቱን መፋቅ ይቻላልን? እንኳን ሌሎች ራሱም መቀየር አይችልም። የአማራ ሙስሊሞችም ጉዳይ እንደዚያ ነው።

ጉዳዩ በቁጥር ማነስና መብዛት የሚወሰንም አይደለም። በዐረቡ ዓለም ውስጥ ያሉ ክርስቲያኖች 5% አይሞሉም። ቁጥራቸው ስላነሰ ዐረብነታቸውን መንጠቅ እንችላለን? አይሆንምኮ! በአማራ ፖለቲከኞች አግላይ አካሄድ ሰበብ በክልሉ ውስጥ ያሉ ከ17% (በመንግስት ህዝብና ቤት ቆጠራ ከተቀመጠው) በላይ ሙስሊሞችን ብሄር የለሽ ናቸው ልንል ነውን? አንችልምኮ! ደግሞም ራሱን በሆነ ብሄር የሚገልፅ አካል "እናንተ ግን ብሄር የላችሁም" ማለት አለበት ወይ? አይባልም። ስለሆነም ሙስሊም ወገኖቻችንን ራሳቸውን በአማራነት ስለገለፁ የምንተችበት አካሄድ ፈፅሞ የተሳሳተ ነው። ማድረግ ያለብን ዘረኝነት ሲጎትታቸው ካየን ከየትም ብሄር ቢሆኑ አላህን እንዲፈሩ ማስታወስ ብቻ ነው። እንጂ አማራ ተብለው እየተገደሉበት፣ እየተገፉበት ያለን ማንነት የለም አይደላችሁም አይባልም።

ስለዚህ  ዛሬ አማራነትን ክርስቲያን ማለት አድርጎ የሚገልፅ ካለ ምሁርም ይሁን መሀይም፣ ደጋፊም ሆነ ነቃፊ ያለ ጥርጥር ተሳስቷል። ይሄ አተረጓጎም የህዝቦችን ማንነትና ማህበራዊ ውቅር ተለዋዋጭነት (dynamism) ከግንዛቤ ያላስገባ ግልብ ድምዳሜ ነው። ስያሜዎች በዘመናት ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች እንደ አካባቢው ሁኔታ ይለዋወጣሉ።

* ትናንት ቱርክ፣ ደይለም፣ ፋርስ የሚሉት መጠሪያዎች ሙስሊም ያልሆኑ ህዝቦችን ለመግለፅ የዋሉበት ዘመን ነበር፣ ለሚታወቅ ምክንያት። ያ ዘመን ካለፈ በኋላ እነዚህ ስያሜዎች ሃይማኖትን ገላጭ የነበረው ይዘታቸው ቀርቷል። አማራም ላይ ያለው እውነታ ተመሳሳይ ነው።

* በፊት አጎራባቾቹ አማራና አርጎባ መሀል የነበረው እውነታም ይህንን አጉልቶ ያሳያል። ሰሜን ሸዋ ላይ አንድ ክርስቲያን አማራ ወደ ኢስላም ሲገባ "እከሌ አርጎባ ሆነ" ነበር የሚባለው። አንድ አርጎባ ወደ ክርስትና ሲገባ ደግሞ "አማራ ሆነ" ነበር የሚባለው። ዛሬ ግን አርጎባነት ዘር እንጂ ሃይማኖት እንዳልሆነ ግልፅ ነው። አንድ ሰው ሃይማኖቱ ስለተቀየረ ዘሩ እንደማይቀየር ማወቅኮ ያን ያህል ውስብስብ ሂሳብ አይደለም።

* ሲዳማ የሚለው ቃል ሃይማኖትን ሲገልፅ የነበረበት ዘመንም ነበር። ዛሬ የሲዳማ መስሊሞችን "ሲዳማ አይደላችሁም፣ ሙስሊሞች ናችሁ" ልንላቸው አንችልም። ምክንያቱም ሲዳማነት እንደ ትላንቱ ሃይማኖትን ሳይሆን የሲዳማ ቋንቋ በወል የሚያገናኛቸው ህዝቦችን የሚገልፅ የብሄር ስያሜ እንደሆነ ግልፅ ነውና። ይሄ ቀላል ግንዛቤ አማራ ዘንድ ሲደርስ መልኩን የሚቀይርበት ስሌት የለም።

ስለዚህ የአማራ ሙስሊሞች ከብሄር አንፃር እንዴት ራሳቸውን አማራ ብለው ይጠራሉ የሚል አተካራ ውስጥ መግባት አያስፈልግም። ይሄ ብሄር ተኮር ጥላቻና መነቋቆርን ከማምጣት ባለፈ የሚያመጣው ኸይር የለም። ማድረግ ያለብን በየትኛውም ብሄር ውስጥ ያደፈጡ ዘረኛ ቡድኖች መጠቀሚያ እንዳንሆን ተቆርቋሪነት በሚታይበት መልኩ እርስ በርሳችን መመካከር ነው። ዋናው ነገር ኢስላማዊ ወንድማማችነታችን የዘር አጥር የሚገድበው አለመሆኑ ነው። የላ ኢላሀ ኢለላህ ገመድ ከዘርና ከቋንቋ በላይ ነው። ዛሬ ስለታመምን እንጂ ለሙስሊሙ አማራ ከነሷራው አማራ በላይ ሙስሊሙ ኦሮሞ ነው የሚቀርበው። ለሙስሊሙ ኦሮሞ ከነሷራው ኦሮሞ በላይ ሙስሊሙ አማራ ነው የሚቀርበው። በጠጣነው ፖለቲካዊ መርዝ ሳቢያ ቢተናንቀንም እውነታው ያ ነው። በዘር ቢሆን ለውዱ ነብያችን ﷺ ከሐበሻው ቢላል በላይ አጎታቸው አቡ ለሃብ በስጋ ይቀርባቸው ነበር። ኢስላማዊው መለኪያ ግን ሌላ ነው። ኢማንና ዘር እኩል ሚዛን ላይ አይቀመጡምና።

(ኢብኑ ሙነወር፣ ጁማደል ኡላ 27/1445፣ (ታህሳስ ዐ1/2016))

=

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

በሌሊቱ ወቅት የሱረቱል በቀራን የመጨረሻ ሁለት አንቀጾች ያነበበ ሰው በአላህ ፍቃድ ሌሊቱን ከመጥፎ ነገር ሁሉ እንደሚጠበቅ ተረድቶ ሲያበቃ አንቀፆቹን አዘወትሮ ያነበባቸው ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ፈርድ የሆኑ ስላቶችን ከሰገደ በኋላ አያተል ኩርሲይን ካነበበ ጀነትን መግባት ሞት እንጂ ምንም እንደ ማይከለክለው ተረድቶ አዘወትሮ አያተል ኩርሲይን ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ከመተኛቱ በፊት አያተል ኩርሲይን ያነበበ ሰው ለሊቱን ሙሉ እስኪያነጋ ከአላህ የተመደበ ጠባቂ እንደሚጠብቀውና ሸይጣንም እንደማይቀርበው አውቆ ከመተኛቱ በፊት አያተል ኩርሲይን አዘወትሮ ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ሱረቱል ኢኽላስን ሶስት ጊዜ ማንበብ ሙሉ ቁርዓንን ከማኽተም ጋር እንደሚስተካከል ተረድቶ ይህችን ሱራ አብዝቶ ያነበበ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ለሴትና ለወንድ አማኞች ሁሉ ዱዓዕ ያደረገ ሰው በአያንዳንዱ አማኝ አላህ ዘንድ አጅር እንደሚመዘገብለት ተረድቶ ለሙዕሚኖች ሁሉ አብዝቶ ዱዓዕ ያደረገ ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ሱብሃነሏህ

ወል ሀምዱ ሊላህ

ወላ ኢላሃ ኢለሏህ

ወሏሁ አክበር

ማለት ፀሀይ ከወጣችበት ሁሉ የተሻለና የበለጠ መሆኑን ተረድቶ እነዚህን ውድ ቃላት አብዝቶና ደጋግሞ ያላቸው ሰው ነው።

እደለኛ ሰው ማለት.....!👌

ይህንን ካወቀ በኋላ የሰራበትና ሌሌሎችም እንዲያውቁና እንዲተገብሩ በማሰታወስና በማካፈል የአጅሩ ተካፋይ የሆነ ሰው ነው።

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

👉ኤርዶጋን "እስራኤል ነፍሰ ገዳይ ብቻ ሳትሆን ሌባም ነች" ያሉ ሲሆን "እስራኤል እንደገና ጋዛን እንድትይዝ መፍቀድ አንችልም"።

👉"የጥቂት አገሮችን ፈቃድ የሚከተል ዓለም አቀፋዊ መዋቅር አለ የተባበሩት መንግስታት ብልሹ መዋቅር መለወጥ አለበት።"

👉ኢስላም ጠልነት በምዕራቡ ዓለም እንደ ወረርሽኝ እየተስፋፋ ነው።

👉"ጋዛ የፍልስጤም ግዛት ናት፣ ጋዛ ለፍልስጤማዊያን የተገባች ናት ለዘላለምም እንዲሁ ትኖራለች።"

#hamas #gaza #qassam #mujahidin #quds #palestine #oic #arableague #resistance #yemen

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

ስፔይን እስራኤልን ወራሪ ሀገር በማለት አወገዘቻት።

እስራኤል ከስፔን አምባሳደሯን ጠርታለች

ስፔይን ከአውሮፓ ሀገራት ሁሉ ቀድማ ከፍልስጥኤማውያን ጎን ተሰልፋለች ።

ፖለቲከኞቿ እስራኤልን ከማውገዝ አልፈው አለምአቀፍ ንቅናቄ ጀምረዋል !

የስፔይኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ እስራኤል የፍልስጤም ምድርን ወርራለች ሲሉ ወርፈዋታል ።

እንደ አውሮፓ ሞራል አለን የምንል ከሆነ ከፍልስጤማውያን ጎን መቆምና የእስራኤልን ድርጊት ማውገዝ አለብንም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ።

የስፔይኑ መሪ አክለውም ብቸኛው መፍትሄ ፖለቲካዊ ነው ያሉ ሲሆን ይህም የሚሆነው ፍልስጤም ሀገር ሆና ስትቆም ነው ብለዋል ።

ጠቅላይ ማኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ አውሮፓ ለፍልስጥኤም የሀገርነት እውቅና መስጠት አለባት ያሉ ሲሆን ስፔይን በበኩሏ ይህንን እንደምታደርግ ፍንጭ ሰጥተዋል ።

በጋዛ የሚደረገው የህፃናት ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ መሆኑን የተናገሩት የስፔይኑ መሪ ይህም እስራኤል አለምአቀፍ ህጎቾን የማታከብር መሆኗን ያሳያል ብለዋል ። በዚህ ድርጊት የተበሳጨቺው እስራኤልም አምሳደሯን ከስፔን ጠርታለች ።

ከቀናት በፊት የስፔይኗ ውብና ትልቅ ከተማ ባርሴሎና ከእስራኤል ጋር የሚደረግን ግንኙነት ሁሉ ማገዷ ይታወቃል ።

ስፔይን የአውሮፓዋ ደቡብ አፍሪካ ሆናለች !

Send as a message
Share on my page
Share in the group
Translation is not possible.

በዲንህም ሆነ በባህሪህ ጠንካራና ምርጥ ላለመሆንህ የአካባቢህ የጓደኛህም ሆነ የቤተሰብህ ጥሩ አለመሆናቸው ምክንያት ማቅረብህ አግባብ አይደለም ምክንያቱም የትኛውም ያህል መጥፎ ማህበረሰብ መሀል ብትሆን ከፊርአውን  አይብሱም አላህ ደግሞ ከፊርአውን ቤት ያቺን ምርጥ ሴት እስከቂያም ቀን ለአማኞች ሁሉ ተምሳሌት አድርጎ አስቀምጧታል።

image
Send as a message
Share on my page
Share in the group